መሐመድ (ቁትኸም) መጽሃፍ ቅዱስ ላይ አልተጠቀሰም የምትሉት ግን ክርስቲያኖች ምን ነክቷችሁ ነው ከዚህ በላይ ምን ማስረጃ ይምጣ
Forwarded from J.CHRISTIAN
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
They might have horses and chariots but we will be great by the name of God YHWH
ደጁ ክፋችለት 💐
ልባም ሴት 😍
መኃልየ. 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል፤ የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል፤ እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።
³ ቀሚሴን አወለቅሁ፤ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ፤ እንዴት አሳድፈዋለሁ?
⁴ ውዴ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥ አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከ።
⁵ ለውዴ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ፤ እጆቼ በደጅ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥ ጣቶቼ ፈሳሹን ከርቤ አንጠበጠቡ።
⁶ ለውዴ ከፈትሁለት፥ ውዴ ግን ፈቀቅ ብሎ አልፎ ነበር። ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች፤ ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም፤ ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም።
⁷ ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ፤ መቱኝ፥ አቈሰሉኝም፤ ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት።
⁸ እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ አምላችኋለሁ፤ ውዴን ያገኛችሁት እንደ ሆነ፥ እኔ ከፍቅር የተነሣ መታመሜን ንገሩት።
⁹ አንቺ በሴቶች ዘንድ የተዋብሽ ሆይ፥ ከሌላ ወዳጅ ይልቅ ውድሽ ማን ነው? ይህን የሚያህል አምለሽናልና ከሌላ ወዳጅ ይልቅ ውድሽ ማን ነው?
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል፤ የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል፤ እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ።
³ ቀሚሴን አወለቅሁ፤ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ፤ እንዴት አሳድፈዋለሁ?
⁴ ውዴ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥ አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከ።
⁵ ለውዴ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ፤ እጆቼ በደጅ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥ ጣቶቼ ፈሳሹን ከርቤ አንጠበጠቡ።
⁶ ለውዴ ከፈትሁለት፥ ውዴ ግን ፈቀቅ ብሎ አልፎ ነበር። ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች፤ ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም፤ ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም።
⁷ ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ፤ መቱኝ፥ አቈሰሉኝም፤ ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት።
⁸ እናንተ የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት ሆይ፥ አምላችኋለሁ፤ ውዴን ያገኛችሁት እንደ ሆነ፥ እኔ ከፍቅር የተነሣ መታመሜን ንገሩት።
⁹ አንቺ በሴቶች ዘንድ የተዋብሽ ሆይ፥ ከሌላ ወዳጅ ይልቅ ውድሽ ማን ነው? ይህን የሚያህል አምለሽናልና ከሌላ ወዳጅ ይልቅ ውድሽ ማን ነው?
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ማሜ ስለ አይሻ ሲጠየቅ He'll be like
ኑ በብርሃኑ እንመላለስ
Photo
Synergy
(ከማኅደር የወጣ)
--
#Synergy:- ነገረ ድኅትን ኦርቶዶክሳውያን አበው እንደዚያ ይሉታል፡፡ መዳን የሰው በነጻ ፈቃድ የሚገለጥ የመዳን ፍላጎትና የእግዚአብሔር መለኮታዊ ፍጹም ፍቅር ውጤት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠነሰስም እንዲሁ ነው፡፡ ‹‹ይኩነኒ›› በነገረ ድኅነት የሰው ልጅ የመዳን ፍላጎት የተገለጠባት ቃል ናት፡፡ ‹‹በአማን ነጸረ እግአብሔር ሰማየ ወምድረ››፤ ዓለሙን ሁሉ አየ፡፡ መረጣት፡፡ ስለመረጣት አላስገደዳትም፡፡ ፈቃዷን በአረጋዊ አምሳል በተገለጠ መልአክ በኩል አረጋገጠ፡፡ ሲያድንህ እንኳ አያስገድድህም፡፡ እንደ ሔዋን የተነገራትን ሁሉ መቀበል ሳይሆን መረመረች፡፡ ‹‹ወንድ ሳላውቅ እንዴት ይሆንልኛል›› ብላ ተሟገተች፡፡ ፅንሰቱ ከወንድ በሚሆን ዘር ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ሥራ (በግብረ መንፈስ ቅዱስ) እንደሆነ ነግሮ ‹‹ለእግዚአብሔር የሚሣነው ነገር የለም›› ሲል ክርክሩን በመለኮታዊ ክሂል ዘጋው፡፡ ከሃሊነቱን አመነች፡፡ ወላዲተ አምላክ ማዕምንት! በላት እንጂ! ተመልከትልኝ፡- ጌታ ለእናትነት የመረጣትን እናት ግዑዝ መጠቀሚያ መሣሪያ (passive instrument) አላደረጋትም፤ ፈቃዷን መግለጥ የምትችል ተሣታፊት (active participant) አደረጋት እንጂ፡፡ ለመመረጡዋ ድርሻ አላት፡፡ ተዘልላ ተቀማጥላ አይደለም የተመረጠች፡፡ ያማ እንዳልሆነ መልአኩ ገና ሰላምታ ሲያቀርብላት ‹‹ጸጋን የተመላሽ›› ብሎ ጀመረ፡፡ ‹‹እንዘ ንጽሕት ይእቲ በድንግልና፡ አልባቲ ሙስና›› ብለህ ዘምር እንጂ! ንጽሕናዋ ከምርጫው፣ ጥሪው ከፈቃዷ ገጠሙ - Synergy፡፡ ወዲህም ልትስበው ትችላለህ፡፡ መዳንህ በአንተ ፈቃድና ፍላጎት እንዲሁም በእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር ይከናወናል፡፡ በመዳንህ ውስጥ ድርሻ አለህ! አምነህ በምትሥራው ሥራ ፈቃድህ ይገለጣል፡፡ ግዑዝ አይደለህም፡፡ በመዳንህ ውስጥ ድርሻ አለህ፡፡ ‹‹ዘያድኅን ኪያከ እንበሌከ ኢያጸድቅ ኪያከ - አዳኝህ ያለሡታፌህ ያለፈቃድህ ኣያድንህም›› (ጥቅሱን ብስተው አትቀየመኝ!)፡፡ ሰብአዊ ክብርና ነጻ ፈቃድህ እዚህ ውስጥ አለ፡፡ ‹‹ፕሮግራምድ›› የተደረግህና በዕጣ ፈንታህ ድርሻ የሌለህ ግዑዝ ፍጥረት አይደለህም! የእመቤታችን በድኅነት መንገድ አስቀድማ በልበ ሥላሴ መታሰቧን ካቶሊካውያን እንዲህ ያመሠጥሩታል፤ የእርሱን ከሃሊነትን ሳይጋፉ የመለኮታዊ ፕሮጀክቱ አካል ነበረች ይሏታል፡- the redemption of mankind should depend upon the consent of the Virgin Mary. This does not mean that God in His plans was bound by the will of a creature, and that man would not have been redeemed, if Mary had not consented. It only means that the consent of Mary was foreseen from all eternity, and therefore was received as essential into the design of God. ቅዱስ ያሬድ በነሐሴ ኪዳነ ምሕረት ድጓው ‹‹እንበለ ትሣረር ምድረ ገነት ሀለወት ቅድስት ድንግል ማርያም›› ማለቱ ከዚህ ይስማማል፡፡ ቃኘውማ! በሕሊና አምላክ ታስባ ትኖር ነበር! Mary was foreseen from all eternity!
--
#ተአምር፡- በነገረ ማርያም ከሚነገሩ ተአምራት ውስጥ አንደኛው ከላይ ያለው ነው፡፡ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና መውለዷ ተአምር ነው፡፡ ያለወንድ ዘር መውለዷ ተአምር ነው፡፡ ተአምር ምንድን ነው? በአዘቦት ኑሮ ያልተለመደ፣ በተፈጥሮ ሕግ ያልተለመደ፣ ከሕሊናና አመክንዮ በላይ የሆነ ማለት ነው፡፡
--
#ቅዱስ_ገብርኤል፡- ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ገብርኤል ብሒል ወልደ እግዚአብሔር - ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ልጅ ማለት ነው›› ይለዋል (በአርያም)፡፡ ዕብራውያን ‹‹እግዚአብሔር ብርታቴ ነው›› ማለት ነው ይሉታል ይሉናል - "God is my strength"፡፡ ናቡከደነፆር በሦስቱ ሕፃናት መካከል በሚነበለበል እሳት መካከል ባየው ጊዜ ‹‹አራተኛውም የእግዚአብሔርን ልጅ ይመስላል›› እንዳለው በትንቢተ ዳንኤል ተጽፏል፡፡ ቅዱስ ያሬድ እርሱን ወስዷል፡፡ ሊቃውንት በቅጽል ስም ቅዱስ ገብርኤልን መጋቤ ሐዲስ ይሉታል፡፡ መበሥር ይሉታል፡፡ ወንጌል ማለት ብሥራት ነው፡፡ ሉቃስ እንደነገረን አብሣሪው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በወንጌል ውስጥ ያለ ወንጌላዊ ቅዱስ ገብርኤል ነዋ!
--
#የብሥራት_ቀን፡- ምሥጢሩ ከትስብእት ይስማማል፡፡ ከመጋቢት 29፡፡ ብሥራቷን ፈረንጆችም በዚያ አካባቢ ያከብሩታል፡፡ በማርች ወር፣ ማርች 25፡፡ ብሥራተ ገብርኤልንም ከዚያ አያይዘው ይዘክሩታል፡፡ ማርች 26፡፡ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት መጋቢት 29 ቀን ከሚከበረው የትስብእት በዓል ለምን ወደ ታኅሣሥ 22 እንደሳቡት ገና ጠይቀን አልተረዳንም፡፡ ብሥራትና ፅንሰት አንድ ቀን ናቸውና ከልደት ጋር ለማስማማት ያውካሉ፡፡ በዓላት መዘዋወራቸው ቀኖና ስለሆነ አያጣላም፡፡ አያጣላም ያሰኘውን ምሥጢር እንሰማለን፡፡ መሰቀል፣ ደብረ ዘይት፣ ምኲራብ፣ በዘመን ደረጃም አስተምህሮ በዓመት ሁለት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ሲታሰቡ ስለምናይ አበው ያለምክንያት ወዲህ እንደማይስቡት እናምናለን፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በራሱ በትውፊታውያን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የመታሰቢያ ቀን አለው፡፡ከዚያም አልፎ በቤተ አይሁድና ሙስሊሞች ክብር አለው፡፡ በተለይ እመቤታችንን ያበሠረበት ቀን Annunciation እየተባለ ይከበራል፡፡ ግሪካውያን ከብሔራዊ በዓላቸው አገናኝተው በብሔራዊ ደረጃ ያከብሩታል፡፡ ይገባዋል! ‹‹ብሥራት›› የሚባል ቤተ ክርስቲያንም ማቋቋም የተለመደ ነው፡፡ በእኛም ብሥራተ ገብርኤል ተብሎ ጽላት ተቀርጾ መከበር መዘከሩ ትውፊቱን የጠበቀ ነው፡፡ ብሥራቷ ብሥራታችን ነው!
--
#ደቅስዮስ፡- ተአምረ ማርያምን ካሰባሰቡ ሊቃውንት ዋነኛው ነው፡፡ በአገራችን ዝክርም መልክም ዚቅም አለው፡፡ ዓመታዊ መታሰቢያው ከዕለተ ብሥራት ይገጥማል፡፡ ታኅሣሥ 22 በየዓመቱ ይዘከራል፡፡
--
#የብሥራት_ምሥጢር፡- የእመቤታችን ብሥራት ምሥጢረ ሥጋዌ፣ ነገረ መንፈስ ቅዱስ፣ ምሥጢረ ሥላሴ በነገረ ድኅነት የሚነገርበት የምሥጢራት መገጣጠሚያ ነው፡፡ ‹‹ይኩነኒ ባለች ጊዜ አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ሆነ››፡፡ እንዴት ሆኖ? አምላክ ሰው ሆነ የምንልበት ምሥጢረ ተዋሕዶ፣ ቃል ሥጋ ሆነ የሚነገርበት ምሥጢር! ብሥራት የሰው ልጅ የድኅነት መንገድ በጌታ ግዘፍ መንሣት በማኅፀን የተጀመረበት ነው! መዳናችን የጀመረ አምላክ በድንግል ማኅፀን ሲያድር ነው፡፡ ቁራኝነት ጠፋ! ብለው ይነሣሉ መተርጕማኑ፡፡ ደጋግመን የምንለው ነው! የሰውን መዳን ቀራንዮ ላይ ብቻ አንጠልጥሎ መረዳት የጌታን 33 ዓመት ከሦስት ወር ጉዞና ፅንሰት ዋጋ ማሳጣት ነው፡፡ ሥጋዌ የነገረ ድኅነት አካል ነው፡፡ መረዳት ሲያቅትህ ‹‹ስለተከፈለልን እንጂ ስለከፋዩ ማንነት መብሰልሰል አያስፈልግም!›› ብትል ከሠርክ፡፡ ክርስቶስን፣ ሰው የሆነውን አምላክ፣ ሥግው ቃልን ለማወቅ ከብሥራቱ ሂደት መጀመር ይመከራል፡፡ እንዲያ ሲሆን ክርስቶስን ከተራ ካሸር ከፍ አድርገህ ማየት ትጀምራለህ! ሰው መገሆኑ፣ ሰው በመሆን ውስጥ የተገለጠ ትሕትናው፣ ትምህርቱ፣ ስደቱ፣ ቤተ መቅደስ መግባቱ፣ ጾሙ፣ ቅደመ ቀራንዮ በዚህ ምድር ያከናወናቸው ተግባራት ሁሉ በመዳናችን ውስጥ ቦታ አላቸው፡፡ እናቱን እንዳንተዋት በብሥራቱም፣ በስደቱም፣ በስቅለቱም ‹‹ልጄ ልጄ›› እያለች ልባችንን
(ከማኅደር የወጣ)
--
#Synergy:- ነገረ ድኅትን ኦርቶዶክሳውያን አበው እንደዚያ ይሉታል፡፡ መዳን የሰው በነጻ ፈቃድ የሚገለጥ የመዳን ፍላጎትና የእግዚአብሔር መለኮታዊ ፍጹም ፍቅር ውጤት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ሲጠነሰስም እንዲሁ ነው፡፡ ‹‹ይኩነኒ›› በነገረ ድኅነት የሰው ልጅ የመዳን ፍላጎት የተገለጠባት ቃል ናት፡፡ ‹‹በአማን ነጸረ እግአብሔር ሰማየ ወምድረ››፤ ዓለሙን ሁሉ አየ፡፡ መረጣት፡፡ ስለመረጣት አላስገደዳትም፡፡ ፈቃዷን በአረጋዊ አምሳል በተገለጠ መልአክ በኩል አረጋገጠ፡፡ ሲያድንህ እንኳ አያስገድድህም፡፡ እንደ ሔዋን የተነገራትን ሁሉ መቀበል ሳይሆን መረመረች፡፡ ‹‹ወንድ ሳላውቅ እንዴት ይሆንልኛል›› ብላ ተሟገተች፡፡ ፅንሰቱ ከወንድ በሚሆን ዘር ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ሥራ (በግብረ መንፈስ ቅዱስ) እንደሆነ ነግሮ ‹‹ለእግዚአብሔር የሚሣነው ነገር የለም›› ሲል ክርክሩን በመለኮታዊ ክሂል ዘጋው፡፡ ከሃሊነቱን አመነች፡፡ ወላዲተ አምላክ ማዕምንት! በላት እንጂ! ተመልከትልኝ፡- ጌታ ለእናትነት የመረጣትን እናት ግዑዝ መጠቀሚያ መሣሪያ (passive instrument) አላደረጋትም፤ ፈቃዷን መግለጥ የምትችል ተሣታፊት (active participant) አደረጋት እንጂ፡፡ ለመመረጡዋ ድርሻ አላት፡፡ ተዘልላ ተቀማጥላ አይደለም የተመረጠች፡፡ ያማ እንዳልሆነ መልአኩ ገና ሰላምታ ሲያቀርብላት ‹‹ጸጋን የተመላሽ›› ብሎ ጀመረ፡፡ ‹‹እንዘ ንጽሕት ይእቲ በድንግልና፡ አልባቲ ሙስና›› ብለህ ዘምር እንጂ! ንጽሕናዋ ከምርጫው፣ ጥሪው ከፈቃዷ ገጠሙ - Synergy፡፡ ወዲህም ልትስበው ትችላለህ፡፡ መዳንህ በአንተ ፈቃድና ፍላጎት እንዲሁም በእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር ይከናወናል፡፡ በመዳንህ ውስጥ ድርሻ አለህ! አምነህ በምትሥራው ሥራ ፈቃድህ ይገለጣል፡፡ ግዑዝ አይደለህም፡፡ በመዳንህ ውስጥ ድርሻ አለህ፡፡ ‹‹ዘያድኅን ኪያከ እንበሌከ ኢያጸድቅ ኪያከ - አዳኝህ ያለሡታፌህ ያለፈቃድህ ኣያድንህም›› (ጥቅሱን ብስተው አትቀየመኝ!)፡፡ ሰብአዊ ክብርና ነጻ ፈቃድህ እዚህ ውስጥ አለ፡፡ ‹‹ፕሮግራምድ›› የተደረግህና በዕጣ ፈንታህ ድርሻ የሌለህ ግዑዝ ፍጥረት አይደለህም! የእመቤታችን በድኅነት መንገድ አስቀድማ በልበ ሥላሴ መታሰቧን ካቶሊካውያን እንዲህ ያመሠጥሩታል፤ የእርሱን ከሃሊነትን ሳይጋፉ የመለኮታዊ ፕሮጀክቱ አካል ነበረች ይሏታል፡- the redemption of mankind should depend upon the consent of the Virgin Mary. This does not mean that God in His plans was bound by the will of a creature, and that man would not have been redeemed, if Mary had not consented. It only means that the consent of Mary was foreseen from all eternity, and therefore was received as essential into the design of God. ቅዱስ ያሬድ በነሐሴ ኪዳነ ምሕረት ድጓው ‹‹እንበለ ትሣረር ምድረ ገነት ሀለወት ቅድስት ድንግል ማርያም›› ማለቱ ከዚህ ይስማማል፡፡ ቃኘውማ! በሕሊና አምላክ ታስባ ትኖር ነበር! Mary was foreseen from all eternity!
--
#ተአምር፡- በነገረ ማርያም ከሚነገሩ ተአምራት ውስጥ አንደኛው ከላይ ያለው ነው፡፡ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና መውለዷ ተአምር ነው፡፡ ያለወንድ ዘር መውለዷ ተአምር ነው፡፡ ተአምር ምንድን ነው? በአዘቦት ኑሮ ያልተለመደ፣ በተፈጥሮ ሕግ ያልተለመደ፣ ከሕሊናና አመክንዮ በላይ የሆነ ማለት ነው፡፡
--
#ቅዱስ_ገብርኤል፡- ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ገብርኤል ብሒል ወልደ እግዚአብሔር - ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔር ልጅ ማለት ነው›› ይለዋል (በአርያም)፡፡ ዕብራውያን ‹‹እግዚአብሔር ብርታቴ ነው›› ማለት ነው ይሉታል ይሉናል - "God is my strength"፡፡ ናቡከደነፆር በሦስቱ ሕፃናት መካከል በሚነበለበል እሳት መካከል ባየው ጊዜ ‹‹አራተኛውም የእግዚአብሔርን ልጅ ይመስላል›› እንዳለው በትንቢተ ዳንኤል ተጽፏል፡፡ ቅዱስ ያሬድ እርሱን ወስዷል፡፡ ሊቃውንት በቅጽል ስም ቅዱስ ገብርኤልን መጋቤ ሐዲስ ይሉታል፡፡ መበሥር ይሉታል፡፡ ወንጌል ማለት ብሥራት ነው፡፡ ሉቃስ እንደነገረን አብሣሪው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በወንጌል ውስጥ ያለ ወንጌላዊ ቅዱስ ገብርኤል ነዋ!
--
#የብሥራት_ቀን፡- ምሥጢሩ ከትስብእት ይስማማል፡፡ ከመጋቢት 29፡፡ ብሥራቷን ፈረንጆችም በዚያ አካባቢ ያከብሩታል፡፡ በማርች ወር፣ ማርች 25፡፡ ብሥራተ ገብርኤልንም ከዚያ አያይዘው ይዘክሩታል፡፡ ማርች 26፡፡ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት መጋቢት 29 ቀን ከሚከበረው የትስብእት በዓል ለምን ወደ ታኅሣሥ 22 እንደሳቡት ገና ጠይቀን አልተረዳንም፡፡ ብሥራትና ፅንሰት አንድ ቀን ናቸውና ከልደት ጋር ለማስማማት ያውካሉ፡፡ በዓላት መዘዋወራቸው ቀኖና ስለሆነ አያጣላም፡፡ አያጣላም ያሰኘውን ምሥጢር እንሰማለን፡፡ መሰቀል፣ ደብረ ዘይት፣ ምኲራብ፣ በዘመን ደረጃም አስተምህሮ በዓመት ሁለት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ሲታሰቡ ስለምናይ አበው ያለምክንያት ወዲህ እንደማይስቡት እናምናለን፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በራሱ በትውፊታውያን አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ የመታሰቢያ ቀን አለው፡፡ከዚያም አልፎ በቤተ አይሁድና ሙስሊሞች ክብር አለው፡፡ በተለይ እመቤታችንን ያበሠረበት ቀን Annunciation እየተባለ ይከበራል፡፡ ግሪካውያን ከብሔራዊ በዓላቸው አገናኝተው በብሔራዊ ደረጃ ያከብሩታል፡፡ ይገባዋል! ‹‹ብሥራት›› የሚባል ቤተ ክርስቲያንም ማቋቋም የተለመደ ነው፡፡ በእኛም ብሥራተ ገብርኤል ተብሎ ጽላት ተቀርጾ መከበር መዘከሩ ትውፊቱን የጠበቀ ነው፡፡ ብሥራቷ ብሥራታችን ነው!
--
#ደቅስዮስ፡- ተአምረ ማርያምን ካሰባሰቡ ሊቃውንት ዋነኛው ነው፡፡ በአገራችን ዝክርም መልክም ዚቅም አለው፡፡ ዓመታዊ መታሰቢያው ከዕለተ ብሥራት ይገጥማል፡፡ ታኅሣሥ 22 በየዓመቱ ይዘከራል፡፡
--
#የብሥራት_ምሥጢር፡- የእመቤታችን ብሥራት ምሥጢረ ሥጋዌ፣ ነገረ መንፈስ ቅዱስ፣ ምሥጢረ ሥላሴ በነገረ ድኅነት የሚነገርበት የምሥጢራት መገጣጠሚያ ነው፡፡ ‹‹ይኩነኒ ባለች ጊዜ አካላዊ ቃል ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ሆነ››፡፡ እንዴት ሆኖ? አምላክ ሰው ሆነ የምንልበት ምሥጢረ ተዋሕዶ፣ ቃል ሥጋ ሆነ የሚነገርበት ምሥጢር! ብሥራት የሰው ልጅ የድኅነት መንገድ በጌታ ግዘፍ መንሣት በማኅፀን የተጀመረበት ነው! መዳናችን የጀመረ አምላክ በድንግል ማኅፀን ሲያድር ነው፡፡ ቁራኝነት ጠፋ! ብለው ይነሣሉ መተርጕማኑ፡፡ ደጋግመን የምንለው ነው! የሰውን መዳን ቀራንዮ ላይ ብቻ አንጠልጥሎ መረዳት የጌታን 33 ዓመት ከሦስት ወር ጉዞና ፅንሰት ዋጋ ማሳጣት ነው፡፡ ሥጋዌ የነገረ ድኅነት አካል ነው፡፡ መረዳት ሲያቅትህ ‹‹ስለተከፈለልን እንጂ ስለከፋዩ ማንነት መብሰልሰል አያስፈልግም!›› ብትል ከሠርክ፡፡ ክርስቶስን፣ ሰው የሆነውን አምላክ፣ ሥግው ቃልን ለማወቅ ከብሥራቱ ሂደት መጀመር ይመከራል፡፡ እንዲያ ሲሆን ክርስቶስን ከተራ ካሸር ከፍ አድርገህ ማየት ትጀምራለህ! ሰው መገሆኑ፣ ሰው በመሆን ውስጥ የተገለጠ ትሕትናው፣ ትምህርቱ፣ ስደቱ፣ ቤተ መቅደስ መግባቱ፣ ጾሙ፣ ቅደመ ቀራንዮ በዚህ ምድር ያከናወናቸው ተግባራት ሁሉ በመዳናችን ውስጥ ቦታ አላቸው፡፡ እናቱን እንዳንተዋት በብሥራቱም፣ በስደቱም፣ በስቅለቱም ‹‹ልጄ ልጄ›› እያለች ልባችንን
ኑ በብርሃኑ እንመላለስ
Photo
ታባባዋለች፡፡ በተሰቃየበት ሁሉ ተሰቃየች! ስላልተወችው አንተዋትም! ቃል አለብን ‹‹እነኋት እናትህ›› የሚለው ቃል ሕያው ነው! የመጽሐፍ ቃል በኃላፊ፣ በተራ ታሪክ አነጋገር ‹‹በድሮ ጊዜ …ሲኖሩ ሲኖሩ … ከዚያ ሞቱ …›› የሚባል የልጅ ማባበያ ተረት አይደለም! ሕያው ነው! ‹‹እነኋት እናትህ!›› ዘወትር የምንኖርለት ሕያው ቃል ነው!
--
እንኳን ለብሥራታዊው መልአክ ዓመታዊ መታሰቢያ አደረሰን! መልካም በዓል!
--
ከደብተራ በአማን ነፀረ
--
እንኳን ለብሥራታዊው መልአክ ዓመታዊ መታሰቢያ አደረሰን! መልካም በዓል!
--
ከደብተራ በአማን ነፀረ
😥 ይኽች ሴትዮ በሀገረ በአሜሪካ ሲያትል የምትኖር የአስተዳዳሪው ሚስት ናት !
«በአሕዛብስንኳ የማይገኝ ነው» [ 1ኛ ቆሮ. 5 ÷ 1 ] ያለው ቃሉን ስናስታውስ በርካታ ጉዳዮቻችን ወዴት እየሔዱ ነው እያስባሉን ነው ።
**_. በዚህ ዘመን የሚሠወር ክብርም ሆነ ነውር የለም ። ከነውር ይልቅ ክብርን መሠወር ቀላል ሆኗል ። ስለዚህ በዚህ ዘመን ያሉ አንዳንድ የደብር አስተዳዳሪዎችና ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎች በቅድስት ቤተክርስቲያን የሚፈጽሙት ጥፋት ከቀን ወደ ቀን እንደ ደም ብዛት እየጨመረ መጥቷል ። የነውርና የጥፋታቸው መበራከት ደግሞ ሌላውን ሰው ከሌላ በረት ለመሰብሰብና ለማምጣት ተስኗቸው የሚያዘገይ ብቻም ሳይሆን በቤቱ ያለንንም መንጋ የሚበትን ፣ የሚያሳድድ ፣ የሚያስኮበልል ፣ ተስፋ የሚያስቆርጡ ፣ ለሚሰሟቸው ደግሞ የሚያቅለሸልሹ ማሰናከያ ጉቶ ሆነዋል ። ቅድስት ቤተክርስቲያን እንድታተርፍ መክሊት የተቀበሉ አገልጋዮች አክሳሪ መክሊት ቀባሪ ነጋዴዎች በመኾናቸው እንድትከስስር እያደረጓት ነው ።
**➥. «ሴቶች» እጅግ ጥበበኞች ሃይማኖታቸው የጸና መጻሕፍትንም የተማሩ ምሥጢርንም ያደላደሉ ቢሆኑ "ያጠምቁና ወንጌልን ያስተምሩ ዘንድ ፈጽሞ አንፈቅድም በካህናት መካከልም ሆነው እንዲቅሙ አንፈቅድም ።
( ዲዲስቅልያ 14 )
** በቤተክርስቲያን ጸሎትአያስጀምሩ ። ለማሰናበት በጸሎት ዐያሳርጉ ። ( ፍት.መን. አንቀጽ 8 )
ይኽንን ነውር እያዩ እንዳላዩ እየሰሙ እንዳልሰሙ ዝም ማለት ራሱ ከነውርም ነውር ነው !!! 😥
ድምጿ ራሱ ሲሰቀጥጥ 😠
#ወደ_ምሥራቅ_እንመልከት
✝️ ⛪️◈◈⛪️ ✝️
#ንነጽር_አዳም_ወሔዋን_ወንለቡ
«በአሕዛብስንኳ የማይገኝ ነው» [ 1ኛ ቆሮ. 5 ÷ 1 ] ያለው ቃሉን ስናስታውስ በርካታ ጉዳዮቻችን ወዴት እየሔዱ ነው እያስባሉን ነው ።
**_. በዚህ ዘመን የሚሠወር ክብርም ሆነ ነውር የለም ። ከነውር ይልቅ ክብርን መሠወር ቀላል ሆኗል ። ስለዚህ በዚህ ዘመን ያሉ አንዳንድ የደብር አስተዳዳሪዎችና ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎች በቅድስት ቤተክርስቲያን የሚፈጽሙት ጥፋት ከቀን ወደ ቀን እንደ ደም ብዛት እየጨመረ መጥቷል ። የነውርና የጥፋታቸው መበራከት ደግሞ ሌላውን ሰው ከሌላ በረት ለመሰብሰብና ለማምጣት ተስኗቸው የሚያዘገይ ብቻም ሳይሆን በቤቱ ያለንንም መንጋ የሚበትን ፣ የሚያሳድድ ፣ የሚያስኮበልል ፣ ተስፋ የሚያስቆርጡ ፣ ለሚሰሟቸው ደግሞ የሚያቅለሸልሹ ማሰናከያ ጉቶ ሆነዋል ። ቅድስት ቤተክርስቲያን እንድታተርፍ መክሊት የተቀበሉ አገልጋዮች አክሳሪ መክሊት ቀባሪ ነጋዴዎች በመኾናቸው እንድትከስስር እያደረጓት ነው ።
**➥. «ሴቶች» እጅግ ጥበበኞች ሃይማኖታቸው የጸና መጻሕፍትንም የተማሩ ምሥጢርንም ያደላደሉ ቢሆኑ "ያጠምቁና ወንጌልን ያስተምሩ ዘንድ ፈጽሞ አንፈቅድም በካህናት መካከልም ሆነው እንዲቅሙ አንፈቅድም ።
( ዲዲስቅልያ 14 )
** በቤተክርስቲያን ጸሎትአያስጀምሩ ። ለማሰናበት በጸሎት ዐያሳርጉ ። ( ፍት.መን. አንቀጽ 8 )
ይኽንን ነውር እያዩ እንዳላዩ እየሰሙ እንዳልሰሙ ዝም ማለት ራሱ ከነውርም ነውር ነው !!! 😥
ድምጿ ራሱ ሲሰቀጥጥ 😠
#ወደ_ምሥራቅ_እንመልከት
✝️ ⛪️◈◈⛪️ ✝️
#ንነጽር_አዳም_ወሔዋን_ወንለቡ
Forwarded from ክርስቲያናዊ ወንድ
ለሀዘን የሚያጋልጡህን ነገሮች
እየቆጠርክ ልብህን ከምታደክም
እግዚአብሔር የሰጠህን ፀጋዎቹን
የዋለልህን ብድራቱን እያሰብክ
ብትመሰግነው አንተም ደስተኛ እና አመስጋኝ ትሆናለህ
ሀዘንህም ከአንተ ይሸሻል ።
እየቆጠርክ ልብህን ከምታደክም
እግዚአብሔር የሰጠህን ፀጋዎቹን
የዋለልህን ብድራቱን እያሰብክ
ብትመሰግነው አንተም ደስተኛ እና አመስጋኝ ትሆናለህ
ሀዘንህም ከአንተ ይሸሻል ።
እስኪ በተዘጋው ቤታችን ጥቂት እንፃፍ ።
#እኛ_የክርስቶስ_ነን
ክርስትና ክርስቶሳዊነት ነው ። ከብሔር ከመንደር ከፍላጎት ከስሜት ... ከሌሎችም ስጋዊ ፍትወታት የፀዳ ።
ክርስቲያን ክርስቲያን የተባለው የሁሉ ሰራዒ እና መጋቢ በሆነው በክርስቶስ እንጂ በሌላ በማንም አይደለም ።
ክርስትና በክርስቶስ እራስነት የሚመራ የክርስቶስ የአካል ብልትነት ነው።
“ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።”— ኤፌሶን 5፥23
የክርስቶስ ቅዱሳን ህዋሳቱ እኛ ስንሆን ርሱ ደግሞ ራሳችን ነው ። እኛ ለእርሱ አካሉ ርሱ ለእኛ ደግሞ ራሳችን ነው ። ርሱ አንድ እንደሆነው ሁሉ እኛ በክርስቶስ አንድ ነን ። “እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን #በክርስቶስ_አንድ_አካል_ነን፥
እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን።”
— ሮሜ 12፥5
እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥27
የክርስቶስ ህዋሳቱ ከሆንን ዘንዳ ክርስቶስን እንምሰል ። ልክ ቅዱስ ፓውሎስ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።”— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥1 እንዳለ ።
ክርስቶስን መምሰል ግን
በቡድንተኝነት
በመጯጯህ
በስድብ
በመናናቅ .... ፈፅሞ አይሆንም ። እነዚህ የጌታ መንፈስ ካለባቸው ክርስቲያኖች ዘንድ ቦታ የላቸውምና ።
በመታረቅ
ይቅርም በመባባል
በቸርነት
በመደማመጥ
በትህትና ግን .... መቀደስ እንችላለን ።
እኛ በክርስቶስ አንድ ነንና ።
#እኛ_የክርስቶስ_ነን
ክርስትና ክርስቶሳዊነት ነው ። ከብሔር ከመንደር ከፍላጎት ከስሜት ... ከሌሎችም ስጋዊ ፍትወታት የፀዳ ።
ክርስቲያን ክርስቲያን የተባለው የሁሉ ሰራዒ እና መጋቢ በሆነው በክርስቶስ እንጂ በሌላ በማንም አይደለም ።
ክርስትና በክርስቶስ እራስነት የሚመራ የክርስቶስ የአካል ብልትነት ነው።
“ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።”— ኤፌሶን 5፥23
የክርስቶስ ቅዱሳን ህዋሳቱ እኛ ስንሆን ርሱ ደግሞ ራሳችን ነው ። እኛ ለእርሱ አካሉ ርሱ ለእኛ ደግሞ ራሳችን ነው ። ርሱ አንድ እንደሆነው ሁሉ እኛ በክርስቶስ አንድ ነን ። “እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን #በክርስቶስ_አንድ_አካል_ነን፥
እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን።”
— ሮሜ 12፥5
እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥27
የክርስቶስ ህዋሳቱ ከሆንን ዘንዳ ክርስቶስን እንምሰል ። ልክ ቅዱስ ፓውሎስ “እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።”— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥1 እንዳለ ።
ክርስቶስን መምሰል ግን
በቡድንተኝነት
በመጯጯህ
በስድብ
በመናናቅ .... ፈፅሞ አይሆንም ። እነዚህ የጌታ መንፈስ ካለባቸው ክርስቲያኖች ዘንድ ቦታ የላቸውምና ።
በመታረቅ
ይቅርም በመባባል
በቸርነት
በመደማመጥ
በትህትና ግን .... መቀደስ እንችላለን ።
እኛ በክርስቶስ አንድ ነንና ።