"የብርሃናት ንጉሥ ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመውለድ ዛሬ የብርሃን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም በእውነት ተወለደች። ከሊባኖስ ተራሮች ርግብ ጸዐዳ ተወለደች፤ በሔዋን ምክንያት የተዘጋው የሕይወት መንገድ ይከፈትልን ዘንድ የሕይወት እናት ዛሬ ተወለደች፡፡ የዓለም ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመብርሃን ዛሬ ተወለደች፡፡
ኢያቄምና ሐና ዳግሚት ሰማይ ተብላ የተጠራችውን ድንግልን ወለዱ፤ እውነተኛው ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመ ፀሐይ (የፀሐይ እናት) ቅድስት ድንግል ዛሬ ተወለደች፤ ብርሃንን ለማስገኘት መወለድ መታደል ነው፤ ከሰው ልጆችም መካከል መመረጥ ዕፁብ ድንቅ ነው፤ የመድኃኔዓለም እናት ለመሆን መወለድ ሰማያዊ ፀጋ ነው።
በእውነት እመብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር ስጦታ ናት። ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን እመብርሃን ዛሬ ተወልዳልናለችና ደስ ይበለን እልልም እንበል።"
የአለሙን ሁሉ መድኃኒት ለወለደች ለብርሃናት ጌታ እናት በቀራንዮ በመስቀሉ ስር እናት ትሆነን ዘንድ ለተሠጠችን ለመመኪያችን ዘውድ ለተወዳጇ ለቅድስተ ቅዱሳን እናታችን ልደት በዓል እንኳን አደረሰን
(Orthodox and Bible fb page)
ኢያቄምና ሐና ዳግሚት ሰማይ ተብላ የተጠራችውን ድንግልን ወለዱ፤ እውነተኛው ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመ ፀሐይ (የፀሐይ እናት) ቅድስት ድንግል ዛሬ ተወለደች፤ ብርሃንን ለማስገኘት መወለድ መታደል ነው፤ ከሰው ልጆችም መካከል መመረጥ ዕፁብ ድንቅ ነው፤ የመድኃኔዓለም እናት ለመሆን መወለድ ሰማያዊ ፀጋ ነው።
በእውነት እመብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር ስጦታ ናት። ንጽሕተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን እመብርሃን ዛሬ ተወልዳልናለችና ደስ ይበለን እልልም እንበል።"
የአለሙን ሁሉ መድኃኒት ለወለደች ለብርሃናት ጌታ እናት በቀራንዮ በመስቀሉ ስር እናት ትሆነን ዘንድ ለተሠጠችን ለመመኪያችን ዘውድ ለተወዳጇ ለቅድስተ ቅዱሳን እናታችን ልደት በዓል እንኳን አደረሰን
(Orthodox and Bible fb page)
#የግንቦት_ልደታ_በዓል_አከባበር
በቤተ ክርስቲያናችን ትዉፊት መሰረት ሃና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትውፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡
ሆኖም በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸው መንፈሳዊያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ፣ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡ እኛም ከእንደነዚህ ዓይነት አሰናካዮች በመለየት ይኼንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር እንድናከብረዉ እና ራሳችንን መልዕክቴ ነው፡፡
ለዚህም የእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን፡፡
በቤተ ክርስቲያናችን ትዉፊት መሰረት ሃና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደዉ በአድባረ ሊባኖስ ስር እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸዉ ‹‹ንፍሮና ጥራጥሬ›› ነበር፡፡ ይኼንን ትውፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ዉጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡
ሆኖም በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማዉን ማስፈጸም የሚፈልገዉ ዲያቢሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸው መንፈሳዊያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነዉ፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለዉጋር ነዉ፣ ቆሌዉን ለመለመን ነዉ፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ ቡና የሚረጩ፣ ቂቤ የሚቀቡ፣ የከብት ደም የሚያፈሱ፣ እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸዉ፡፡ እኛም ከእንደነዚህ ዓይነት አሰናካዮች በመለየት ይኼንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር እንድናከብረዉ እና ራሳችንን መልዕክቴ ነው፡፡
ለዚህም የእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን፡፡
👉=>ውበትን ደስታ አታድርጉት
የረገፈና የቆሰለ ዕለት ታዝናላችኹ!
👉=>ሐብታችኹን ደስታ አታድርጉት
ሲቀሟችኹ ታዝናላችኹ!
👉=>ዘመድን የደስታ ምንጭ አታድርጉት
ሲታመም ሲሞት ትጎዳላችኹ!
👉=>ባልንጀራን የደስታ ምንጭ አታድርጉት
ሲለያችኹ ሲከዳችኹ ታዝናላችኹ!
👉=>ጉልበታችኹን የደስታ ምንጭ አታድርጉት
ስትታመሙ ስትደክሙ ኹሉም ይቀራል!
✝የደስታ ምንጭ ክርስቶስ ነው።✝
✝ደስታም ክርስቶስ ነው✝
ከየኔታ ስብከት የተወሰደ
የረገፈና የቆሰለ ዕለት ታዝናላችኹ!
👉=>ሐብታችኹን ደስታ አታድርጉት
ሲቀሟችኹ ታዝናላችኹ!
👉=>ዘመድን የደስታ ምንጭ አታድርጉት
ሲታመም ሲሞት ትጎዳላችኹ!
👉=>ባልንጀራን የደስታ ምንጭ አታድርጉት
ሲለያችኹ ሲከዳችኹ ታዝናላችኹ!
👉=>ጉልበታችኹን የደስታ ምንጭ አታድርጉት
ስትታመሙ ስትደክሙ ኹሉም ይቀራል!
✝የደስታ ምንጭ ክርስቶስ ነው።✝
✝ደስታም ክርስቶስ ነው✝
ከየኔታ ስብከት የተወሰደ
+ የተሠጠህን ቁጠር +
ሔዋን ከዕባብ ጋር እየተነጋገረች ነው። የመጀመሪያ ጥፋትዋ ካለደረጃዋ ወርዳ ከዕባብ ጋር ወዳጅነት መጀመርዋ ሳይሆን አይቀርም። ዕባብ ደግሞ የስይጣን አንደበት ነበረ።
ሰይጣን እንዲህ አላት:- በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት። ልብ አድርጉ እግዚአብሔር "ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ" አላለም። የከለከለው አንዲት ዛፍ ነው:: ሰይጣን ግን ሁሉን ተከልክላችሁዋል? ብሎ እንዳላዋቂ ጠየቀ። ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ንግግሩን የከፈተው በውሸት ነበረ።
ዓላማው ከሔዋን መረጃ ለማግኘት አልነበረም። ሔዋን እስከዛሬ ያላሰበችውን ማሳሰብ ነበር። ብሉ ተብሎ ከተሠጣቸው ብዙ ሺህ ዛፍ ይልቅ የተከለከሉትን አንዲት ዛፍ አሳይቷት ሔደ። ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ስላልተሠጣት ማሰብ ጀምራ ደስታዋን አጣች። የተከለከለችውን በልታ የተሠጣትን ብዙ ሥጦታ ከነሠጪው አጣች።
ወዳጄ የቀደመው እባብ ዛሬም መርዙን ይረጫል
በሕይወታችን ከተሠጠን ብዙ ነገር ይልቅ ያልተሠጠንን ጥቂት ነገር እናስባለን። ገንዘብ እንደሌለህ እያሰብክ ጤና እንዳለህ ትረሳለህ። ጫማ እንደሌለህ እያሰብክ እግር እንዳለህ ትረሳለህ። አልጋ እንደሌለህ እያሰብክ እንቅልፍ እንዳለህ ትረሳለህ። ስለዚህ ውስጥህ ያለውን የዕባቡን ድምፅ አትስማ ከሌለህ ይልቅ ያለህ ይበልጣልና የተሠጠህን ቁጠር።
(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)
ሔዋን ከዕባብ ጋር እየተነጋገረች ነው። የመጀመሪያ ጥፋትዋ ካለደረጃዋ ወርዳ ከዕባብ ጋር ወዳጅነት መጀመርዋ ሳይሆን አይቀርም። ዕባብ ደግሞ የስይጣን አንደበት ነበረ።
ሰይጣን እንዲህ አላት:- በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት። ልብ አድርጉ እግዚአብሔር "ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ" አላለም። የከለከለው አንዲት ዛፍ ነው:: ሰይጣን ግን ሁሉን ተከልክላችሁዋል? ብሎ እንዳላዋቂ ጠየቀ። ሰይጣን በመጽሐፍ ቅዱስ ንግግሩን የከፈተው በውሸት ነበረ።
ዓላማው ከሔዋን መረጃ ለማግኘት አልነበረም። ሔዋን እስከዛሬ ያላሰበችውን ማሳሰብ ነበር። ብሉ ተብሎ ከተሠጣቸው ብዙ ሺህ ዛፍ ይልቅ የተከለከሉትን አንዲት ዛፍ አሳይቷት ሔደ። ከዚያች ደቂቃ ጀምሮ ስላልተሠጣት ማሰብ ጀምራ ደስታዋን አጣች። የተከለከለችውን በልታ የተሠጣትን ብዙ ሥጦታ ከነሠጪው አጣች።
ወዳጄ የቀደመው እባብ ዛሬም መርዙን ይረጫል
በሕይወታችን ከተሠጠን ብዙ ነገር ይልቅ ያልተሠጠንን ጥቂት ነገር እናስባለን። ገንዘብ እንደሌለህ እያሰብክ ጤና እንዳለህ ትረሳለህ። ጫማ እንደሌለህ እያሰብክ እግር እንዳለህ ትረሳለህ። አልጋ እንደሌለህ እያሰብክ እንቅልፍ እንዳለህ ትረሳለህ። ስለዚህ ውስጥህ ያለውን የዕባቡን ድምፅ አትስማ ከሌለህ ይልቅ ያለህ ይበልጣልና የተሠጠህን ቁጠር።
(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)
"አንተ ገሊላዊ አሸንፈሃል"
ቄሣር ዮልያኖስ (361 -- 363 ዓ.ም)
ቄሣር ዮልያኖስ በሮም ዘመነ መንግስቱን ላይ ተደላድሎ የነበረ ቄሣር ነው ። በስልጣን ላይ በተቀመጠባቸው ሁለት ዓመታት ውስጥ ክርስቲያኖችን ከሌሎቹ አረማውያን ቄሳሮች ለየት ባለመልኩ መከራን አድርሶባቸው ነበር ። ግን አሸንፋቸዋለሁ ብሎ በግፍ ደማቸው ሲያፈስ፣በዋሉበት ማሳደሪያ ባደሩበትም መዋያ አሳጥቶ የነበረው ይሄ ግፈኛ ዓረማዊ ቄሳር በመቅሰፍተ እግዚአብሔር ተቀጥቶ ነፍሱ ከስጋው ልትለይ ባለችበት ሰዓት የተናገረው ንግግር ይሄ ነበር ""አንተ ገሊላዊ አሸንፈሃል"" ።
ገሊላዊ ብሎ የጠራው በስጋ ተገልጦ የድህነታችን ቤዛ የሆነው ቅዱሱ አምላካችን "ክርስቶስ ኢየሱስ" ነው ። ዮልያኖስ ትክክል ነው ። ገሊለዊ የናዝሬቱ ክርስቶስ ኢየሱስ ሳይታገል ያሸንፋል ። ስይደክም ይረታል ። ሳይወርድ ይሰብራል ። ሳይወጣ ያደቃል ።
አዎ " ገሊላዊው ያሸንፋል " ክብር ምስጋና አምልኮት እና ውዳሴ ከምድር እስከ አርያም ከፀሐይ መውጫ እስከመግቢያው ድረስ ለቅዱስ ስሙ ይሁን ።
🤲 አሜን🤲
@alatyon15
ቄሣር ዮልያኖስ (361 -- 363 ዓ.ም)
ቄሣር ዮልያኖስ በሮም ዘመነ መንግስቱን ላይ ተደላድሎ የነበረ ቄሣር ነው ። በስልጣን ላይ በተቀመጠባቸው ሁለት ዓመታት ውስጥ ክርስቲያኖችን ከሌሎቹ አረማውያን ቄሳሮች ለየት ባለመልኩ መከራን አድርሶባቸው ነበር ። ግን አሸንፋቸዋለሁ ብሎ በግፍ ደማቸው ሲያፈስ፣በዋሉበት ማሳደሪያ ባደሩበትም መዋያ አሳጥቶ የነበረው ይሄ ግፈኛ ዓረማዊ ቄሳር በመቅሰፍተ እግዚአብሔር ተቀጥቶ ነፍሱ ከስጋው ልትለይ ባለችበት ሰዓት የተናገረው ንግግር ይሄ ነበር ""አንተ ገሊላዊ አሸንፈሃል"" ።
ገሊላዊ ብሎ የጠራው በስጋ ተገልጦ የድህነታችን ቤዛ የሆነው ቅዱሱ አምላካችን "ክርስቶስ ኢየሱስ" ነው ። ዮልያኖስ ትክክል ነው ። ገሊለዊ የናዝሬቱ ክርስቶስ ኢየሱስ ሳይታገል ያሸንፋል ። ስይደክም ይረታል ። ሳይወርድ ይሰብራል ። ሳይወጣ ያደቃል ።
አዎ " ገሊላዊው ያሸንፋል " ክብር ምስጋና አምልኮት እና ውዳሴ ከምድር እስከ አርያም ከፀሐይ መውጫ እስከመግቢያው ድረስ ለቅዱስ ስሙ ይሁን ።
🤲 አሜን🤲
@alatyon15
ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ በዳሰነች ወረዳ ከ1200 በላይ አዳዲስ አማንያን አጠመቁ
__
ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 1200 በላይ አዳዲስ አመንያንን ዛሬ ሐምሌ 06 ቀን 2016 ዓ.ም በዳሰነች ወረዳ አጥምቀው ወደ እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አምጥተዋል። ተጠማቂዎቹ በሀገረ ስብከቱ፣ በወረዳ ቤተክህነቱ፣ በማኅበረ ቅዱሳን ትብብር በአካባቢው በተሰማሩ የቋንቋ ሰባክያን ጥረት ለጥምቀት የሚያበቃቸውን መሠረታዊ የነገረ ሃይማኖት ትምህርት ሲማሩ ቆይተው በዛሬው ዕለት ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅነት ተቀላቅለዋል።
ብፁዕነታቸው ለአካባቢው አዳዲስ አማኞች የሚገለገሉበት አዲስ ቤተክርስቲያን ለመገንባት ትናንት ሐምሌ 06 ቀን 2016 ዓ.ም በዳሰነች ወረዳ የመርመርቴ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
ከዚህ በፊት በሀገረ ስብከቱ ከ185,000 በላይ አዳዲስ አማንያን መጠመቃቸው የሚታወስ ነው።
__
ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ 1200 በላይ አዳዲስ አመንያንን ዛሬ ሐምሌ 06 ቀን 2016 ዓ.ም በዳሰነች ወረዳ አጥምቀው ወደ እናት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አምጥተዋል። ተጠማቂዎቹ በሀገረ ስብከቱ፣ በወረዳ ቤተክህነቱ፣ በማኅበረ ቅዱሳን ትብብር በአካባቢው በተሰማሩ የቋንቋ ሰባክያን ጥረት ለጥምቀት የሚያበቃቸውን መሠረታዊ የነገረ ሃይማኖት ትምህርት ሲማሩ ቆይተው በዛሬው ዕለት ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅነት ተቀላቅለዋል።
ብፁዕነታቸው ለአካባቢው አዳዲስ አማኞች የሚገለገሉበት አዲስ ቤተክርስቲያን ለመገንባት ትናንት ሐምሌ 06 ቀን 2016 ዓ.ም በዳሰነች ወረዳ የመርመርቴ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የመሠረት ድንጋይ አስቀምጠዋል።
ከዚህ በፊት በሀገረ ስብከቱ ከ185,000 በላይ አዳዲስ አማንያን መጠመቃቸው የሚታወስ ነው።
That which was from the beginning, which we have heard, which we have seen with our eyes, which we have looked upon, and our hands have handled, concerning the Word of life-- - 1 John 1:1
Read the testimony of John: "That which we have seen, which we have heard, which we have looked upon with our eyes, and our hands have handled, of the Word of life."
But the very same apostles testify that they had both seen and "handled "Christ.
"That "says John, "which we have seen with our eyes, which we have looked upon, and our hands have handled, of the Word of life."
But what is that which, in a certain way, has been grasped by hand.
To God their beauty, to God their youth (is dedicated). With Him they live; with Him they converse; Him they "handle"
- Tertullian of Carthage
Read the testimony of John: "That which we have seen, which we have heard, which we have looked upon with our eyes, and our hands have handled, of the Word of life."
But the very same apostles testify that they had both seen and "handled "Christ.
"That "says John, "which we have seen with our eyes, which we have looked upon, and our hands have handled, of the Word of life."
But what is that which, in a certain way, has been grasped by hand.
To God their beauty, to God their youth (is dedicated). With Him they live; with Him they converse; Him they "handle"
- Tertullian of Carthage
“ዘወትር በዐይንህ ፊት ፈሪሃ እግዚአብሔር ይኑር፤ ሕይወትና ሞት የሚሰጠውን አዘክረው፡፡ ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ ጥላው፤ ከሥጋ የሚመጣውን ደስታና ሰላም አትሻ፤ ለዚህኛው ኑሮ ሙትና ለእግዚአብሔር ሕያው ሁን፤ ለእግዚአብሔር ቃል የገባኸውን አትርሳ፤ ያም በፍርድ ቀን ካንተ ይፈለግብሃል፡፡ ረኀብን በጸጋ ተቀበለው፤ ተጠማ፥ ተራቆት፥ ንቁና በሐዘን የምትኖር ሁን፡፡ በልቡናህ አልቅስና ጩኽ፤ ለእግዚአብሔር የምትመች መሆን አለመሆንህን ፈትን፤ ሥጋህን ቀጥተህ ነፍስህን ታድናት ዘንድ፡፡”
(አባ እንጦንስ)
(አባ እንጦንስ)