Telegram Web Link
"ብርሃን ወደ አንድ ቤት ውስጥ ሲገባ ጨለማን እንደሚያስወግድ ሁሉ፤ እግዚአብሔርን መፍራት ወደ አንድ ሰው ልብ ሲገባም አለማወቅን (በኃጢአት የሚወድቅባትን) ያስወግዳል።"

#አባ_እንጦንስ
እጅግ የተወደደና የተከበረው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ አለ

“ወዳጄ ሆይ ወንድምህ ከአንተ ይልቅ አስተዋይና አዋቂ ብርቱም ቢሆን በዚህ ቅር አይበልህ ከዚህ ይልቅ እግዚአብሔርን አመስግን

ከወንድምህ አስተዋይነትና ብርታት ትጠቀማለህና በዚህ ሳታቆም ራስህን ስጦታየ ምንድነው?ወንድሜን እህቴን በምን ልጥቀም ?ብለህ ጠይቅ

ይህን ጥያቄ በትክክል ስትመልስ እንደመለስከው ምላሽም ስትተገብር በአንድ መልኩ በሚበልጥህ ሰው ቅር መሰኘትህን በሌላ መልኩ ደግሞ የምትበልጠውን ወንድምህን መናቅህን ታቆማለህ”
🌼እንኳን በሰላም መጣችሁ እህት ወንድሞችን 🌼
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዙሪያ ላላችሁ ጥያቄ መልስ የምታገኙበት እናንተም የምትጠየቁበት ማህበር ነው ።
👉በተጨማሪም ተከታታይ ትምህርቶች
👉ውይይቶች ይኖራሉ
በሚደረጉ ሐይማኖታዊ ውይይቶች ላይ
👉አንዱ የሌላውን እምነት ማናናቅ
👉የሌሎችን ፅሁፍ ቀድቶ መገልበጥ
👉...በጥብቅ የከለከለ ነው ።
🍀መልካም የውይይት ጊዜ🍀
Forwarded from ልባም ሴት 😍 (አላትዮን)
አንቺ ፀሐይ ሆይ የዛሬው ፈተና ልክ እንደደመና ተናፋቂ እንዲያደርግሽ እንጂ ፈፅማ የሚትጠፋ እንደማያደርግሽ አውቀሽ በተስፋ ኑሪ ።
አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ!

አንድን የሥጋ ቁስል ለመፈወስ ለእያንዳንዱ ሰው ከባድ ነው፤ የነፍስን ቁስል መፈወስ ግን ለኹሉም ቀላል ነው፡፡ የሥጋ ቁስል ለመፈወስ መድኃኒት ብሎም ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነፍስን ለመፈወስ ግን ቀላል ብሎም ወጪን የማይጠይቅ ነው፡፡ ሥጋን ከዚያ ከሚያሰቃይ ቁስሉ ለመፈወስ አድካሚ ነው፡፡ ምክንያቱም በቀዶ ጥገና ምላጭ መቀደድ አለበት፤ መራራ መድኃኒቶችም ሊጨመሩበት ይገባል፡፡ ነፍስን ለመፈወስ ግን እንዲህ ዓይነት ነገር አያስፈልግም፡፡ ፈቃደኛ መኾን ብቻ በቂ ነው፤ ፍላጎቱ ካለ ኹሉንም ነገር ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ የእግዚአብሔር መግቦቱም እስከ አሁን ድረስ ይህ ነው፡፡ ሥጋ ቢቆስል ያን ያህል ከባድ ጉዳትን አያመጣብንም፤ ምክንያቱም ምንም ባንታመምም እንኳን ሞት መጥቶ ይህን ሥጋችን ያፈርሰዋል፤ ያበሰብሰዋልምና፡፡ ነፍሳችን ብትታመም ግን ጉዳቱ ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሔር የነፍስን ሕመም ለመፈወስ መድኃኒቱ ቀላል፣ ምንም ወጪና ስቃይ የሌለበት ያደረገውም ስለዚሁ ነው፡፡ ታዲያ ምንም እንኳን በሕመሙ ምክንያት የሚያገኘን ጉዳት ያን ያህል ብዙ ባይኾንም የገንዘብ ወጪን የሚጠይቀው፣ ሐኪም የሚያስፈልገው፣ ብዙ ስቃይ ያለበት ሥጋችን ሲታመም እርሱን ለማከም እጅግ የምንደክም ኾነን ሳለ፥ እጅግ ብዙ ጉዳት የሚያመጣውን፣ እርሱን ለመፈወስ ወጪ የማይጠይቀውን፣ ለማስታመም ሌሎች ሰዎች የማያስቸግረውን፣ እንደ ምላጩና እንደ መራራ መድኃኒቱ ስቃይ የሌለበትን ይልቁንም ከእነዚህ አንዱስ እንኳን ሳይፈልግ በእኛ ኃይል ባሉ ምርጫና ፈቃድ ብቻ መዳን የሚችለውን፣ ይህን ማድረግ ሳንችል ስንቀርም ከባድ ፍርድና ቅጣት ስቃይም እንደሚያገኘን በእርግጥ እያወቅን የነፍሳችንን ቁስል ችላ የምንል ከኾነ ሊደረግልን የሚችል ምሕረት እንደ ምን ያለ ምሕረት ነው? እኮ የምናገኘው ይቅርታ እንደ ምን ያለ ይቅርታ ነው?

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ትምህርት በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ #በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ የተተረጎመ
ሰው ሁን!
1ኛ ነገ. ፪፥፫
አበባ አቤ
ከአባቶች አንዱ እንዲህ አለ
"አንበሳ ኃያልና አስፈሪ ነው ። መነኩሴው ተጋድሎውን ቢተው ፍላጎቱንም ቢከተል ግርማው ይጠፋል መዘባበቻም ይሆናል ። "

መፅሐፈ ገነት ገፅ 9
በዝቋላ ደብረ ከዋክብ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም መነኮሳት አባቶች ላይ የተፈጸመውን የግፍ ግድያ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አውግዟል !

የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶች የግፍ ግድያውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። መንግሥት ለቤተክርስቲያኗ እና ለዜጎች አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርግ የጉባኤው የበላይ ጠባቂ አባቶች ጠይቀዋል።

መንግሥት በቤተክርስቲያኒቱ አባቶች ላይ የተፈጸመውን የግፍ ግድያ እንዲያጣራ እና የወንጀል ተግባሩን የፈጸሙትን ለሕግ እንዲያቀርብ እና የሕግ የበላይነትን እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል።

መንግሥት እየተፈጸሙ ያሉ እገታና የደኅንነት ሥጋቶችን በማስወገድ የዜጎችን የመንቀሳቀስ ሕገ መንግሥታዊ መብት የማስጠበቅ መንግሥታዊ እና ሕጋዊ ኀላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
Forwarded from ጰላድዮስ (🤔)
ሰቆቃወ ድንግል
እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች ናቸው፥ ሰባትንም ነፍሱ አጥብቃ ትጸየፈዋለች
     ➛ ትዕቢተኛ ዓይን፥
     ➛ ሐሰተኛ ምላስ፥
     ➛ ንጹሕን ደም የምታፈስስ እጅ፥
     ➛ ክፉ አሳብን የሚያበቅል ልብ፥
     ➛ ወደ ክፉ የምትሮጥ እግር፥
     ➛ በሐሰት የሚናገር ሐሰተኛ ምስክር
     ➛ በወንድማማች መካከልም ጠብን የሚዘራ።

ምሳሌ 6፥16-19
2024/09/28 19:32:34
Back to Top
HTML Embed Code: