Telegram Web Link
👍ቅዱሳን ስዕላት ጌጥ አይደሉ

አዎ ስዕላት የአምልኮ ንዋያት እንጂ መዋቢያ ወይም ደግሞ ቦታ ማሟያ አይደሉም ።
በየመኪና የሚለጣጠፋ ቅዱሳን ስዕላት እንዲቀሩ መንግስት የተንኮል አዋጅ ቢያውጅም። የእግዚአብሔር ሐሳብም እንዳለበት ማስተዋል ችያለሁ ። በየህዝብ መጓጓዣዎች የተለጠፋ ቅዱሳት ስዕላት የተሳፋሪዎች ፣የረዳቱን እንዲሁም የዘዋሪ ሹፊሮችን ስድድብ እና ክፋታዊ ተግባር እንጂ ለስዕላቱ ላይ ለሚገለጥ የእግዚአብሔር ፀጋ ምስጋናን አልጠገቡም ።

ቀያፋ በጊዜ ትንቢት ሳያውቅ የክርስቶስን የማዳን ስራ እንደተናገረው ሁሉ ባለ ስልጣናቱን ለበጎ ያላይደለ ለክፋ የወሰኑት ውሳኔ በድፍረታችን ይሁን ባለማወቅ በየቦታው በማይመጥናቸው ሁኔታ የሰቀልናቸውን ስዕላት ማስከበሩ ደስ ያሰኛል ።
Forwarded from ልባም ሴት 😍
🦋 ለእህቴ . . .🦋

🥛እርጎ ውስጥ እደገባችዋ ዝንብ ህይወትሽ በጠ
ጪው እጅ አይወሰን 🙅‍♂


አንቺ ሴት ነሽ👸 የእናትሽ ልጅ 🤱 ሴት !!

👉አንቺ ውብ ነሽ ምክንያቱም ሴት ነሽ
👉አንቺ ብልህ ነሽ ምክንያቱም ሴትነሽ
👉አንቺ  ሴት ነሽ ያውም ጀግና ሴት

🌹 ምንም ማረግ ትችያለሽ ዓለም 🌍 ያላንቺ ጨረቃ 🌘 ያኮረፈቻት ፀሃይ 🌥 የተቀየመቻት ጨለማ 🖤 ናት

🌹ሁሉም ቀን ቀንሽ ነው 🌹

🎙የአብስራ ተስፋዬ 📩 @yeabm
መንግስት ለዚህም የሚሆን አዋጅ አምጣ 😡
የ9ኙ መነኮሳት ምርጫ ተጠናቋል

ቅዱስ ሲኖዶስ የዘጠኝ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫን አካሔደ

* ሲመታቸው ሐምሌ 9 ይከናወናል፤
* ከነገ ሰኔ 29/2015 ዓ.ም ጀምሮ ሥልጠና ይገባሉ፤

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ፣ ዛሬ ረቡዕ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በአካሔደው ልዩ ስብሰባ፣ በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልሎች፣ በተደራቢነት ተይዘው ለቆዩ፣ ክፍት በኾኑና አንገብጋቢ ችግር ባለባቸው ዘጠኝ አህጉረ ስብከት ላይ የሚመደቡ ዘጠኝ ኤጲስ ቆጰሳትን ምርጫ አካሒዷል፡፡

በዚኽም መሠረት፡-
ለኦሮሚያ ክልል ሰባት አህጉረ ስብከት፤
1. አባ ሣህለ ማርያም ቶላ - ምዕራብ አርሲ - ሻሸመኔ ሀገረ ስብከት
2. አባ ወልደ ገብርኤል አበበ - ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት
3. አባ ጥላሁን ወርቁ - ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
4. አባ ዓምደ ሚካኤል ኀይሌ - ሆሮ ጉድሩ ወለጋ - ሻምቡ ሀገረ ስብከት
5. አባ ኀይለ ማርያም ጌታቸው - ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት
6. አባ ተክለ ሃይማኖት ገብሬ - ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት
7. አባ እስጢፋኖስ ገብሬ - ቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት

ለደቡብ ኢትዮጵያ ኹለት አህጉረ ስብከት፤
8. አባ ክፍለ ገብርኤል ተክለ ሐዋርያት - ጌድኦ አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት
9. አባ ስብሐት ለአብ ወልደ ማርያም - ዳውሮ እና ኮንታ ሀገረ ስብከት
በቅዱስ ሲኖዶስ የጸደቀው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ውጤት ይፋ ተደረገ

ምንጭ: EOTC TV
"…እንዴ፣ እንዴ ኧረ በማርያም በአዛኝቷ፣ ደጀኔ ቶላም (ደጁም) ጳጳስ ሊሆን ነው ማለት ነው…? አዛኜን በፍፁም ይሄማ አይሆንም። ነውር ነው። 😂😂። ወይ 3ሚልዮን ብር… ? አባ ሳዊሮስና አባ ሩፋኤል ፈጣሪ ብድራቱን ይክፈላችሁ።

• እንግዲህ ሊጀምረኝ ነው።፣
"…የአይጥ ምስክሯ…😂😂

"…ኦቦ ተስፋዬ ይሄ አምቡላ መጋፊያ አረቄ ቤት አይደለም። እንከባበር። ይሄ የጋራ ሃይማኖታችን የከበረ የቅድስና ሥነ ሥርዓት የሚፈጸምበት ሃይማኖታዊ ጉዳይ ነው። ተጣድፎ ምስክርነትህን እዚያው በጃምቦ ቤት አድርገው። ምዕራብ አሩሲ አለፈላት ይላል እንዴ ደግሞ እንዲያውም ጉድ ፈላባት በል እንጂ አባው።

"…በዚህ የማይረባ የጎጥ ኔትወርክ ውስጥ ያላችሁ በሙሉ በሙሉ ከሀ እስከ ፐ የቅርብ ሰዎቼንም ሆነ የሩቅ ወዳጆቼን በሙሉ በአስቸኳይ አቁሙ። እኔ ዘመዴ አልፋታችሁም። ሸዋን በዚህ መልክ አትጠቅሙትም። ሸዋም በዚህ መልክ አይከብርም። ሌሎች ሰዎች ጠፍተው ነው…?

"…ምንአልባትም የማከብርዎት አረጋዊው ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስም በዚህ ጉዳይ ቢተዉ ነው የሚሻለው። ኧረ ደስ አይልም በማርያም። ገና ለገና… ብቻ ደስ አይልም። በቃ መጠጡ ነው ችግሩ እሱን እንዲተው እንመክረዋልን ይለኛል እንዴ በማርያም። አዛረ ምን ጉድ ነው።

"…ደጀኔ ቶላም በማኅበራዊ ሚድያው ላይ የማኅበረ ቅዱሳን አንዳንድ የሸዋ ጎጠኞች፣ እንደ ተስፋዬ ሞሲሳ ዓይነት የአምቡላ ጋን ስር ሰባኪዎች በየፌስቡኩ ስለመሰከሩ፣ ስለተጯጯሁልህ እንዳትኮፈስ። አይገባኝም አይሆንም በል። ይሄን ስታይ ቢያንስ የቀሲስ አብርሃምስ እህት ምን ትላለች አይባልም እንዴ…?  ቀሲስ በላይ መኮንንም እኮ የ3 ልጆች አባት ነው። እንዲያ ከሆነ እሱስ የማይሾም ለምንድነው…?

• አባ ሩፋኤል
• አባ ሕርያቆስ
• አባ ሳዊሮስ
• እና ሌሎችም በዚህ ጉዳይ ላይ ወጥራችሁ ከሸዋ ጳጳስ መብዛት አለበት ብላችሁ የተሳተፋችሁ በሙሉ በየሄዳችሁበት አንገታችሁን ከመድፋታችሁ በፊት በቶሎ ነገርየውን አስተካክሉ። ሌሎቹም ላይ እንዲሁ እቀጥላለሁ።

• ወይ ምስክርነት መች በፍሬንድስነት ሆነና…? ሃኣ…!
where were you hajieee 😂
ሐኪማችን የሚደክም፤ የሚሰላችም አይደለም፡፡ እልፍ ጊዜ ብንቆስል ያድነናል፤ ስለዚህ ጥበብ በማጣት በአካላችን ላይ ትንሽ ብንቆስልም ሐኪማችን ሁል ጊዜ ሊያድነን ይተጋል፡፡ እርሱ በኤርምያስ እጅ ለተነሳሕያን በተላከ ደብዳቤ ላይ በነቢዩ አፍ ድምጹን ከፍ አድርጎ ‹‹አሁንም መንገዳችሁንና ሥራችሁን አሳምሩ፤ የአምላካችሁንም የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፧ እግዚአብሔርም የተናገረባችሁን ክፉ ነገር ይተዋል›› ይለናል (ኤር ፳፮፥፲፫)፡፡ ስለዚህ ነቢዩ በመሓላ ቃል ‹‹በኃጢአተኛው ሞት አልደሰትም›› ይላል፡፡

ለአዳም ልጆች ሁሉ ተስፋ ቃል ኪዳን እንደ ገባላቸው ወደ በሩ መጥተው ለሚያንኳኩ ሁሉ የእግዚአብሔር በር ሁል ጊዜ እንደ ተከፈተ ነው፡፡ የቸርነቱ ፍቅር በንስሓ ለሚመላለሱት ይደሰታል፤ ስለዚህ እጆቹን ዘርግቶ ይቀበላቸዋል፡፡

ክብሩ ተነሳሕያንን ይረዳቸዋል፤ በእቅፉ ውስጥ መሆን ይቅርታን ያስገኛል፡፡ እርሱ በወንጌል ‹‹ንስሓ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኙ ጻድቃን ይልቅ ንስሓ ስለሚገባ ስለ አንድ ኃጢአተኛ በሰማያት ፍጹም ደስታ ይሆናል›› አለ (ሉቃ ፲፭፥፯)፡

በሰማያት ያሉ መላእክትን ደስ ይላቸዋል፣ የቅዱሳን ማኅበርም ሐሴት ያደርጋሉ፡፡ ጠባቂ መላእክትም ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ሆሣዕና እያሉ ይዘምራሉ፤ ሊቃነ መላእክትም በኅብረት ድምጻቸውን አሰምተው ይዘምራሉ፡፡

በአስፈሪ ግርማ ሞገስ የገነትን በር የሚጠብቅ ኪሩቤል እናንተ ተነሳሕያን እንኳን ደኅና መጣችሁ ብሎ ይቀበላችኋል፤ እናንተ አዲሶቹ የገነት ወራሾች ናችሁ ብሎ ደመ ማኅተሙን ከመስቀል ይዞ እንደ ሔደ ቀማኛ የምታጓጓዋን የገነት በር ይከፍትላችኋል።

ከሕይወት ዛፍም ትበላላችሁ ትጠግባላችሁም፡፡ የገነት ዛፍ ሕያው ፍሬውን ይሰጣችኋል፡፡ የኤደን አትክልትም ዙርያችሁን ይሞላል፡፡ የበለጸጉ ዛፎችም ይከባችኋል፡፡ በዚያ ከቅዱሳን ጋር ተሰምቶ የማያውቅ ምስጋናን ለአምላካችሁ ታቀርባላችሁ። በዚያ ቅዱሳኖቹ ይጠብቋችኋል፤ ባሸበረቀው አዳራሽ ውስጥ ታላቅ ደስታ በዚያ ይጠብቋችኋል፡፡ እናንተም የዚህ ታላቅ በዓል ታዳሚዎች ትሆናላችሁ፡፡

በዚያ በብርሃን በተሞላ ግዛት ውስጥ ብዙ ቅዱሳን አሉ፤ እናንተም ለቅዱሳን የሚሰጥ አክሊል ተዘጋጅቶላችሁ እየጠበቃችሁ ነውና። እንግዲህ ጠቢባን ሁኑ፤ ከንስሓ ወደ ኋላ በመመለስ ከዚህ ክብር አትራቁ፡፡

እናንተ በንስሓ ውስጥ ያላችሁ ሰዎች ሆይ እንግዲህ ሙሽራው እስኪመጣ ድረስ መጠበቅ፣ መዘግየትም የለባችሁም፡፡ ይልቁን ለሰርግ የሚገባውን ልብስ፤ የክብር ካባ ለብሳችሁ ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ እንጂ፡፡ ወደ ሰርጉ ለመግባት የሙሽራውን ነጭ ልብስ ውሰዱ፡፡ የሙሽራው መምጫ ሳይደርስ የመብራቱን ዘይት አዘጋጁ፡፡ የመለከቱ ድምፅ ሳይሰማ በፊት በእጃችሁ ያለውን አሳዩ፡፡

እናንተ ኃጥአን ሆይ ዕዳችሁ የተተወላችሁ ይመስል በቸልታ መቀመጥን፣ ስንፍናንስ ማን አስተማራችሁ? እርሱ ዝም ብሎ ቢያያችሁ ትዕግሥቱን ሲያሳችሁ ነውና እንግዲህ በንስሓችሁ ዕንባ ነፍሳችሁን አድኑ፤ መጸጸታችሁንም አሳዩት፡፡ ይቅር ባይነቱ ታግሦአችኋልና እንግዲህ ዲናሩን ከነ ትርፉ መልሱለት፡፡

ጌታ ሆይ በሁሉም መንገድ ቸርነትህ ትጠራኛለች በቃልኪዳኖችህም ሁሉ ክብርህ እና ፈቃድህ ሕይወት እንድናገኝ ነው፡፡ ጌታ ሆይ ታላቅ የሆነ ቸርነትህን ለሰው ልጆች ሁሉ ሰጠህ። ለምዕመናንም፣ ለዘማውያንም መረብህን ዘረጋህ፡፡ አመጸኛው ሰላማዊ ይሆን ዘንድ፤ የጠፉትም ይገኙ ዘንድ፡፡ ለድኅነታችን ይሆን ዘንድ በታላቅ ይቅርታው በቸርነት ዓይኖቹ አየን፡፡

ጌታ ሆይ ወፍ ከአዳኝ ወጥመድ እንደምታመልጥ እኔም ከኃጢአት አመለጥኩ፤ በመስቀልህ ሥርም መሸሸጊያ ጎጆን ሠራሁ፡፡ ወደዚህ ሥፍራ አሳች ከይሲ ሊደርስ አይችልምና፡፡

ጌታ ሆይ እርግብ ከመረብ እንደምትወጣ ከኃጢአት ወጥመድ ወጣሁ። በመስቀልህም ሥር ሆኜ ወደ ላይ እወጣለሁ፡፡ በዚያ ክፉ ጠላት የሆነ ዘንዶ ሊያገኘኝ አይችልምና፡፡ በዚያ ሆኜ ሕይወት የሚሰጠውን ስምህን የልጅህንም ስም የእውነት መንፈስ የመንፈስ ቅዱስንም ስም አመሰግናለሁ፡፡

#ቅዱስ_ኤፍሬም

(በእንተ ንስሐ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ወ አፍርሐት ገጽ 35-38 ➛በዲ/ን መዝገቡ የተተረጎመ)
ይቅርታ…!

• ቅዱስ ሲኖዶስ የትግራይ ሕዝብንና ምዕመናንን ይቅርታ በይፋ ጠይቋል።

• “የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፥ ይማራሉና።” ማቴ 5፥7

• “የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና።”ማቴ 5፥9

"2ኛ. በክልል ትግራይ (በአማርኛ ትግራይ ክልል ለማለት ነው) በተካሄደው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመስጠቷ፣ በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ከልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው ሕዝበ ትግራይን (በአማርኛ የትግራይን ሕዝብ ለማለት ነው) በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣ ጦርነቱ ቁሞ በአገር እቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣ በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ (በአማርኛ የትግራይ ሕዝብ ለማለት ነው) መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታ ጠይቋል።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርከ።

ወሰብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት"

ማስታወሻ፥

ብአዴን በትግርኛ ሲጠራ ነው። ብሔረ ዐማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እንደማለት ነው። ለብአዴን ዐማራዎች ስሙን ቢያወጡለት ኖሮ ብአዴን ሳይሆን የሚባለው አብዴን ነበር ተብሎ የሚጠራው። የዐማራ ብሔር ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ነበር የሚባለው። ሕዘበ ትግራይም እንደዚያው ነው።

•አባቶቻችን የይቅርታ ቃል ከእናንተ ወጥቷል። አሁን ዕዳው በትግራይ ላሉት አባቶች ነው።
2024/09/29 23:24:32
Back to Top
HTML Embed Code: