Telegram Web Link
Profile and wallpaper
ቅዱስ አባ ጳውሊ ከሰይጣን ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ!

👉 @mehereni_dngl

ክፍል-3(፫)

👉 @mehereni_dngl

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡

አባ ጳውሊም ሰይጣን ያለውን በሰማ ጊዜ የአንተን ሥራ የሚሠሩትን ወዳጆችህን እንዴት ታጠፋለህ አለው፡፡ ሰይጣንም እኔ ከፈጣሪ ታዝዣለሁ ፤ የአዛዤን ትእዛዝ እተላለፍ ዘንድ አይቻለኝም አለው፡፡
አባ ጳውሊም ፦ ብዙ ጥያቄ እጠይቅሃለሁና እንዳትዋሸኝ በሕያው እግዚአብሔር ስም አምዬሐለሁ አውግዤሃለሁ አለው፡፡
ሰይጣንም የምትሻውን ጠይቀኝ ትዕዛዝህን አልተላለፍም ኃይሌ በጸሎትህ ደክሟልና አለው፡፡

አባ ጳውሊም ሰይጣንን ፦ ከመጀመሪያው ከሰዎች በአንዱ አድረህ በኃጢአት ትጥለው ዘንድ አጋዥ የሚሆንህ ምንድነው አለው፡፡
ሰይጣንም ፦ ሰው በእግዚአብሔር ሕግ ጸንቶ ሳለ በማንም ላይ ማደር አይቻለንም፡፡ ነገር ግን ከእግዚአብሔር ሕግ ትንሽ ፈቀቅ ቢል ፤ እንዲሁ ደግሞ በየጊዜው ስሙን ባይጠራ ያን ጊዜ በእርሱ ለማደር ኃይል እናገኛለን፡፡

የእግዚአብሔር ስም መጥራት ያልኩህም በፍጹም ሃይማኖት ሆኖ ፦ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ማለት ነው፡፡ ሕፃንም ቢሆን ከመጠመቁ በፊት እናቱ በላዩ ላይ የእግዚአብሔርን ስም የማትጠራና በመስቀልም ምልክት በላዩ ላይ የማታማትብ ከሆነ እኛ እናድርበታለን፡፡ ዳግመኛም ወላጆችና አሳዳጊዎች ይህን መንፈሳዊ ሥራ ካልሠሩ በሕፃናት ላይ ለማደር ሥልጣን አለን አለው፡፡

ዳግመኛ ሴትና ወንድ ለመጋባት በወደዱና በፈቀዱ ጊዜ አስቀድመው በካህናት ጸሎትና በክርስቶስ ሥጋና ደም አንድ ከሆኑ ስልጣን የለንም፡፡ በመኝታቸው አንድ በሚሆኑበት ጊዜም ስሙን በመጥራት ወደ ፈጣሪያቸው ወደ እግዚአብሔር ቢጸልዩ በዚህ መልካም ሥራቸው ኃይላችን ይደክማልና በእነርሱም በልጆቻቸውም ላይ ስልጣን የለንም፡፡ ነገረ ግን ከዚህ ሁሉ መንፈሳዊ ሥራ ቢርቁ እኛ በእነርሱም በልጆቻቸውም ላይ እናድርባቸዋለን፡፡ እንሰለጥንባቸዋለን፡፡ ሰላምን እናሳጣቸዋለን ኑሮአቸው ጠብና ክርክር ፤ መጨረሻውም መለያየት ይሆናል፡፡
ሰው ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም እየጠራ ካልጸለየ የወደድነውን ሁሉ እናደርግበታለን፡፡ ዓለሙን ሁሉ ድል አድርገን እንገዛ ዘንድ ባለን ዐቅማችን እንታገላለን አለው፡፡

👉 @mehereni_dngl
👉 @mehereni_dngl
#Add በማረግ የኦርቶዶክስ ቁጥርን እጨምር !

group
👉 @mehereni_dngl_21
👉 @mehereni_dngl_21
#ጥያቄ

የአብርሃም ልጅ ማን ይባላል ?

#ምርጫ

⚫️ ያዕቆብ

🟣ጴጥሮስ

🔵ይሳቅ

🟢ማቴዎስ
#ሁላቹን_ይመለከታችኋል

በመሐርኒ ድንግል ውስጥ ምን አይነት መርሐ ግብር እዲቀርብላችሁ ትፈልጋላችሁ ሀሳባችሁን አሳውቁን በመሐርኒ group እና bot


👉 @mehereni_dngl_bot
👉 @mehereni_dngl_bot

👉 @mehereni_dngl_21
👉 @mehereni_dngl_21
የተለያዩ ኦርቶዶክሳዊ ጥያቄዎች ይቀጥሉ የምትሉ !




👉 @mehereni_dngl
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
  †   መሐርኒድንግል

[ እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ! ]


" በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው ፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም

እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።

በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል ፤ እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉአቸዋል ፥ ያቃጥሉአቸውማል።"

[ ዮሐ.፲፭፥፬ ]


አሁንም ከኦርቶዶክስ ጎን ነን!

          † † †
@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
እኛ የመሐርኒ ድንግል ተከታዮች እና አድሚኖች ግበረ ሰዶምን እንቃወማለን!

ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር

We, the followers and admins of Meharni Dungal, are against Gebre Sodom!

Long live Orthodoxy
#share
@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
#ታላቅ_የበረከት_ጥሪ_ለፍልሰታ

እንኳን ለፍልሰታ ፆም አደረሶት !

የወልድያ መባ እጥረት ላለባቸው የገጠር አብያተ ክርስቲያናት የሚውል መባ የማሰባሰብ ሥራን በመሥራት ላይ ስለሆንን በዚህ የበረከት ሥራ መሣተፍ የምትችሉ ሁሉ ትሳተፉ ዘንድ በእግዚአብሔር ስም ጥሪ እናስተላልፋለን።

መሳተፍ የምትፈልጉ @natansolo በውስጥ መስመር ማናገር የምትችሉ መሆኑን አሳውቃለሁ።

የተለያዩ ለቤተክርስቲያን ገቢ እና የተለያዩ ክብረ በዓል እናስታውቃለን ደግሞ በነፃ ነው!

አናግሩን👉 @mehereni_dngl_bot

@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
ስለ ቻናላችን እና ግሩፓችን የተለያዩ አስተያየት እና ቅሬታ ከላቹ ከ አሁን ሰዓት ጀምሮ እዚው ግሩፕ ላይ ወይም የምትፈሩ ከሆነ 👉 @mehereni_dngl_bot ያናግሩን
እንኳን ለደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የቡሄ መዝሙር በቅርቡ ይለቀቃል ጠብቁን !

@mehereni_dngl
ከርዕስ ውጪ |

የፋሽስቱን ሰራዊት መውጫ መግቢያ ያሳጡት ንጉስ እና ንግስታችን ዳግማዊ አፄ ሚኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ የተወለዱት በዚህች ቀን ነው።

እምዬ ምኒሊክ × ብርሀነ ዘ ኢትዮጵያ 💚💛❤️

የኢትዮጵያ ከፍታዎች !

@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
Audio
የቡሄ (ደብረ ታቦር) መዝሙር

እንኳን ለደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ!

@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
#ነሐሴ_16

#ዕርገተ_ማርያም

ነሐሴ ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን አምላክን የወለደች የእመቤታችን ድንግል ማርያም ሥጋዋ ወደ ሰማይ ያረገበት መታሰቢያዋ ሆነ። ከዕረፍቷም በኋላ ከእርሳቸው ስለመለየቷ ሐዋርያት ፈጽሞ እያዘኑ ነበር።

ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ተገለጠላቸው እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድ እንዳላቸውም ተስፋ ሰጣቸው። ወንጌላዊ ዮሐንስም እስያ በሚባል አገር እያስተማረ ሳለ በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድስተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደአለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ።

የክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ሥር ተቀምጦ አየው። የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው። እነርሱም የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል አሏት። ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ወጣ።

የክብር ባለቤት ጌታችንም እንዲህ እያለ አረጋጋት የተወደድሽ የወለድሽኝ እናቴ ሆይ ዘላለማዊ ወደ ሆነ መንግሥተ ሰማያት አሳርግሽ ዘንድ ነዪ። ያን ጊዜም በገነት ያሉ ዕፀዋት ሁሉም አዘነበሉ መላእክት የመላእክት አለቆች ጻድቃን ሰማዕታትም እየሰገዱላትና ፈጽሞ እያመሰገኗት አሳረጓት።

አባቷ ዳዊትም ንግሥት እመቤታችን ወርቀ ዘቦ ለብሳ ደርባ ደራርባ በቀኝህ ትቀመጣለች እያለ በበገና አመሰገናት። በኪሩቤል ሠረገላ ተቀምጣ ከዐረገች በኋላ በልጁዋና በፈጣሪዋ ቀኝ በታላቅ ክብር ተቀመጠች።

ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ሰግዶላት ተመልሶ ከሰማይ ወረደ ሐዋርያትን ተሰብስበው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው። እርሱም እንደ አየ እንደ ሰማ ሥጋዋንም በታላቅ ክብር በምስጋና እንደ አሳረጓት ነገራቸው።

ሐዋርያትም በሰሙ ጊዜ ዮሐንስ እንዳየና እንደሰማ ባለማየታቸውና ባለመስማታቸው እጅግ አዘኑ። ከዚህም በኋላ እያዘኑ ሳሉ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸውና የፍቅር አንድነት ልጆች ሰላም ይሁንላችሁ ስለ እናቴ ማርያም ሥጋ ለምን ታዝናላችሁ። እነሆ እኔ እርሷን በሥጋ ላሳያችሁ ልባችሁም ደስ ሊለው ይገባዋል አላቸው ይህንንም ብሎ ከእርሳትው ዘንድ ወደ ሰማያት ዐረገ።

ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ የነሐሴም ወር በባተ ቀን ለሐዋርያት ዮሐንስ እንዲህ አላቸው አምላክን የወለደች የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት የተዘጋጀን አድርጎ ያሰየን ዘንድ ኑ ይህን ሁለት ሱባዔ በመጾም የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው በልጅዋ በወዳጅዋ ቀኝ ተቀምጣ አይተን በእርሷ ደስ እንዲለን።

በዚያን ጊዜም ዮሐንስ እንዳላቸው በጾም በጸሎት ሱባዔ ያዙ የነሐሴ ወር እንደ ዛሬ ዐሥራ ስድስተኛ ቀን በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም ሐዋርያት ወደ ሰማይ አወጣቸው። በታላቅ ክብር በተወደደ ልጅዋ ቀኝ ተቀምጣ ከሥጋዋ ተዋሕዳ ተነሥታ እመቤታችን ማርያምን አዩዋት። እጆቿንም ዘርግታ የከበሩ ሐዋርያትን እያንዳንዳቸውን ባረከቻቸው በልባቸውም እጅግ ደስ አላቸው።

የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በከበረ ሥጋውና ደሙ ላይ ሠራዒ ካህን ሆነ። እስጢፋኖስም አዘጋጀ ዮሐንስም በመፍራት ቁሙ አለ። ሁሉም ሐዋርያት በመሠዊያው ዙሪያ ቆሙ በዚያን ጊዜ ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ።

ጌታችንም የቅዳሴውን ሥርዓት በፈጸመ ጊዜ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው ። ከዚያም በኪሩቤልና በሱራፌል ሠረገላ ተቀምጣ በምታርግ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እመቤታችን ማርያምን እንዲህ ብሎ ተናገራት።

በዚች ቀን የሆነ የዕርገትሽን መታሰቢያ በዓለም ውስጥ እንዲሰብኩ ልጆችሽ ሐዋርያትን እዘዣቸው። መታሰቢያሽን የሚያደርገውን ሁሉ ተጠብቆም በዚች ቀን ቅዱስ ቁርባንን የሚቀበለውን ኃጢአቱን እደመስስለታለሁ። የእሳትን ሥቃይ ከቶ አያያትም መታሰቢያሽን ለሚያደርግ ሁሉ በዚች ቀን ለድኆች በስምሽ ለሚመጸውት ቸርነቴ ትገናኘዋለች ይህም ሥጋሽ ወደ ሰማይ ያረገበት ነው።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ክብር ይግባውና ጌታችንን እንዲህ አለችው ልጄ ሆይ እነሆ በዐይኖቻቸው አዩ በጆሮቻቸውም ሰሙ በእጆቻቸውም ያዙ ሌሎችም ታላላቅ ደንቆች ሥራዎችን አዩ። እመቤታችንም ይህን ስትናገር ጌታችን ሰላምታ ሰጥቷቸው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረ ዘይት ተመለሱ።

የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ በፍጹም ደስታ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ ይገባናል እርሷ ስለእኛ ወደ ተወደደ ልጅዋ ሁልጊዜ ትማልዳለችና።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን። በረከቷም ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ከአባ ማትያስ ከሁሉም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት ጋራ ሐዋርያት ከሰበሰቧት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ከሁላችን ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ነሐሴ)

@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
2024/09/27 04:22:53
Back to Top
HTML Embed Code: