Telegram Web Link
ኦርቶዶክሳዊ የወጣቶች ህይወት !

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን፡፡

👉 @mehereni_dngl

#ማግባትን_ለምትሹ !

👉 @mehereni_dngl

" ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው ? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን ? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው ፤ እንዲህ ያለውን ፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው ፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" [ ፩ኛ ቆሮ.፯፥፪ ]

" ከድህነት ይወጣ [ ትወጣ ] ዘንድ " ነው የሚለውን ? ወይስ " ሀብት ለማግኘት ሲባል " ነው የሚለውን ? አይደለም ! ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው ፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡

ስለዚህ ልጆቼ ! እማልዳችኋለሁ ፦ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው ፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡

አባቶች ሆይ ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት ፦ ሀብትን አላየም ፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም ፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም ፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡

እናቶች ሆይ ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡ እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ ! ይስሐቅን ምሰሉት ፦ ዘፈንን ፣ ዳንኪራን ፣ ሳቅና ስላቅን ፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን ፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ ፣ ዝሙት ፣ ቅናት ፣ ጭቅጭቅ ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም ፥ አትነዋወፁም፡፡

እናንተ ልጃገረዶች ሆይ ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር ፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡

የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን ፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም ፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት ፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡"


(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

Join & share
👉 @mehereni_dngl
👉 @mehereni_dngl
👉 @mehereni_dngl
Enter a caption here!
Enter a caption here!
#የማንቂያ_ደውል

🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔
የምንፈራውም የማይቀረውም ሞት ነው። ዕለት ዕለት ስለሞት እየሰማንና እያየን ብንኖርም ቤተኛ አድርገን ልንወዳጀው ያልቻልነው ሞት ብቻ ነው።
ሞት ሁልጊዜ አዲስ ነው። እንደምንሞት አምነን እድር ብንመዘገብም እንደምንሞት አምነን ግን ንሰሐ ለመግባት አንፈጥንም። ሁልጊዜ እየቀበርን እንደምንኖር እንጂ አንድ ቀን እኛም ሞተን የምንቀበር አይመስለንም። ምክንኛቱም ሞት ማለት አዳምና ሄዋን ያመጡብን ድፍርስ ውሃ እንጂ ስንፈጠር ያልነበረ እንግዳ ነገር በመሆኑ ነው።
ስለዚህ ለዘለዓለም ሕይወት የተፈጠረ የሰው ልጅ ሞትን አሜን ብሎ መቀበል አለመፈለጉ እውነት ነው። ይሁን እንጂ ብንቀበለውም ባንቀበለውም እናታችን እንኳን የማትቀይረን ሞት ከፊታችን አለ። ነገር ግን ይህንን ንሡምና ምሁሩ ባዕለጠጋውና ደሀው ባለ ዝና ሆኖ ዓለም ያወቀውና ያላወቀው ሰው የሆነ በሙሉ የሚፈራውና የሚጨነቅለት ሞት በክርስቶስ ኢየሱስ ሙት ሆኗል።
እርሱ አምላካችን ሞትን በሞት ውጦታል። መድኃኒት ገዳዩን በሽታ ገሎ እንደሚያድን ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስም ገዳዩን ትገድሎ ከፍርሃትና ከባርነት ነጻ አውጥቶናል። ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሞተና እንደተነሳ ያመነ ሁሉ እርሱም ይነሳል መርፌው ባለፈበት ሁሉ አብሮ የተጣበቀው ክር ያልፋል።
ክርስቶስ በሄደበት ሁሉ ክርስቲያን ይሄዳል። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞተ ተነሳ ንጽህት ቅድስት እናቱ ድንግል ማርያምም ሞተች እሷም እንደልጇ ተነሳች። ሌሎችም በመቃብር ልብ ያሉ ክርስቲያኖች በሙሉ ከሞት ለመነሳት የጌታን ቀን እየጠበቁ ነው።አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ ሄኖክ አልሞተም። ነቢዩ ኤልያስም ሞትን ሳያይ በክብር አርጓል ብሎ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያለውን እውነት አምናለው የሚል ሰው እንዴት የአምላክ እናት ከሞት በመነሳት አርጋለች ሲሉት ለማመን ይቸገራል?ለማንኛውም ማስተዋሉን ይስጣቸው።

🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔
🔔Join🔔 @mehereni_dngl 🔔
🔔Join🔔 @mehereni_dngl 🔔
🔔Join🔔 @mehereni_dngl 🔔
🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔
Forwarded from ዘ ተዋህዶ
እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳቹ? አደረስን
🌹ዘተዋህዶ🌹
💐@tewhodox💐
💐@tewhodox💐
💐ለወዳጅ ለዘመድ ለጓደኛ ያጋሩ 💐
Forwarded from ዘ ተዋህዶ
🌿ሆሳዕና_ማለት_ምን_ማለት_ነው ??
🌿በሆሳዕና_ለምን_ቀለበት_እናስራለን ?
🌿በሆሳዕና_ጌታችን_ለምን_በአህያ_ላይ_ተቀመጠ .
🌿በሆሳዕና_ለምን_ዘንባባ_አነጠፉ ?
................................................................
እና ሌሎች በደንብ ይነበብ ሼር!
=> ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው??
ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ
የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::

=> በሆሣዕና ዕለት በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው??
1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው።
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከኃጢአት አውጣን ማረን ለንስኃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በለን ስንል ለጌታ ዳግም ላናጠፋ ቃል የምንገባበት ነው፡፡

=> ጌታችን በዕለተ ሆሳዕና ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??
ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ "
አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ
ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል።(ትንቢተ ዘካርያስ 9:9)
=> በአህያ መቀመጡ፦

•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምዕመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡

•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው
የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ
ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ።
ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ዘባባ የመነጠፉ ሚስጢር የምን ምሳሌ ነው???
1.ዝንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂይወት ይዘራል፡- የደረቀ የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡
ህዝቡ ከልብሳቸው ሌላ ስንት አይነት ቅጠንል አነጠፉለት ምን ምን??

ልብሳቸውን ማንጠፋቸው፡-
ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ሦስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡
ትልቅዋ አህያ በምን ትመሳለለች ውርን ጭለዋስ???
ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው።
1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና።

ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡

ወስበሐት_ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ_ድንግል ወለመስቀሉ_ክቡር አሜን አሜን አሜን
🌹ዘተዋህዶ🌹
💐@tewhodox💐
💐@tewhodox💐
💐ለወዳጅ ለዘመድ ለጓደኛ ያጋሩ 💐
እንኳን ለበዓለ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ! አደረሰን!


✝️ መልካም በዓል ✝️

Join & share
👇👇👇👇👇👇
@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
@mehereni_dngl
መሐርኒ ድንግል pinned «🌿ሆሳዕና_ማለት_ምን_ማለት_ነው ?? 🌿በሆሳዕና_ለምን_ቀለበት_እናስራለን ? 🌿በሆሳዕና_ጌታችን_ለምን_በአህያ_ላይ_ተቀመጠ . 🌿በሆሳዕና_ለምን_ዘንባባ_አነጠፉ ? ................................................................ እና ሌሎች በደንብ ይነበብ ሼር! => ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው?? ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን…»
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼🌼መልካም አዲስ አመት🌼🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

እንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ሉቃስ አሸጋገራችሁ !

መልካም አዲስ አመት
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
🌼👇👇👇👇👇👇🌼
🌼 @MEHERENI_DNGL 🌼
🌼 @MEHERENI_DNGL 🌼
🌼 @MEHERENI_DNGL 🌼
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️

✝️🌼✝️ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ! ✝️🌼✝️

መሐርኒ ድንግል
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
✝️ @MEHERENI_DNGL ✝️
✝️ @MEHERENI_DNGL ✝️
✝️ @MEHERENI_DNGL ✝️
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@MEHERENI_DNGL
በስመአብ በወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን

#ጥያቄ

የዘብዴዎስ ልጅ ማነው?

#ምርጫ

⚫️ቅዱስ በርቶሎሜዎስ
🔴ቅዱስ ያዕቆብ
🔵ቅዱስ እስጢፋኖስ
⚪️ቅዱስ ሐናንያ

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጥያቄ እና መልስ ለማግኘት
👉 @mehereni_dngl
👉 @mehereni_dngl
👉 @mehereni_dngl
Audio
🌹ዘተዋህዶ🌹
💐@tewhodox💐
💐@tewhodox💐
💐ለወዳጅ ለዘመድ ለጓደኛ ያጋሩ 💐
+እንደ አርዮስ ሐሳብ መድኃኒታችን ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ አይደለም (ሎቱ ስብሐት!!) ማለት ክርስትናን ከሥሩ ፈንቅሎ መጣል ነው::
+ስለ ክርስቶስ እግዚአብሔርነት ብሉይም ሐዲስም እየመሰከሩ:-
(ኢሳ. 9:6, መዝ. 46:5, 77:65, ዘካ. 14:4, ዮሐ. 1:1, 10:30, ራዕይ. 1:8, ሮሜ. 9:5 . . .)
አርዮስና የዛሬ መሰሎቹአንዲት ጥቅስ ይዘው ክርስትናን ከመሠረቱ ለመናድ መሞከራቸው በእርግጥም ከሰይጣን መላካቸውን ያሳያል::

+በወቅቱም በመወገዙ አርዮስ ወደ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ሔዶ ከሰሰ:: ቅዱሱ ንጉሥም የጉዳዩን ክብደት ተመልክቶ የዓለም ሊቃውንት ይሰበሰቡ ዘንድ አዘዘ::

+በ325 ዓ/ም (በኛው በ318 ዓ/ም) ለ40 ቀናት የሚቆይ ሱባኤን ያዙ:: ሱባኤውን ሲጨርሱም በ4ቱ ፓትርያርኮች (እለእስክንድሮስ: ሶል ዼጥሮስ: ዮናክንዲኖስና ኤዎስጣቴዎስ) መሪነት: በእለእስክንድሮስ ሊቀ መንበርነት: በአትናቴዎስ ጸሐፊነት ጉባኤው ተጀመረ::

+በጉባኤው ሙሉ ስልጣን በሰማይ ከፈጣሪ: በምድር ከንጉሡ የተሰጣቸው አበው አርዮስን ተከራክረው ከነ ጀሌዎቹ ምላሽ አሳጡት:: ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ: ሥግው ቃል: ራሱም እግዚአብሔር መሆኑን አስረዱት::

+በጉባኤው መጨረሻም አልመለስም በማለቱ አርዮስን አወገዙ: ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንደሚገባ አደራጁ:: አባቶችም ሥራቸውን ከጨረሱ በሁዋላ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስን ባርከው ወደየ ሃገረ ስብከታቸው ተመልሰዋል::

+ቅዱስ ሶል ዼጥሮስም ከጉባዔው ከተመለሰ በሁዋላ በጐ ጐዳናውን አቅንቶ ቀጥሏል:: ብዙ ድርሳናትን ደርሶ: በድካም ሰብኮ ኢአማንያንን መልሷል:: ፈላስፎችንም ድል ነስቶ አሳምኗል:: መናፍቃን ደግሞ ፈጽመው ይፈሩት ነበር:: ሊቀ ዽዽስናን በተሾመ በ11 ዓመቱም በዚህች ቀን ዐርፏል::

=>የሥላሴ ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁንና ጥር 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.በዓለ ሥሉስ ቅዱስ
2.ቅዱስ ሶል ዼጥሮስ
3.ቅዱስ ኤፍሬም
4.ቅዱስ ሰሎሞን

=>ወርሐዊ በዓላት
1.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
2.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
3.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
4.አባ ባውላ ገዳማዊ
5.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
6.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)

=>+"+ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: +"+ (ቆሮ. 13:14)

   <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
2024/09/27 13:26:41
Back to Top
HTML Embed Code: