Telegram Web Link
የጠቅላይ ቤተ ክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባዔ አባላት በጽርሐ ተዋሕዶ የጋራ ጉባዔ በማድረግ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት ጋር በሁለትዮሽ የአሠራር ሂደት፣በመልካም አስተዳደር፣በሕግ ፣ደንቦችና መመሪያዎች አከባበር በአጠቃላይ ሥራዎችን በተቋማዊ አሠራር ሂደት በማከናወን ዙሪያ የጋራ መድረክ ተዘጋጅቶ ውይይት እንዲደረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ኅዳር ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የጋራ ጉባኤ በማካሔድ ላይ ናቸው።

በጉባኤው መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፣ቃለ በረከትና ቡራኬ በቤተ ክርስቲያናችን ያለውን የመልካም አስተዳደር ችግር ሁላችንም እናውቀዋለን።ማስተካከልም እንችላለን ብለዋል።

እኛ በቤተ ክርስቲያናችን የሚስተዋለውን ችግር ለማስተካከል የማንችለው ልባችን ስላላስተካከልን ነው።ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ ራሳችንን ሳናስተካክል ሌላውን ማስተካከል ስለማንችል ቅድሚያ ራሳችንን ለማስተካከል ቆርጠን መነሳት ይኖርብናል ብለዋል።
አያይዘውም ሁላችንም የቆምነው ለቤተ ክርስቲያናችን እንጂ ለሌላ ዓላማ አይደለም።ያሉት ቅዱስነታቸው ችግሮቻችንን ለመፍታት መወያየት ተገቢ ነው።"ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም" እንደሚባለው ሁሉ ችግሮቻችንን ለመፍታት ከልብ ከተነሳን የሚያስቸግር ነገር ይኖራል ብለን አናምንም።ካሉ በኋላ ከተጠያቂነትና ከተወቃሽነት ለመዳን፣ቤታችንን ለማቅናትና ለማስተካከል የሚጎለን ምንድነው ?ያሉት ቅዱስነታቸው ይህን ለማድረግና ቤተክርስቲያናችንን ለመጠበቅ ሙሉ ሥልጣንና ኃላፊነት እያለን መቸገራችን ያስገርማል ብለዋል።

ዘወትር ሁላችንም ራሳችንን መመርመር አለብን የት ነው ያለነው፣ምንድነው የምንሠራው፣ወዴት ነው የምንሔደው ብለን ራሳችንን በመጠየቅ ያለፈውን ጊዜ ችግሮች ማሰብና በተሰጠን መንፈሳዊ ኃላፊነት ልክ በመሥራት ቤተክርስቲያንን መጠበቅና ምዕመናንን የሚያረካ ተግባር መፈጸም ይኖርብናል ያሉት ቅዱስነታቸው ሁላችንም ራሳችንን በአግባቡ በመመርመር ራሳችንን እናስተካክል ካሉ በኃላ በአንድነትና በጽናት ለቤተክርስቲያናችን እንቁም።በመመካከር አንድ ሆነን በመቆም ለቤተክርስቲያን ህልውና በጋራ እንሥራ እኛ ተመካሪዎች አይደለንም መካሪዎች እንጂ ስለዚህ መመካከር ችግሮችን ለመቅረፍ የሚጠቅም ስለሆነ ተመካክረን እንሥራ ችግሮችንም በግልጽ በማውጣት ለችግሮቻችን መፍትሔ በማበጀት ለውጤት ልናበቃው ይገባል በማለት አባታዊ መልእክታቸውን በማጠናቀቅ ጉባኤውን በይፋ ከፍተዋል።

ብፁእ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ባስተላለፉት መልእክት፦ መልካም አስተዳደርን ለማምጣትና ችግሮችን ለመፍታት ውይይት ወሳኝ ነው።ቅዱስነትዎም በቤተክርስቲያናችን መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የዘወትር ምኞትዎና ጸሎትዎ እንደሆነ ይታወቃል።

በዚህ ጊዜ የሚታየውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በጋራ ተወያይተን መፍታትና የቁጥጥር ሥርዓታችንን በማጥበቅ ችግሮችን በአግባቡ መፍታት አለብን ብለዋል አያይዘውም ሕገ-ወጥ ቅጥርና ዝውውርን በተመለከተ እየተከናወነ የሚገኘውን ሕገ ወጥ ቅጥርና ዝውውር በማረም በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በቀረበው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት መሥራት ይኖርበታል ብለዋል።

ሀገረ ስብከቱና ጠቅላይ ቤተክህነቱ ተናበውና ተግባብተው መሥራት በሚገባቸው ጉዳዩች ላይም ሕግንና ሕግን መሠረት አድርገን መሥራት ስለሚገባቸው ይህን መድረክ ለማዘጋጀት ተገደናል ያሉት ብፁእነታቸው የዚህ መድረክ ዓላማ ለመወነጃጀል ለመነቃቀፍና ለመተቻቸት ሳይሆን በመወያየትና በመግባባት በሀገረ ስብከቱ የሚታዩትን ችግሮች ለመፍታት ነው በማለት የመክፈቻ ንግግራቸውን አጠቃለዋል።

ጉባኤው በዛሬው ዕለት በሚያካሒደው ጥልቅ ውይይት ሕግ፣መመሪያ፣ደንቦችና ተቋማዊ አሠራሮችን በጠበቀ መልኩ ሥራዎችን በማከናወን ማእከላዊነትን ባለማክበር ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት ተቋማዊና ሕጋዊ አሠራሮችን በመተግበር በሀገረ ስብከቱና በጠቅላይ ቤተክህነት መካከል መዋቅራዊ ግንኙነቶችን ማጠናከር የሚያስችሉ ልዩልዩ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://www.tg-me.com/mahibere_kidusan
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተክህነት መሆኑን በመገንዘብ ሕግና መመሪያን አክብሮ እውነትና እውነተኝነትን መርሁ አድርጎ እንዲሰራ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ።
****

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በጋራ ለመፍታትና መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት በዛሬው እለት ባደረጉት የጋራ ጉባኤ ተስማሙ።

ሀገረ ስብከቱ ለጠቅላይ ቤተክህነት በይግባኝ የቀረቡ አቤቱታዎችና ለጉባኤው በአጀንዳነት የቀረቡት ሰነዶች በሸኚ ደብዳቤ እንዲደርሰው ተደርጎ በአጭር ጊዜ ውስጥ መፍትሔ እንደሚሰጥበት እንደሚያደርጉ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገለጹ።
በዚሁ የጋራ ጉባኤ ማጠናቀቂያ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብና ጥብቅ የሥራ መመሪያ ከእንግዲህ በኋላ በሀገረ ስብከቱ የአሰራር ስህተትና መመሪያን አክብሮ ባለመስራት ምክንያት የሚያለቅሱ ካህናት እምባቸው እንዲታበስ፣ ማንም ሰው አያልቅስ፣ ፍትህ እንዲነግስ፣ የተበደለ እንዲካስ፣ ቤተ ክርስቲያንን ብቻ ማዕከል በማድረግ እንስራ ፣ የሚደረግ ዝውውርና የሚሰጥ ሹመት በህግና በመመሪያ ብቻ እንዲከናወን፣ የማንኛውም የሥራ ኃላፊና የአድባራት ወገዳማት አክተዳዳሪዎች ዝውውር ሥራን ማዕከል ባደረገ አግባብ ብቻ እንዲከናወን፣የሚከናወኑ ዝውውሮች ሁሉ በምክንያት ብቻ እንዲሆኑ፣ማንም ሰው ሲያድግም ሆነ ሲዛወር በሥራ አፈጻጸሙ ማለትም የሚያድግ ባሳየው የሥራ እድገት፣ የሚዘወርድ ደግሞ ባስመዘገበው የሥራ ድክመት ብቻ እንዲሆን፣ በተደጋጋሚ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤና በቋሚ ሲኖዶስ በተሰጠው መመሪያ መሰረት ከሥራ ገበታቸው የተፈናቀሉ የትግራይ ተወላጆችና ያለበቂ ምክንያት ከሥራ ገበታቸው የተነሱ አገልጋዮች በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ባስቸኳይ ወደ ሥራ መደባቸው እንዲመለሱ የመጨረሻና ጥብቅ መመሪያ ሰጥተዋል።

በሀገረ ስብከቱ በኩል ከጠቅላይ ቤተክህነት የሚሰጡ መመሪያዎችን ሁሉ "ጠቅላይ ቤተክህነት ምን አገባው" በሚል ሰንካላ ምክንያት የሚደረገው መመሪያን ያለማክበርና ያለመፈጸም ተግባር ችግሮችን ላለማባባስ ሲባል በትዕግስት ስናልፈው ቆይተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ከዚህ በኋላ ይህ አይነቱ ተግባር ፍጹም ተቀባይነት የሌለውና በትዕግስት የምናልፈው ጉዳይ አይደለም ብለዋል።

አያይዘውም ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣው መመሪያ መሰረት ሀገረ ስብከቱ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተክህነቱ መሆኑን ታሳቢ ባደረገ አግባብ ሕግና ሕጋዊ አሰራርን ብቻ በመከተል ሥራውን ማከናወን እንደሚገባው ገልጸው በጅምላና ምክንያታዊ ባልሆነ አግባብ የሚደረግን ዝውውርና እድገት ጠቅላይ ቤተክህነቱ በፍጹም የማይታገሰው መሆኑን በመረዳት ሀገረ ስብከቱ ሕግን አክብሮ መስራት ይገባዋል ብለዋል።

በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋለውን ከፍተኛ የመልካም አስተዳደር ችግር በብፁዕ አቡነ አብርሃምና በብፁዕ አቡነ ሔኖክ መካከል የተፈጠረ ችግር በመኖሩ የተፈጠረ በማስመሰል ለህገወጥ ድርጊቶች ሽፋን ለመስጠት መሞከር ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን የገለጹት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በእርሳቸውና በብፁዕ አቡነ ሔኖክ መካከል ምንም አይነት ልዩነትና ጸብ የሌለ መሆኑን ጠቁመው እየተጋጨ ያለው ሥራው በህግና በመመሪያ ተደግፎ ማዕከላዊነትን ባልጠበቀ አግባብ በመከናወኑ ስለሆነ መፍትሔውም ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣውን ደንብ አክብሮ መስራት ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።

የምንሰራው ሥራ መንፈሳዊ አገልግሎት እንደመሆኑ መጠን እውነትንና እውነተኛነትን ብቻ መሰረት ባደረገ አግባብ መከናወን ይኖርበታል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ሀገረ ስብከቱ ካህናትና ምዕመናንን ከሚያሳዝንና በቤተክርስቲያን ላይ አመኔታን ከሚያሳጣ ሥራ በመራቅ ሀቅን መሰረት አድርጎ መመሪያን በማክበር እንዲሰራ የመጨረሻ ያሉትን መመሪያ ሰጥተዋል።

በመጨረሻም ጉባኤው እንዲህ አይነቱ የጋራ መድረክ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማሳሰብና በብፁ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የተሰጡ መመሪያዎችን አክብሮና አስከብሮ ለመስራት በመስማማት የዕለቱን ጉባኤ በጸሎት አጠናቋል።

ምንጭ፦ የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

https://www.tg-me.com/mahibere_kidusan
በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ በመሠረታዊ የርቀት ትምህርት መርሐ ግብር ያስተማራቸውን የመጀመሪያዎቹን ተመራቂዎች ማስተባበሪያው በየወሩ የወሩ መጨረሻ በሚውለው እሑድ በሚያዘጋጀው የወርኃዊ ጉባኤ መርሐ ግብር ላይ ኅዳር 30/2016 ዓ.ም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ ስለሚያስመርቅ በዕለቱ በመገኘት ቃለ እግዚአብሔርን እየተማርን ተመራቂ የርቀት ተማሪዎችን እንድናስመርቅ ሁላችንም ተጋብዘናል!
‹‹የእግዚአብሔር ሰው›› (፩ኛ ሳሙ.፱፥፮)

ክፍል ሁለት

አምላካችን እግዚአብሔር ይህን ዓለም ፈጥሮ እንዲሁ የተወው አይደለም፡፡ በብዙ መንገድ ይጠብቀዋል፤ ያስጠብቀዋል፤ ያስተምረዋል፤ ይመክረዋል፤ ያስመክረዋል፤ በየዘመኑ እንዲሁ ሲያደርግ እንደኖረ እንረዳለን፡፡ ‹‹እግዚአብሔር በአንድም በሌላም ይናገራል›› እንዲል መጽሐፍ እግዚአብሔር በተለይ የሰውን ልጅ ከፍጥረት አልቆ ከፈጠረው በኋላ መለኮታዊ ጥበቃ፣ መልአካዊ ጥበቃ እንዲሁም ሰዋዊ ጥበቃ እንዳይለየው አድርጎታል፡፡ (ኢዮ.፴፫፥፲፬)

ሰዋዊ ጥበቃ በነገሥታቱ፣ በካህናቱ እንዲሁም በነቢያቱ ምክር፣ ትምህርት፣ ተግሣጽና ጥበቃ ሥር አድርጎ በየጊዜው ከክፉ ነገር ጠብቆ አኑሮታል፤ እያኖረው ይገኛል፡፡ በዚህ ረገድ በተለይ በብሉይ ኪዳኑ ዘመን ከአባታችን አዳም ጀምሮ በየዘመኑ በትውልዱ ቅብብሎሽ ሕዝቡን እንዲመክሩ፣ እንዲያስተምሩ፣ እንዲገሥጹ ወደ ፊት ሊመጣ ካለው መቅሠፍት እንዲጠበቁ፣ አስተማሪ፣ መካሪ ፣በመከራም ወቅት አጽናኝ አድርጎ ከላካቸው ቅዱሳን ዋነኞቹ ነቢያት ናቸው፡፡

በክፍል አንድ እንዳቀረብነው ነቢያት የእግዚአብሔር መልእክተኞች እና የእግዚአብሔር ሰዎች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔር ሰዎች ደግሞ ትክክለኛና እውነተኛ ሰዎች በመሆናቸው የተናገሩት ሁሉ የሚፈጸም ነው፡፡ በአንደኛ ሳሙኤል መጽሐፍ ላይ እንዲህ የሚል ቃል አለ፤ ‹‹…እነሆ አንድ የእግዚአብሔር ሰው በዚህች ከተማ አለ፤ እርሱም የተከበረ ሰው ነው፤ የሚናገረውም ሁሉ በእውነት ይፈጸማል …፡፡›› (፩ኛሳሙ.፱፥፮) ይህ ቃል የተነገረው ስለ ነቢዩ ሳሙኤል ነው፡፡ ነቢያት ከእውነተኛው እግዚአብሔር የተነገራቸውን እውነተኛ ትንቢት፣ እውነተኛ ትምህርት፣ እውነተኛ ቃል በእውነት የሚናገሩ፣ የሚያሰተላልፉ፣ የራሳቸውን ሳይሆን የእግዚአብሔርን መልእክት ለሕዝቡ የሚያደርሱ ታማኝ መልእክተኞችና አፈ እግዚአብሔር ናቸው፡፡

አንዳች ቃል ከራሳቸው አይናገሩም፤ ለክብራቸውና ለዝናቸውም ሆነ ለሥጋዊ ጥቅማቸውና ዓላማቸው አንዳች ተጨንቀው፣ ከንቱና ምድራዊ ሐሳብን ከልባቸው አንቅተው፣ ከአንደበታቸው አውጥተው የሚናገሩ አይደሉም፡፡ ሲናገሩ እንኳን ‹‹እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤›› ይሉ ነበር፡፡ (አሞ.፩፥፫፤፮፥፱) ምክንያቱም ትንቢት ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ሀብት ጸጋ እንጅ በሰው ፈቃድ የመጣ ወይም የሚገኝ አይደለም፡፡ ቃለ መልእክቱም የአናጋሪው እግዚአብሔር እንጂ የተናጋሪው አይደለም፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹..ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደለትም፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፤ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ…›› ያለው ለዚያ ነው፡፡ (፪ኛጴጥ.፩፥፳፩) ከሐዋርያው መልእክት የምንረዳው ብዙ ነገር ነው፡፡

. አንደኛ ትንቢት በሰው ፈቃድ የመጣ አለመሆኑን፤
. ሁለተኛ ማንም ለራሱ ፈቃድ ትንቢትን መተርጎም የማይገባው መሆኑን፤
. ሦስተኛ ከእግዚአብሔር ያልተላከ የማይናገረው መሆኑን፤
. አራተኛ ከእግዚአብሔር ተልኮ ትንቢት ለመናገር መልክተኛው ራሱ ቅዱስ መሆን የሚገባው መሆኑን ወዘተ ነው፡፡

ነቢያት ዘወትር በእግዚአብሔር ውሳኔ ስለሚፈጸሙ ድርጊቶች፣ መንግሥታት ሕግ ሲተላለፉ ስለሚመጣባቸው መቅሠፍት ወይም ማድረግ የሚገባቸውን እንዲያድርጉ፣ ስለ ኃጢአት ወይም ወደፊት ስለሚከሰቱ ነገሮች ወዘተ በምሳሌም፣ በቀጥታም፣ በቃልም፣ በድርጊትም፣ የሚገልጡና የሚያሰተላልፉ መሆናቸውን በብዙ መልኩ ተጽፏል፡፡ (ኢሳ.፭፥፩-፯፤ሕዝ.፬፥፪) ክርስቶስም ወደዚህ ዓለም በሥጋ ብእሲ ሲመጣ ከፈጸማቸው አገልግሎቶችም ትንቢተ ነቢያት ዋናው ነው፡፡ (ማቴ.፭፥፲፯)

እንደ ብሉይ ኪዳን ዘመን አገልግሎቱ የጎላም ባይሆን በሐዲስ ኪዳንም እግዚአብሔር ሀብተ ትንቢት የተሰጣቸው ነቢያትን እንዳስነሣና ከሐዋርያቱ ጋር ቤተ ክርስቲያንን እንደ መሠረቱ፣ ከመምህራንም ጋር እንዳገለገሉ በሐዋርያት ሥራ ፲፫፥፩ እንዲሁም በቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ላይ ተጽፎ እናነባለን፡፡ (ኤፌ፪፥፳) በአብዛኛው የሐዲስ ኪዳን ነቢያት አገልግሎታቸው እንደ ብሉይ ኪዳን የጎላና የታወቀ ብዙም ትኩረት የሚሰጠው አይደለም፡፡

ትንቢትና ራእይ የሚባሉትም በዚያ ልክ የሚተኮርባቸው አይደሉም፡፡ ምክንያቱም ሊቃውንቱ እንደሚሉት በብሉይ ኪዳን ዘመን የነቢያትም ሆነ የትንቢት አስፈላጊነት ከፍ ያለ እንዲሆን ምክንያቱ ዓመተ ፍዳ፥ ዓመተ ኩነኔ ነበር፤ ዘመኑ የሰው ልጅ በአዳማዊና በሔዋናዊ በደል ምክንያት በመከራና በጨለማ የነበረበት በመሆኑ፣ በሥጋ ወደ መቃብር፣ በነፍስ ወደ ሲኦል የሚወረድበት ዘመን ስለ ነበር ‹‹ሁላችንም እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፤ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፤ በደላችንም እንደ ነፋስ ወስዶናል›› እንዳለ ሕዝቡ በመከራ ውስጥ ስለ ነበሩ ተስፋ እንዳይቆርጡ፣ እግዚአብሔር ትቶናል እንዳይሉ፣ ነቢያት አጽናኝ መካሪ ሆነው፣ የእግዚአብሔርን ማዳን እየሰበኩ፣ ነገረ ምጽአቱን እየነገሩ ተስፋ የሚሰጡ፣ የሚመክሩ፣ የሚያጽናኑ ስለሆኑ ነበር፡፡ (ኢሳ.፷፬፥፮፣፵፥፩) በሐዲስ ኪዳን ግን ገና ሊመጣ ያለው፥ ክርስቶስ ያልነገረን አዲስ ሊነግሩን የሚችሉት ያላወቅነው፥ ግን ልናውቀው የሚገባ እምብዛም ነገር ስለሌለ ነቢይነትና ትንቢት ጎልተው የሚነገሩበት ዘመን አይደለም፡፡

ይልቁንስ ሐሰተኛች ነቢያት ነቢይ ሳይሆኑ ነቢይ ነን የሚሉ፣ ሀብተ ትንቢት ሳያድርባቸው ትንቢት እንናገራለን የሚሉ፣ ትንቢትን ለራሳቸው ፈቃድ የሚተረጉሙ፣ ሐሰተኛ ሆነው በሐሰት ትምህርታቸው የሚያስቱ ብዙዎች እንደሚመጡ ባለቤቱ የነገረን እንደ ብሉይ ኪዳኑ ዘመን ብዙ ነገራችን በትንቢትና በትንቢት ተናጋሪዎች አጀንዳ እንዳይወሰድ ነው፡፡ ይህ ማለት በሐዲስ ኪዳን ዘመን “ትንቢትም፣ ነቢይም የለም፤ አይኖርም” ብሎ ለመደምደም አይደለም፤ እግዚአብሔር ባወቀ በዚህ ጸጋ የጎበኛቸው ኃላፍያትንና መጻእያትን ማየት የሚችሉ የሉም ለማለት አይደለም፡፡ በሐዲስ ኪዳን ነቢያት ቢኖሩ እንኳን ሥራቸው ቤተ ክርስቲያንን መምከር፣ ማጽናትና ማነጽ ነው እንጂ ትንቢት መናገር አይደለም፡፡ (መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ ፻፵፩፤የሐዋ.ሥራ.፲፭፥፴፪)

እንግዲህ ከላይ እንደጠቀስነው ሐሰተኞች ነቢያት እንደሚነሡ፣ ብዙዎችንም እንደሚያስቱ፣ ክርስቶስም፥ ሐዋርያትም ብዙ ተናግረዋል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ‹‹..የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውስጣቸው ግን ነጣቂ ተኩላዎች ከሆኑ ሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ›› እንዳለ የበግ ለምድ የለበሱ ናቸው፤ (ማቴ.፯፥፲፭) በጦር የተወጉትን፣ በመጋዝ የተተረተሩትን፣ በቅድስና ዘመናቸውን የፈጸሙትን፣ ሕዝቡን በቅንነት የመሩትን፣ ያገለገሉትን መልካሙን የነቢያትን ስም ለብሰዋል፤ ውስጣቸው ግን በተንኮል፣ በፍቅረ ንዋይ፣ በፍቅረ ዝሙት፣ በሟርትና በጥንቆላ፣ በክፋትና በሽንገላ የተሞላ ክፉ ነጣቂዎች፣ ከሕይወት ወደ ሞት የሚነጥቁ፣ ቀልብ አጥተው ቀልብ የሚያሳጡ፣ ክፉ፣ ቀማኞችና ሐሰተኞች ነቢያት ዛሬ በዘመናችን መጥተዋል፡፡
ቅዱስ ጴጥሮስ በበኩሉ ‹‹ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ፤ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳን ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሾልከው ያገባሉ›› በማለት አስተምሮናል፡፡ (፪ኛ ጴጥ.፪፥፩) ዛሬ በዘመናችን አንዳችም ሳይሸራረፍ ይህ ቃል ተፈጽሟል፡፡ በሐሰተኛ የኑፋቄ ትምህርት ሕዝቡን የበከሉ፣ መንጋውን ከበረት አስወጥተው ተቅበዝባዥ ያደረጉ፣ በነፋስ እንደሚገፋ ገለባ አየር ላይ በምኞትና በከንቱ ተስፋ የሚያንሳፍፉ ሐሰተኞች ነቢያት ብዙ ናቸው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ ሐዋርያት በመልእክታቸው የነገሩንን የሐሰት ትምህርት የሚያስተምሩ፣ የዋጃቸውን ጌታ የካዱ ትውልዱን ወደ እቶን እሳት የሚጨምር፣ ክፉና የተሳሳተ የጥፋት ትምህርትን አሾልከው ያስገቡ፣ ስተው የሚያስቱ፣ ጠፍተው የሚያጠፉ ክፉ ነቢያት፣ ሐሰተኛ መምህራን መጥተዋል፡፡ ቅዠታቸውን ራእይ፣ ምኞታቸውን ትንቢት፣ ተረታቸውን ወንጌል ብለው የሚያስተምሩ ነጣቂ ተኩላዎች ከዚህም ከዚያም በዝተዋል፡፡ ግን ጌታ ምን አለን? ከእነዚህ ተጠንቀቁ፡፡

ቅዱስ ዮሐንስም በመልእክቱ ‹‹ወዳጆች ሆይ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና›› ይላል፡፡ (፩ኛዮሐ.፬፥፩) ቆም ብሎ መመርመር፣ ሐሰተኞችን ከእውነተኞች መለየት፣ ከነጣቂዎችና ከክፉ ትምህርታቸው መጠበቅ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉን ሊሆን ያለውን ነገር እያንዳንዱን ነግሮናል፤ አስቀድሞ አስጠንቀቅቆን ሳለ ድንቅ የሆነ አዲስ ነገር ፍለጋ በክፉ መንፈስ በሚመሩ፣ ከእግዚአብሔር ባልሆነ የአጋንንት መንፈስ በሚጓዙ፣ በመልካሙ ስም በነቢይነት፣ በከበረው ስም በመምህርነት የሚመጡትን እናውቃቸውና እንጠነቀቃቸው ዘንድ ተነግሮናል፡፡

ተወዳጆች ሆይ! ሐሳቡ ሰፊ በመሆኑ ልንጨርሰው አልተቻለንም፡፡ ስለሆነም ሐሰተኖች ነቢያት የሚባሉት የትኞቹ ናቸው? ሐሰተኛ የሚያስብሏቸው ምክንያቶች ምንድን ናቸው? የሚሉትንና ተዛማጅ ነገሮችን በቀጣይ በክፍል ሦስት ልናቀርብላችሁ እንሞክራለን፡፡
የበረከት ጾምና የመጽናናት ሳምንት ይሁንልን፤ አሜን!
"ጽዮንን ክበቧት" መዝ.፵፯፥፲፪

መጽሐፈ ኦሪት ዘፀአት የታቦተ ጽዮንን ነገር እንዲህ ይተርከዋል። ሙሴ እስራኤልን ከካራን ወደ ከነዓን ይዞ ሲወጣ በሲና ተራራ ፵ መዓልትና ሌሊት ከዘረጋ ሳያጥፍ ከቆመበት ሳይቀመጥ በፍጹም ጽሙና ሁኖ በጾምና ጸሎት እግዚአብሔርን ጠየቀው። የለመኑትን የማይነሣ የጠየቁትን የማይረሳ እግዚአብሔርም ዐሥርቱ ትእዛዛት የተጻፈበትን ሁለት ጽላት ለሙሴ ሰጠው። ሙሴም ወደ ሕዝበ እስራኤል ይዞ ወረደ። እስራኤል አሮንን አስገድደው፤ በጌጦቻቸው የጥጃ ምስል ያለው ጣዖት ሠርተው እያመለኩ ቢጠብቁት ሙሴ ከእግዚአብሔር የተቀበለውን ታቦት ሰበረ። ዳግመኛም እግዚአብሔር ሙሴን እንደ ቀድሞዎቹ አድረገህ ቅረጻቸው ብሎ ጽላትን እንዲያዘጋጅ አስተማረው። ሙሴም እንደታዘዘው አድርጎ ሠራ። (ዘፀ.፳፬ እና ፳፭) ‹‹ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ሙሴ ጽላቶቹን ባይሰብር ጽላትን መሥራት እንዴት ይቻል ነበር? (ሮሜ ፰፥፳፰)

ለ፭፻ ዓመታት ገደማ በእስራኤል ብዙ ገቢረ ተአምራትን ስታደርግ የነበረችዋ ይህች በሙሴ የተቀረጸች ታቦት በቀዳማዊ ምኒልክ በኩል ለኢትዮጵያ ተሰጠች። (መጽሐፈ ክብረ ነገሥትን ሙሉውን ያንብቡ) የቤተ ክርስቲያን መረጃዎች ስለ አመጣጧ እንዲህ ያስነብበናል፤ ‹‹በማእከላዊ ትግራይ አክሱም ሀገረ ስብከት አክሱም ከተማ የምትገኘው ታቦተ ጽዮን በቀዳማዊ ምኒልክ ከኢየሩሳሌም መጥታ በምኩራብ ትኖር ነበር። ይህም ከጌታ ልደት በፊት ፱፻ ዓመት ገደማ ነው።›› (የቤተ ክርስቲያን መረጃዎች፣ በሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት፣ ገጽ ፪፻፭)
በምኩራብ ብትቆይም አብርሃ እና አጽብሐ የተባሉት ነገሥታት ፲፪ መቅደስ ፸፪ አዕማድ ያላት የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን አሠርተውላታል። ቀጣዩ ቤተ መቅደስ በዐፄ አንበሳ ውድም ተሠርቷል፤ ይህን ደግሞ ግራኝ አቃጠለው፤ መልሰውም ዐፄ ፋሲል አሠርተውታል፤ አሁን ያለውን ደግሞ በዘመናዊ መንገድ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ አሠርተዋል፤ ይህን ተከትሎም የጽዮን በዓል በታላቅ ድምቀት ኅዳር ፳፩ ይከበራል።

ኢትዮጵያ ሀገረ እግዚአብሔር ናት ከምትባልባቸው ምክንያቶች አንዱ ይህ የጽላተ ሙሴ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ኅዳር ፳፩ ቀን በታላቅ ክብር ታከብረዋለች፡፡ በዚሁ ዕለት የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወዳጆች ምእመናን በዓሉን ለማክበርና ለመሳለም ወደ አክሱም ጽዮን ቤተ ክርስቲያን በብዛት ይገሠግሳሉ፡፡ ዕጣን፣ ጧፍ፣ ዘቢብና መባ ይሰጣሉ፡፡ ካህናቱም ከዋዜማው ጀምረው በከበሮና በጸናጽል ስብሐተ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፡፡ በድርሳነ ጽዮን መጽሐፍ እንደተገለጠው በጽዮን ፊት እንደ የመዓርጋቸው ቆመው ‹‹ዕግትዋ ለጽዮን ወህቀፍዋ፤ ጽዮንን ክበቧት፥ በዙሪያዋም ተመላለሱ›› የሚለውን መዝሙር ከዳዊት እያወጣጡ ይጸልያሉ፤ ይዘምራሉ፡፡ ፈጣሪያቸውን እያመሰገኑ የታቦተ ጽዮንን ተራዳኢነት በምእመናን ፊት ይመሰክራሉ፡፡ (መዝ. ፵፯፥፲፪)

ታቦት የአመቤታችን ምሳሌ ነውናም ነቢያት ስለ ክርስቶስ በተለያየ ኅብረት፣ ትንቢትና አምሳል እንደ ተናገሩ ሁሉ ክርስቶስ ስለሚገኝባት አማናዊት ድንግል ማርያምም ተናግረዋል፤ እግዚአብሔር ወልድ ወደዚህ ዓለም በሥጋ ማርያም ከመገለጡ በፊት ከእግዚአብሔር ተልከው ሕዝቡን ከአምልኮተ ጣዖትና ከገቢረ ኃጢአት እንዲጠበቅ የሚመክሩ፣ የሚያስተምሩና የሚያጽናኑ ነበሩ፡፡ (ሉቃ.፲፮፥፲፯፣ኢሳ.፵፥፩፣ኢሳ.፵፬፥፩-፲፩) የነቢያት ትንቢት ዋናው ዓላማም እግዚአብሔር አምላክ ሕዝቡን እንደተዋቸው እንደማይቀር፣ ወደዚህ ዓለም መጥቶ. ሰው ሆኖ ተገልጦ. ወንጌልን አስተምሮና ስለ እኛ መከራን ተቀብሎ እንደሚያድነን መግለጥ ነበር፡፡ በዚህም ስለ እግዚአብሔር ማደረያ እመቤታችን ትንቢት ተናግረዋል፡፡ (ኢሳ.፯፥፬፣ማቴ.፩፥፳፫፣ሚክ. ፭፥፪)

በታቦት ሰሌዳ ላይ ‹አልፋ ወዖ› የሚለው ስመ እግዚአብሔር እንደተቀረጸ ሁሉ በአማናዊቷ ታቦት በእመቤታችን ማሕፀንም ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀርጿል። በዚህ ዕለት በኢትዮጵያ የሚከበረው ታቦተ ጽዮን ባለችባት አክሱም ብቻ አይደለም። በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በታነጹ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በተለያዩ ቦታዎች ይከበራል።

ስለዚህም ተወዳጆች ሆይ! ጽዮንን እንክበባት! በእርሷ ምልጃና ጸሎት እንዲሁም ተራዳኢነት አምላካችን እግዚአብሔር ምሕረቱን ያወርድልን፣ ሰላምና ፍቅር ይሰጠን ዘንድ!

የአምላካችን የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የቅድስት ድንግል ማርያም አምላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን!
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም/ጽዮን ማርያም/ ዓመታዊ  በዓል አደረሳችሁ!!

ዕለቱን የሚመለከቱ ከታች ያሉት ሊንኮች በዜማ ወጥበብ ዘማኅበረ ቅዱሳን ቀጥታ የሚገኙ ሲሆን ከፍታችሁ እንድታደምጧቸው እንጋብዛችኋለን።

1"እናታችን ጽዮን"           
https://www.youtube.com/watch?v=HHEHdAARp-w

2"ትምክህተ ዘመድነ"          
https://www.youtube.com/watch?v=P_aVdVRVC3Q

3"ትውልድ ሁሉ"         
https://www.youtube.com/watch?v=di0mrqz3YgI

4"እኅትነ ይብልዋ"      
https://www.youtube.com/watch?v=XefxNuy_oco&t=35s

5. "ማርያም ድንግል"           
    https://www.youtube.com/watch?v=jdjGuA9cO_8&t=140s

6"የእመቤታችን የንስሐ መዝሙራት"  
     https://www.youtube.com/watch?v=I4pHvaYNRgo&t=567s

7.  "የሕይወት መሰላል"

https://youtu.be/FbvQdUXUthI?si=3tOZMVW1y6U1UfmC

8. "ዮም ንወድሳ ለማርያም "    
          https://www.youtube.com/watch?v=cM0O_B3YAdk

9."ማርያም አንቲ"

https://youtu.be/o4h4vZaO0O0?si=CeQKfk75lRzQ8fE3

10. ''ሰአሊ ለነ ቅድስት" የበገና መዝሙር

https://youtu.be/cBoPdinUTFg?si=g_k9GUEIAKun7Fkf

11. "ድንግል ወላዲተ ቃል'' የበገና መዝሙር

https://youtu.be/zKFAkFc3_2I?si=RJ4viqUpNu5uppOt

12."ስለ ድንግል ብሎ " የበገና መዝሙር

https://www.youtube.com/watch?v=lBP8JI3vJnM

13. "የእመቤታችን የቸብቸቦ መዝሙራት''

https://youtu.be/7EuDmMOvnsg?si=YRg2mpLRQfJvlOP-

14. "የድንግል ልዕልና" የበገና መዝሙር

https://youtu.be/WlBalfjtkRw?si=4ca0K35XeybqWGe2

15. "ድንግልም በምትወልድበት ወራት" የበገና መዝሙር

https://youtu.be/FHToIvZJBDQ?si=07WsIkfU5dDLjhl7

16. " የሲና ሐመልማል'' የንስሐ

https://youtu.be/5TrafbV4-Wc?si=hrpcueZxYSR2GalT

17. "መሠረተ ሕይወት "

https://youtu.be/__OmXeEG76w?si=e1Qxu_G1iDzM5RkI

18. "ክነፈ ርግብ"

https://youtu.be/9sEzWM-ZNDU?si=uuth3D_XvPlfgQgk

19. "አይ ይእቲ ዛቲ"

https://youtu.be/LfOtK25D5tQ?si=6hpgTbsZwTa10w66

20. "You Who Have Been Promised " የእንግሊዘኛ /አማናዊት ኪዳን/

https://youtu.be/ljrCdzxcMeI?si=_kBE1LkVP5CSE1LE

21. " Woossarkki Maariyaame" ወላይቲኛ መዝሙር

https://youtu.be/eOwb9oLQy3w?si=5moA79rRJVwNXwiS

22. "ምስጋና ንማርያም" የትግሪኛ መዝሙር

https://youtu.be/Y_7D54e6Irg?si=DVKDeVF-rWJ2NY_p

23. "የዐቢ ክብራ" የትግሪኛ መዝሙር

https://youtu.be/enGoXiGmxVg?si=yUP6W7-1jaSB2saX

24. "Yaa mana Waaqayyooየኦሮሚኛ መዝሙር  የንስሐ

https://youtu.be/R6C-UKPqOSU?si=FAXGo0CiGWZ5igHQ

25. "Maalumaan'' የኦሮሚፋ መዝሙር

https://youtu.be/CAz2RMDsf6o?si=BzZgbNnXWNMVwEOB

26. '' Qulqulleetti'' ኦሮሚፋ መዝሙር

https://youtu.be/xFm04BcVIR0?si=9CYtMt1FR56ZwiZj

27. በአባቶች ልመና/የበገና/

https://youtu.be/Qip4FYQsoHo?si=1MiyzezOuKowQ_U6


Youtube👇

ዜማ ወጥበብ ዘማኅበረ ቅዱሳን

https://www.youtube.com/channel/UC2U27bED0bj7ONXPNmBEKmA

Telegram 👇
ቴሌግራም  በቴሌግራም


ዜማ ወጥበብ ቴሌግራም ሊንክ
ዜማ ወጥበብ ቴሌግራም ሊንክ ይጫኑት
https://youtu.be/upsdW8bpf9Q?si=Lp8ibPWBdDMJZVeQ

ድንግል ሆይ/ወላዲተ አምላክ/
   

ወላዲተ አምላክ የሁሉ እመቤት
ለምኝልን ለእኛ ከልጅሽ ምሕረት
በአንቺ አማላጅነት በእርሱ ቸርነት
እንዲያወጣን ነፃ ከፍርድ ቅጣት 
ድንግል ሆይ ለምኝልን/2/

በበደል ተዳክሮ ፈቃደ ነፍሳችን
በምድራዊ ምኞት ናውዞ ልቦናችን
ፍቅርና ትኅትና ጠፍቶ ከፊታችን
ለሞት እንዳይሰጠን ይህ ክፉ ሥራችን 
ድንግል ሆይ ለምኚልን/2/ 

የምስኪኖች ተስፋ የደካሞች ኃይል
ጠውልገናል እና ጥላ ሁኝን ድንግል
እምነት ጨምሪልን ልቦናችን ይጽና
እመምላክ አብሪልን የመዳንን ፋና 
ድንግል ሆይ ለምኚልን/2/ 

ፍፁም እንዳናዝን እንዳናፍር ኋላ
ተነጥቀን እንዳንቀር ከዘላለም ተድላ
በፍቅርሽ መልሽን ከሲኦል ጎዳና
ድንግል መመኪያችን ተስፋችን ነሽና 
ድንግል ሆይ ለምኚልን/2/
✝️“አለሁ እኔ፣ ለወገኔ” ✝️
ለድጋፍዎ #የወገን ፈንድ አማራጭንም ይጠቀሙ!!
+++
ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ፣ ጠለምት፣ በየዳና ጃና አሞራ፣ እንዲሁም በዋግኸምራ ዞን ሰሃላና አካባቢው ባጋጠመው ድርቅ የተጎዱ ወገኖቼ ለመርዳት አስቸኳይ ድጋፍ እያሰባሰበ ይገኛል። እኔም የከበረ የሰው ሕይዎትን ለማትረፍ የተቻለኝን ድጋፍ አደርጋለሁ። እርስዎስ ?
ድጋፍ ለማድረግም፡-
በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
2. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
3. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
4. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
5. በአዋሽ ባንክ - 01329817420400 መጠቀም ይችላሉ።
በወገን ፈንድ ለመለገስ የተያያዘውን ሊንክ ይጫኑ።
https://www.wegenfund.com/causes/nu-badereqe-yatagodu-waganocaacenene-hheyete-eneta/
ለበለጠ መረጃ
• 09 84 18 15 44
• 09 43 00 04 03
የማኅበረ ቅዱሳን ቅዱሳን ሙያና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ
ሃያ አራቱ አለቆች (መጽሐፈ ስንክሳር)

ምስጋና ለሥሉስ ቅዱስ ይድረስና ሁልጊዜ በየዓመቱ በኅዳር ፳፬ ቀን እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን የካህናተ ሰማይ /ሱራፌ/ በዓልን እንድናከብር አባቶች ሥርዓትን ሠርተውልናል፡፡

ቅዱሳን መላእክት ሱራፌል እግዚአብሔር ለመላእክት መኖሪያነት ከፈጠራቸው ከሦስቱ ሰማዮች መካከል በኢዮር በሦስተኛው ከተማ የሚኖሩ መላእክት ናቸው፡፡ ሱራፌል የነገደ መላእክቱ የብዙ ቁጥራቸው መጠሪያ ሲሆን በነጠላ ስማቸው ሱራፊ (የአንዱ መልአክ መጠሪያ) ይባላሉ፡፡

ስያሜ

ሱራፊ የሚለው ቃል ‹‹የሚያነድ፣ የሚያጤስ፣ የሚያጥን፣ ዐጣኝ›› የሚል ትርጉም ሲኖረው ይኸውም አገልግሎታቸውን ይገልጻል፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፰፻፹፮) ቅዱሳን መላእክት ሱራፌል ሃያ አራቱ ካህናት፣ ሃያ አራቱ ሊቃናት (አለቆች)፣ አንዳንዴም ሃያ አራቱ ሽማግሌዎች ተብለው የሚጠሩ ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን የእውነት ካህናት የሆኑ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ የሆኑና ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከፍ ከፍ ያሉ መላእክት ናቸው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ‹‹በዙፋኑ ዙሪያም ሃያ አራት ዙፋኖች ነበሩ፤ በዙፋኖቹም ላይ ነጭ ልብስ ለብሰው፣ በራሳቸውም የወርቅ አክሊል፣ ደፍተው ሃያ አራት ሊቃናት ተቀምጠው ነበር›› በማለት ስለ እነርሱ ጽፏል፡፡ (ራእይ ፬፥፲፬)
ቁጥራቸው ሃያ አራት የመሆኑ

መጽሐፍት እና የቤተ ክርስቲያን መምህራን ካህናተ ሰማይ ቁጥራቸው ሃያ አራት የሆነበትን ምክንያት ሲያስተምሩ ሱራፌል በሃያ አራቱ ሰዓት ያለሟቋረጥ ለአምላክ ምስጋናና ጸሎት በማቅረብ ራሳቸውንም ፍጥረትንም ጠብቀው ዋጋቸውን ተቀብለው የሚኖሩ በመሆናቸው አምላካችን እግዚአብሔር ሃያ አራት አድርጓቸዋል በማለት ይናገራሉ፡፡ በተጨማሪ ደግሞ በብሉይ ኪዳን የእስራኤል ዘሥጋ መነሻ የሆኑት ዐሥራ ሁለቱን አበውና በሐዲስ ኪዳን ደግሞ የእስራኤል ዘነፍስ መሠረት የሆኑትን የቅዱሳን ሐዋርያትን ድምር ስለያዙ ቁጥራቸው ሃያ አራት ሆኗል፡፡ ለቤተ እስራኤል ዐሥራ ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች ምንጮች እንደሆኑ ለቤተ ክርስቲያንም ቅዱሳን ሐዋርያት ምንጭ /ነቅዕ/ ናቸውና፡፡ (መዝ.፲፯፥፲፭)

አገልግሎታቸው

ሱራፌል ‹‹ዐጠንተ መንበሩ ለልዑል›› በመባል ይጠራሉ፡፡ የካህን ሥራው መንበር ማጠን እንደሆነ እነርሱም ማዕጠንተ-ወርቃቸውን ይዘው፣ አክሊላቸውን ተቀዳጅተው፣ ስለሚያመሰግኑ ካህናተ-ሰማይ ተብለው ይጠራሉ፡፡ አእላፍ መላእክት ሲላላኩ፣ ኪሩቤል መንበሩን ተሸክመው ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› ሲሉ፣ ሠራዊተ-መላእክት ከፊቱ ቆመው ሲሰግዱ፣ ትጉሃን ሲያመሰግኑ፣ ሱራፌልም ማዕጠንተ ወርቃቸውን ይዘው መንበሩን እየዞሩ ያጥናሉ፡፡ ሥራቸውን በመንፈስ ቅዱስ የተመለከተው ቅዱስ ያሬድም ‹‹ፍቁራኒሁ ለአብ ኄራን መተንብላን እለ ይሥእሉ ምሕረተ ለውሉደ ሰብእ›› ይለናል (ኄራን መላእክት ለሰው ልጆች ምሕረትና ይቅርታን ይለምናሉ) ማለት ነው፡፡

በማዕጠንታቸውም ዘወትር ወደ አምላካችን የጻድቃንን ጸሎት፣ ምድራውያን ካህናት የሚሠውትን መሥዋዕት እና የሚያጥኑትን ዕጣን የሚያሳርጉም ቅዱሳን መላእክት ሱራፌል ናቸው፡፡ በቅዱሳን መላእክት ሱራፌል አገልግሎት ውስጥ ስድስቱ ክንፎቻቸው ሦስት ትእምርቶችን ይገልጻሉ፡፡ እነዚህም ትእምርተ ፍርሃት፣ ትእምርተ ተልእኮ እና ትእምርተ መስቀል ናቸው፡፡

ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ የእነርሱን ሁኔታ ሲገልጥ ‹‹ሱራፌል በዙሪያው ቆመው ነበር፤ ለእያንዳንዱም ስድስት ክንፍ ነበረው፤ በሁለት ክንፍ ፊቱን ይሸፍን ነበር፤ በሁለት ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር፤ በሁለት ክንፍ ይበርር ነበር፡፡ አንዱም ላንዱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር፡፡›› ብሏል (ኢሳ.፮፥፪-፫)

በሁለቱ ክንፋቸው ፊታቸውን መሸፈናቸው፣ በሁለቱ ክንፋቸው እግራቸውን መጋረዳቸው የመለኮቱ እሳትነት /ዋዕየ መለኮ/ እንዳያቃጥላቸው ነው፤ ያስ ቢሆን አካላቸው አይደለም ቢሉ ትእምርተ ፍርሀት ነው፤ አሁን ሰው ሾተል በመዘዙበት፣ ጦር በነጠቁበት ጊዜ እጁን እንደሚጋርድ ነው፡፡

ሁለት ክንፋቸውን ወዲያ እና ወዲህ ማድረጋቸው ትእምርተ ተልእኮ፣ ተልእኮ አለብን ማለታቸውን ይገልጻል፡፡ በሁለቱ ክንፋቸው ፊታቸውን በሁለቱ ክንፋቸው እግራቸውን ሲሸፍኑ በሁለቱ ክንፋቸው ጽንፍ እስከ ጽንፍ ሲበሩ በአንድነት ትእምርተ መስቀል ይሆናል፡፡

ቅዱሳን መላእክት ሱራፌል (ካህናተ ሰማይ) ዛሬ የእኛ ሕይወት ፍቅር በማጣት፣ በኃጢአት ከርፍቷልና በወርቅ ማዕጠንታቸው የፍቅርን ዕጣን አጥነውን፣ ከኃጢአታችንም ነጽተንና ሥራችን ሁሉ በጎ መዓዛ ኖሮት በሰላምና በመተሳሰብ ለመኖር ይርዱን፤ አሜን!

ምንጭ፡- መጽሐፍ ቅዱስ፣ ትንቢተ ኢሳይያስ ንባቡና ትርጓሜው (በአንድምታ)፣ መጽሐፈ ስንክሳር ፣ መጽሐፈ አሚን ወሥርዓት በመምህር ዶ/ር ዘበነ ለማ ፣ምሥጢረ ሰማይ ( መምህር ማዕበል ፈጠነ)፣ የአንቀጸ ብርሃን አንድምታ ትርጓሜ (መምህር ኃይለማርያም ዘውዱ)
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በማስመልከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤
**********

"ወዳጆች ሆይ፥ በእናንተ መካከል እንደ
እሳት ሊፈትናችሁ ስለሚሆነው መከራ ድንቅ ነገር እንደ መጣባችሁ አትደነቁ፤ ነገር ግን ክብሩ ሲገለጥ ደግሞ ሐሤት እያደረጋችሁ ደስ እንዲላችሁ፥ በክርስቶስ መከራ በምትካፈሉበት ልክ ደስ ይበላችሁ።" 1ኛ ጴጥርስ 4፥12:13

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን       

በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን፤ የጸጥታ ተቋማትም ጥቃቱን እንዲከላለሉ እንጠይቃለን።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአርሲ ዞን በሹርካ ወረዳ ሶሌ ሚካኤል፣ በዲገሎ ማርያም፣ በሮቤ እንደቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም አብያተክርስቲያናት ላይ በተለያዩ ጊዜያት 36 ኦርቶዶክሳዊያን በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸውን ማጣታቸውን ሀገረ ስብከቱ ባደረሰን መረጃ ለማወቅ ችለናል።

በዚሁ ጥቃት በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች 28 ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም 7ቱ ሴቶችና 21ዱ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኙበታል። በዛሬው ዕለት ደግሞ በዲገሉ ማርያም ቤተ ክርስቲያን 5 ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት ደግሞ ተቃጥሏል። 
2024/09/30 16:42:32
Back to Top
HTML Embed Code: