የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ
********
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሥላሴ ገ/መድኅንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክፍለ ሀገር በመቀሌ ከተማ ልዩ ቦታው በዓታ ለማርያም በተባለው ቦታ 1934 ዓ.ም ተወለዱ።
ፊደልና ንባብና የቃል ትምሕርት በመማር ለግብረ ዲቁና የሚያበቃቸውን ትምሕርት ከየኔታ ክንፈ ገብርኤል በመማር ማዕረገ ዲቁናን ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ዜማ ከየኔታ ተክለ ማርቆስ ማየ አንበሳ ገዳም ተንቤን፤ ቅኔ ከየኔታ ንጉሤ መነዌ ገዳም ተንቤን እንዲሁም ቅኔን ከየኔታ አክሊሉ ደበጋ ጎንደር ትርጓሜ መጻሕፍት፣ እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ማርያም ቀረፃ ማርያም ከምትባል ገዳም ፤ ቅኔና ትርጓሜ መጽሐፍት እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ልሣነ ወርቅ ጎጃም ፤ ቅኔ ከየኔታ ዲበኩሉ ጎጃም በሚገባ ከተማሩ በኋላ ለመምህርነት በቅተዋል፡፡
በተጨማሪም መዝገብ ቅዳን ከየኔታ ልዑል ቦረራ ሚካኤል ተምረዋል፡፡በወቅቱ የጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ የቅስናና የቁምስና ማዕረግ ተቀብለዋል፡፡ብፁዕነታቸው በሊቀ ጵጵስና በአክሱም፣በምሥራቅ ሐረርጌና በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም አገልግለዋል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን
********
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሥላሴ ገ/መድኅንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክፍለ ሀገር በመቀሌ ከተማ ልዩ ቦታው በዓታ ለማርያም በተባለው ቦታ 1934 ዓ.ም ተወለዱ።
ፊደልና ንባብና የቃል ትምሕርት በመማር ለግብረ ዲቁና የሚያበቃቸውን ትምሕርት ከየኔታ ክንፈ ገብርኤል በመማር ማዕረገ ዲቁናን ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በቀድሞ ስማቸው ሊቀ ሥልጣናት አባ ሐረገ ወይን ገብረ ሥላሴ ዜማ ከየኔታ ተክለ ማርቆስ ማየ አንበሳ ገዳም ተንቤን፤ ቅኔ ከየኔታ ንጉሤ መነዌ ገዳም ተንቤን እንዲሁም ቅኔን ከየኔታ አክሊሉ ደበጋ ጎንደር ትርጓሜ መጻሕፍት፣ እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ማርያም ቀረፃ ማርያም ከምትባል ገዳም ፤ ቅኔና ትርጓሜ መጽሐፍት እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ልሣነ ወርቅ ጎጃም ፤ ቅኔ ከየኔታ ዲበኩሉ ጎጃም በሚገባ ከተማሩ በኋላ ለመምህርነት በቅተዋል፡፡
በተጨማሪም መዝገብ ቅዳን ከየኔታ ልዑል ቦረራ ሚካኤል ተምረዋል፡፡በወቅቱ የጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ የቅስናና የቁምስና ማዕረግ ተቀብለዋል፡፡ብፁዕነታቸው በሊቀ ጵጵስና በአክሱም፣በምሥራቅ ሐረርጌና በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም አገልግለዋል።
የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን
👍71
ብፁዕ አቡነ ሰላማ በ ፲፱፻፷፬ ዓ.ም ወደ አርሲ ክፍለ ሀገር በመሄድ በወቅቱ የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በነበሩት በብፁዕ አቡነ ሉቃስ መልካም ፈቃድ በሀገረ ስብከቱ በማስተማር፣ የአውራጃ ሰባኬ ወንጌል በመሆን፣ የወረዳ ሊቀ ካህናት በመ ሆን በተለያዩ የኃላፊነት ሥራዎች ተመድበው በመሥራት ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል፤ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል፤ በዚሁ ሀገረ ስብከት ለ፳፪ ዓመታት በማስተማር ቆይተዋል፤ በዚህም ሰፊ ወቅት ብዙ ደቀ መዛሙርትን አውጥተው ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡
ብፁዕነታቸው ከአርሲ ሀገረ ስብከት በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ውቅያኖስ በሆነው እውቀታቸውና በቅድስናቸው ቤተ ክርስቲያንንም ሆነ ምእመናንን እንደሚጠቅሙ በማሰብ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በቅዱሳን ፓትርያርኮች ፈቃድና ትእዛዝ እየተሾሙ፦-
⇨ በቡራዩ ፄዴንያ ማርያም፣
⇨ በመተሐራ መድኃኔ ዓለም፣
-በቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤልና ሳሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣
⇨ በሰዓሊተ ምሕረት፣
⇨ በደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት በአስተዳዳሪነት ተመድበው ለበር ካታ ዓመታት በማስተማር በሚያስመንነው ስብከታቸው ብዙ አማ ንያንን አበርክተዋል፤ ለምናኔም አብቅተዋል፤ በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ በጸሎታቸው አያሌ ሕሙማንን ፈውሰዋል፧ ሰበካ ጉባኤን አጠናክረዋልº ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል፧ በተለይም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊቀ ሥልጣናት ሆነው ለ ዓመታት ያህል በአስተዳደሩበት ጊዜ ከፈጸሟቸው ተግባራት ዋና ዋናዎቹ ምእመናን በጣዕመ ስብከታቸውና በቅድስናቸው እየተማረኩ ለካቴድራሉ በሚያደርጉት የቦታና የገንዘብ ልግስና በርካታ የሆኑ የልማት ተግባራትን አከናውነዋል።
❖ በዚህም መሠረት በትምህርታቸው በጎ አድራጊዎችንና ምእመናንን በማስተባበር በካቴድራሉ ስም የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትና ከፍተኛ ክሊኒክ አሠርተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ አክ ሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተባርኮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡
⇨ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለ፭ ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በእን ጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም በአስተዳዳሪነት አገልግለዋል።
⇨ ብፁዕ አቡነ ሰላማ ሙሉ የቤተ ክርስቲያን ትምህርታቸውን አጠናቅቀው በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከተመደቡበት ጊዜ ጀምሮ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር በአብነት መምህርነታቸው በተለይም በቅኔ መምህርነታቸው በተለያዩ አህጉረ ስብከት ወንበር ዘርግተው በማስተማር እስከ ጵጵስና ደረጃ የደረሱ አያሌ ምሁራንን አፍርተው ለቤተ ክርስቲያን ያስረከቡ፣ በልዩ የስብከት ችሎታቸው የታወቁ ሰባክያነ ወንጌልን ያፈሩና አማንያንን ያበዙ፣ ቅድስናን ከሙያ ጋር አስተባብረው የያዙ፣ የቅዱሳኑ፣ የፍጹማኑ ረድኤት ያልተለያቸው፣ እንደ አባቶቻቸው ቅዱሳን ሐዋር ያት አጋንንትን የማስወጣትና ሌላውንም ደዌ ሁሉ የመፈወስ ሀብተ ፈውስ የተሰጣቸው፣ በጥላቸው ብቻ ሕሙማንን የሚፈ ውሱ፣ የበቁ (ፍጹም) አባት ነበሩ።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸው ተውህቦ የተወሰነ አይደለም ሀብተ ጸጋቸው ብዙ ነው! ጣዕመ ስብከታቸው ካለ መጠገቡም በላይ በተመስጦ በአካለ ሥጋ ያሳርጋልI ቅኔያቸውም ልዩ ጣዕም አለው ከማር ከወተት ይጣ ፍጣል! ፈጣሪያቸውን ብቻ አይደ ለም የሚያከብሩት፣ ሲበዛ ሰው አክባሪ ናቸው‥ ምንም ይሁን ምን በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠረውን ትልቁንም ትንሹንም ሁሉ በአክብሮት የሚወዱ አባት ነበሩ።
በአጠቃላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የቤተ ክርስቲያናችን ጸጋና በረከት ነበሩ።በዚህ ቅድስና ቸው፣ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሙሉ ችሎታቸው፣ በአብነት መምህርነታቸው በርካታ ምሁራንን በማፍራታቸውና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸው ባበረከቱት ሰፊ የሆነ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ተመዝነው ብቁና ፍጹም አባት ሆነው በመገኘታቸው ሐምሌ ፱ ቀን ፲፱፻፺፯ ዓ.ም በተደረገው የጳጳሳት ምርጫ ከሌሎች ዕጩ ቆሞሳት ጋር ተወዳድረው የድምፅ ብልጫ ስለ አገኙ የአክሱምና ማዕከላዊ ዞን ሃገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ ሆነው የተመደቡ ሲሆን ከታኅሣሥ ፱/ ፪ሺ፪ ዓ/ም ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከትን ደርበው እየሰሩ እስከ ግንቦት ፳፰/፪ሺ፭ ዓ/ም ድረስ ሐዋርያዊ ተግባራቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል።
ግንቦት ፳፰ /፪ሺ፭ ዓ/ም ከትግራይ ማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው በ ፪ሺ፮ ዓ/ም የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ፮ ዓመታት በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ከፍተኛ ሐዋርያዊ አገልግሎትን ፈጽመዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከህዳር ፳፻ ፲፪ዓ/ም ጀምሮ በድጋሚ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው በበአታቸው በመወሰን ሲያገለግሉ ቆይተው ባደረባቸው ሕመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም ፲፰ቀን፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም ይህን ዓለም በዕረፍተ ሥጋ ተለይተው ወደ ሰማያዊው አባታቸው ተጉዘዋል።
በረከታቸው ይደርብን
ብፁዕነታቸው ከአርሲ ሀገረ ስብከት በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ውቅያኖስ በሆነው እውቀታቸውና በቅድስናቸው ቤተ ክርስቲያንንም ሆነ ምእመናንን እንደሚጠቅሙ በማሰብ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በቅዱሳን ፓትርያርኮች ፈቃድና ትእዛዝ እየተሾሙ፦-
⇨ በቡራዩ ፄዴንያ ማርያም፣
⇨ በመተሐራ መድኃኔ ዓለም፣
-በቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤልና ሳሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣
⇨ በሰዓሊተ ምሕረት፣
⇨ በደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት በአስተዳዳሪነት ተመድበው ለበር ካታ ዓመታት በማስተማር በሚያስመንነው ስብከታቸው ብዙ አማ ንያንን አበርክተዋል፤ ለምናኔም አብቅተዋል፤ በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ በጸሎታቸው አያሌ ሕሙማንን ፈውሰዋል፧ ሰበካ ጉባኤን አጠናክረዋልº ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል፧ በተለይም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊቀ ሥልጣናት ሆነው ለ ዓመታት ያህል በአስተዳደሩበት ጊዜ ከፈጸሟቸው ተግባራት ዋና ዋናዎቹ ምእመናን በጣዕመ ስብከታቸውና በቅድስናቸው እየተማረኩ ለካቴድራሉ በሚያደርጉት የቦታና የገንዘብ ልግስና በርካታ የሆኑ የልማት ተግባራትን አከናውነዋል።
❖ በዚህም መሠረት በትምህርታቸው በጎ አድራጊዎችንና ምእመናንን በማስተባበር በካቴድራሉ ስም የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትና ከፍተኛ ክሊኒክ አሠርተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ አክ ሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተባርኮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡
⇨ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለ፭ ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በእን ጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም በአስተዳዳሪነት አገልግለዋል።
⇨ ብፁዕ አቡነ ሰላማ ሙሉ የቤተ ክርስቲያን ትምህርታቸውን አጠናቅቀው በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከተመደቡበት ጊዜ ጀምሮ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር በአብነት መምህርነታቸው በተለይም በቅኔ መምህርነታቸው በተለያዩ አህጉረ ስብከት ወንበር ዘርግተው በማስተማር እስከ ጵጵስና ደረጃ የደረሱ አያሌ ምሁራንን አፍርተው ለቤተ ክርስቲያን ያስረከቡ፣ በልዩ የስብከት ችሎታቸው የታወቁ ሰባክያነ ወንጌልን ያፈሩና አማንያንን ያበዙ፣ ቅድስናን ከሙያ ጋር አስተባብረው የያዙ፣ የቅዱሳኑ፣ የፍጹማኑ ረድኤት ያልተለያቸው፣ እንደ አባቶቻቸው ቅዱሳን ሐዋር ያት አጋንንትን የማስወጣትና ሌላውንም ደዌ ሁሉ የመፈወስ ሀብተ ፈውስ የተሰጣቸው፣ በጥላቸው ብቻ ሕሙማንን የሚፈ ውሱ፣ የበቁ (ፍጹም) አባት ነበሩ።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸው ተውህቦ የተወሰነ አይደለም ሀብተ ጸጋቸው ብዙ ነው! ጣዕመ ስብከታቸው ካለ መጠገቡም በላይ በተመስጦ በአካለ ሥጋ ያሳርጋልI ቅኔያቸውም ልዩ ጣዕም አለው ከማር ከወተት ይጣ ፍጣል! ፈጣሪያቸውን ብቻ አይደ ለም የሚያከብሩት፣ ሲበዛ ሰው አክባሪ ናቸው‥ ምንም ይሁን ምን በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠረውን ትልቁንም ትንሹንም ሁሉ በአክብሮት የሚወዱ አባት ነበሩ።
በአጠቃላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የቤተ ክርስቲያናችን ጸጋና በረከት ነበሩ።በዚህ ቅድስና ቸው፣ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሙሉ ችሎታቸው፣ በአብነት መምህርነታቸው በርካታ ምሁራንን በማፍራታቸውና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸው ባበረከቱት ሰፊ የሆነ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ተመዝነው ብቁና ፍጹም አባት ሆነው በመገኘታቸው ሐምሌ ፱ ቀን ፲፱፻፺፯ ዓ.ም በተደረገው የጳጳሳት ምርጫ ከሌሎች ዕጩ ቆሞሳት ጋር ተወዳድረው የድምፅ ብልጫ ስለ አገኙ የአክሱምና ማዕከላዊ ዞን ሃገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ ሆነው የተመደቡ ሲሆን ከታኅሣሥ ፱/ ፪ሺ፪ ዓ/ም ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከትን ደርበው እየሰሩ እስከ ግንቦት ፳፰/፪ሺ፭ ዓ/ም ድረስ ሐዋርያዊ ተግባራቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል።
ግንቦት ፳፰ /፪ሺ፭ ዓ/ም ከትግራይ ማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው በ ፪ሺ፮ ዓ/ም የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ፮ ዓመታት በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ከፍተኛ ሐዋርያዊ አገልግሎትን ፈጽመዋል።
ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከህዳር ፳፻ ፲፪ዓ/ም ጀምሮ በድጋሚ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው በበአታቸው በመወሰን ሲያገለግሉ ቆይተው ባደረባቸው ሕመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም ፲፰ቀን፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም ይህን ዓለም በዕረፍተ ሥጋ ተለይተው ወደ ሰማያዊው አባታቸው ተጉዘዋል።
በረከታቸው ይደርብን
👍22
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት #የብፁዕ_አቡነ_ሰላማ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ዕረፍትን በማስመልከት ያስተላለፉት አባታዊ የሐዘን መግለጫ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
«መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት:–ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?»
መዝሙር ፹፱፥፵፰
የትህትና፣ የጸሎት ሕይወት እና የመልካምነት ምሳሌ የነበሩት #ብፁዕ_አባ_ሰላማ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የሰማነው በታላቅ ሐዘን ነው።
ያለንበትን ፈተና የበዛበት ዘመን በጸሎት የሚያሻግሩ አባቶችን ማጣት ቤተ ክርስቲያንን የሚጎዳ ቢሆንም በቅዱስ መጽሐፍ ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ መኖር የሚችል ማን ነው? እንደተባለ ሰው በምድር ላይ የሚኖርበት ዘመን በእግዚአብሔር ዘንድ የተቆጠረ እና የተለካ በመሆኑ ብፁዕነታቸው ሃይማኖትን ጠብቀውና መልካሙን ገድል ፈጽመው ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር በክብር ተሸጋግረዋል።
ብፁዕነታቸው በዕረፍተ ሥጋ ከእኛ በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘን ቢሰማንም በሰማይ የሚጠብቃቸውን ክብር እያሰብን እንጽናናለን።
የብፁዕነታቸውን ነፍስ በቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት አጠገብ ያሳርፍልን!
ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውም መጽናናትን ያድልልን!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 18 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት
ዋሽንግተን ዲሲ አሜሪካ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
«መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት:–ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?»
መዝሙር ፹፱፥፵፰
የትህትና፣ የጸሎት ሕይወት እና የመልካምነት ምሳሌ የነበሩት #ብፁዕ_አባ_ሰላማ ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የሰማነው በታላቅ ሐዘን ነው።
ያለንበትን ፈተና የበዛበት ዘመን በጸሎት የሚያሻግሩ አባቶችን ማጣት ቤተ ክርስቲያንን የሚጎዳ ቢሆንም በቅዱስ መጽሐፍ ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ መኖር የሚችል ማን ነው? እንደተባለ ሰው በምድር ላይ የሚኖርበት ዘመን በእግዚአብሔር ዘንድ የተቆጠረ እና የተለካ በመሆኑ ብፁዕነታቸው ሃይማኖትን ጠብቀውና መልካሙን ገድል ፈጽመው ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር በክብር ተሸጋግረዋል።
ብፁዕነታቸው በዕረፍተ ሥጋ ከእኛ በመለየታቸው ጥልቅ ሐዘን ቢሰማንም በሰማይ የሚጠብቃቸውን ክብር እያሰብን እንጽናናለን።
የብፁዕነታቸውን ነፍስ በቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት አጠገብ ያሳርፍልን!
ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውም መጽናናትን ያድልልን!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ ይቀድስ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 18 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት
ዋሽንግተን ዲሲ አሜሪካ
👍40👎2
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ የተሰማትን ሐዘን ገለጸች።
👍11
የብፁዕ አቡነ ሰላማ ሥርዓተ ቀብር እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ዓ.ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።
********
መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት የብፁዕ አቡነ ሰላማን የቀብር ሥነሥርዓት በማስመልከት ቋሚ ሲኖዶስ ከቀትር በፊት አስቸኳይ ስብሰባ በማድረግ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዲፈጸም ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሠረት ነገ ቅዳሜ መስከረም ፲፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከቀኑ ፱ ሰዓት ላይየብፁዕነታቸው ክቡር አስከሬን ከሃሌ ሉያ ሆስፒታል በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በአበው ቆሞሳትና በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ጸሎት ከተደረገበት በኋላ ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ጉዞ በማድረግ ሥርዓተ ጸሎት ተደርሶ ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ፍትሐትና ሥርዓተ ማኅሌት ሲደረግበት ያድራል።
በማግስቱ እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ዓ.ም ጠዋት ሥርዓተ ቅዳሴው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ከተካሔደ በኋላ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ አበው መነኮሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎች ፣የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ታጅበው ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ገዳም በእግር ጉዞ ይደረጋል።
********
መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት የብፁዕ አቡነ ሰላማን የቀብር ሥነሥርዓት በማስመልከት ቋሚ ሲኖዶስ ከቀትር በፊት አስቸኳይ ስብሰባ በማድረግ ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከቅዳሴ በኋላ የብፁዕነታቸው ሥርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዲፈጸም ውሳኔ አስተላልፏል።
በዚህም መሠረት ነገ ቅዳሜ መስከረም ፲፱ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ከቀኑ ፱ ሰዓት ላይየብፁዕነታቸው ክቡር አስከሬን ከሃሌ ሉያ ሆስፒታል በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በአበው ቆሞሳትና በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ጸሎት ከተደረገበት በኋላ ወደ መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ጉዞ በማድረግ ሥርዓተ ጸሎት ተደርሶ ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ፍትሐትና ሥርዓተ ማኅሌት ሲደረግበት ያድራል።
በማግስቱ እሁድ መስከረም ፳ ቀን ፳፻፲፮ዓ.ም ጠዋት ሥርዓተ ቅዳሴው በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ከተካሔደ በኋላ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ አበው መነኮሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎች ፣የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ታጅበው ወደ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ገዳም በእግር ጉዞ ይደረጋል።
👍30
በካቴድራሉም ለብፁዕነታቸው የሚመጥን ሥርዓተ ጸሎት ተደርጎ የሕይወት ታሪካቸው ተነቦ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የማጽናኛ ቃለ ምዕዳን ተላልፎ ሲያበቃ ሥርዓተ ቀብሩ የሚፈጸም ይሆናል።
በሥርዓተ ጸሎቱ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ይገኛሉ።
የብፁዕነታቸው ጸሎትና ቢራኬ ይደርብን
ምንጭ:EOTC public relations
በሥርዓተ ጸሎቱ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ይገኛሉ።
የብፁዕነታቸው ጸሎትና ቢራኬ ይደርብን
ምንጭ:EOTC public relations
👍45
የብፁዕ አቡነ ሰላማ ክቡር አስከሬን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ጸሎተ ፍትሐት።
በረከታቸው ይደርብን።
**********************************
ፎቶ፦ መ/ሰአባ ኪሮስ ወልደ አብ
በረከታቸው ይደርብን።
**********************************
ፎቶ፦ መ/ሰአባ ኪሮስ ወልደ አብ
👍17
በአርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ምእመናን የደህንነት ስጋት ላይ መሆናቸውን ገለጹ።
መስከረም 15/2016 ዓ.ም በመስቀል ደመራ ዋዜማ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥቃት መድረሱ ይታወሳል።
(በቤተ ማርያም ተምትሜ)
(ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት)
+++++++++++++++++++++++++++++++
መስከረም 15/2016 ዓ.ም በኦሮምያ ክልል አርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ከምሽቱ 4 እስከ 5 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ 7 ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከጣቢያችን ቆይታ ያደረጉ የአካባቢው ምእመናን ተናግረዋል።
ድርጊቱን የፈጸሙት አካላት በሀገረ ስብከቱ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የቦሌ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደሪ በሆኑት ካህን ላይ መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ ግድያ ለመፈጸም ቢሞክሩም አስተዳደሪው በኋላ በር አምልጠው ሕይወታቸውን አትርፈዋል።
ይሁን እንጂ በዚህ በቃኝ ያላሉት ጥቃት ፈጻሚዎች ቤት ውስጥ ያገኙዋቸውን የአስተዳደሪውን ባለቤት ከእነ ልጃቸው በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን የአካባቢው ምእመናን ተናግረዋል።
በዚህ ጥቃትም ወንበር ዘርገተው የሚስተምሩ እንድ የአብነት ትምህረት ቤት መምህር ጨምሮ በአጠቃላይ 7 ኦርቶዶክሳውያን የተገደሉ ሲሆን 5 ምእመናን ካባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
ምእመናኑ በተደጋጋሚ በአካባቢው ላይ ኦርቶዶክስ ተኮር በሆነ መልኩ ለሚፈጸም ጥቃት መንስኤ የሆነው በአካባቢው በሕገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎችን መቆጣጣር ባለመቻሉ መሆኑንን ጠቅሰዋል።
መስከረም 15/2016 ዓ.ም በመስቀል ደመራ ዋዜማ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ጥቃት መድረሱ ይታወሳል።
(በቤተ ማርያም ተምትሜ)
(ማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት)
+++++++++++++++++++++++++++++++
መስከረም 15/2016 ዓ.ም በኦሮምያ ክልል አርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ከምሽቱ 4 እስከ 5 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ 7 ኦርቶዶክሳውያን መገዳላቸውን ከጣቢያችን ቆይታ ያደረጉ የአካባቢው ምእመናን ተናግረዋል።
ድርጊቱን የፈጸሙት አካላት በሀገረ ስብከቱ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የቦሌ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደሪ በሆኑት ካህን ላይ መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ ግድያ ለመፈጸም ቢሞክሩም አስተዳደሪው በኋላ በር አምልጠው ሕይወታቸውን አትርፈዋል።
ይሁን እንጂ በዚህ በቃኝ ያላሉት ጥቃት ፈጻሚዎች ቤት ውስጥ ያገኙዋቸውን የአስተዳደሪውን ባለቤት ከእነ ልጃቸው በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን የአካባቢው ምእመናን ተናግረዋል።
በዚህ ጥቃትም ወንበር ዘርገተው የሚስተምሩ እንድ የአብነት ትምህረት ቤት መምህር ጨምሮ በአጠቃላይ 7 ኦርቶዶክሳውያን የተገደሉ ሲሆን 5 ምእመናን ካባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ለጣቢያችን ተናግረዋል።
ምእመናኑ በተደጋጋሚ በአካባቢው ላይ ኦርቶዶክስ ተኮር በሆነ መልኩ ለሚፈጸም ጥቃት መንስኤ የሆነው በአካባቢው በሕገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎችን መቆጣጣር ባለመቻሉ መሆኑንን ጠቅሰዋል።
👍40
አሁን በደረሰው ጉዳት ምክንያትም በአካባቢው ቤተክርስቲያን የምትሰጠው አገልግሎት መቋረጡን ገልጸዋል።
በዚህም የአካባቢው ምእመናን የመኖር ህልውናቸው አደጋ ላይ መሆኑን በመጥቀስ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስጋታችንን ተረድቶ ጥቃቱ እንዲቆም ከሚመለከተው አካል ጋር ተገቢውን ስራ ካልከወነ ዛሬ በአባቶቻችን፣ ወንድም እና እህቶቻችን ላይ የደረሰው ዕጣ ነገ በእኛ ላይ እንደማይደርስ ምንም ዋስትና የለንም ብለዋል።
በዚህም የአካባቢው ምእመናን የመኖር ህልውናቸው አደጋ ላይ መሆኑን በመጥቀስ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስጋታችንን ተረድቶ ጥቃቱ እንዲቆም ከሚመለከተው አካል ጋር ተገቢውን ስራ ካልከወነ ዛሬ በአባቶቻችን፣ ወንድም እና እህቶቻችን ላይ የደረሰው ዕጣ ነገ በእኛ ላይ እንደማይደርስ ምንም ዋስትና የለንም ብለዋል።
👍40