በሰሜን ምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የደረጃ ሁለት ተተኪ መምህራን ሥልጠና መጠናቀቁን ደብረ ማርቆስ ማእከል አስታወቀ
ሐምሌ ፲፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ደብረ ማርቆስ ማእከል ግቢ ጉባኤ ማስተባበሪያ አዘጋጅነት ከተለያዩ የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲ ለተዉጣጡ ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለሃያ ስድስት ተከታታይ ቀናት እየተሰጠ የቆየው የደረጃ ሁለት ተተኪ መምህራን ሥልጠና የምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ኤሊያስ ታደሰ በተገኙበት አስመርቋል።
ተመራቂ ሠልጣኞች ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ከቡሬ ካምፓስ፣ከጤና ካምፓስ እና ከተለያዩ የከተማ ግቢ ጉባኤ የተወጣጡ ቁጥራቸው 36 መሆናቸው ተገልጿል።
ሠልጣኞቹ በቆይታቸው ነገረ ቤተክርስቲያን ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ኦርቶዶክሳዊ የሕይወት ክህሎት፣የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣የስብከት ዘዴ፣ሕይወትና ክህሎት፣ ምሥጢራትና ሥርዓት፣ ነገረ-ማርያም እና ሌሎች ሥልጠናዎች እንደተሰጠም ተመላክቷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ቆሞስ አባ ኤሊያስ እንደገለጹት የተካሄደው ሥልጠና እጅግ ጠቃሚ የሆነና ሊበረታታ የሚገባው መሆኑን ጠቅሰው የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው በማለት ሠልጣኞች በተሰጠው ሥልጠና እግዚአብሔርን በመፍራት፣ ሕይወታቸውን በመምራት፣ መክሊታቸውን በማትረፍ በሚሄዱበት ሁሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን፣ ግቢ ጉባኤዎቻቸውን፣ ወላጆቻቸውንና አገራቸውን እንዲያገለግሉ የአደራ መልእክትና አባታዊ ቡራኬ ሰጥተዋል።
ሐምሌ ፲፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ደብረ ማርቆስ ማእከል ግቢ ጉባኤ ማስተባበሪያ አዘጋጅነት ከተለያዩ የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲ ለተዉጣጡ ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለሃያ ስድስት ተከታታይ ቀናት እየተሰጠ የቆየው የደረጃ ሁለት ተተኪ መምህራን ሥልጠና የምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ኤሊያስ ታደሰ በተገኙበት አስመርቋል።
ተመራቂ ሠልጣኞች ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ከቡሬ ካምፓስ፣ከጤና ካምፓስ እና ከተለያዩ የከተማ ግቢ ጉባኤ የተወጣጡ ቁጥራቸው 36 መሆናቸው ተገልጿል።
ሠልጣኞቹ በቆይታቸው ነገረ ቤተክርስቲያን ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ኦርቶዶክሳዊ የሕይወት ክህሎት፣የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣የስብከት ዘዴ፣ሕይወትና ክህሎት፣ ምሥጢራትና ሥርዓት፣ ነገረ-ማርያም እና ሌሎች ሥልጠናዎች እንደተሰጠም ተመላክቷል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ቆሞስ አባ ኤሊያስ እንደገለጹት የተካሄደው ሥልጠና እጅግ ጠቃሚ የሆነና ሊበረታታ የሚገባው መሆኑን ጠቅሰው የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው በማለት ሠልጣኞች በተሰጠው ሥልጠና እግዚአብሔርን በመፍራት፣ ሕይወታቸውን በመምራት፣ መክሊታቸውን በማትረፍ በሚሄዱበት ሁሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን፣ ግቢ ጉባኤዎቻቸውን፣ ወላጆቻቸውንና አገራቸውን እንዲያገለግሉ የአደራ መልእክትና አባታዊ ቡራኬ ሰጥተዋል።
❤31🙏4
እንጅባራ ማእከል 19ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን ገለጸ
ሐምሌ ፳፩/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በእንጅባራ ማእከል 19ኛ ዓመት 19ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ከሐምሌ 18 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት ማካሄዱን ገልጿል።
በጉባኤው የኮሶበር መንበረ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አማረ ወንዴ ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ሰሜን ምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ተወካዮች ፣ የወረዳ ማእከላት ተወካዮች፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰ/ት/ቤት አንድነት ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የማእከሉ አባላት ተግኝተዋል።
የኮሶበር መንበረ ሥላሴ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አማረ ወንዴ እንደተናሩት ማኀበረ ቅዱሳን የትህትና እና የሥርዓት ባለቤት ነው ስለሆነም ከሰ/ት/ቤቶች ከልዩ ልዩ በጎ ማኅበራት ከገዳማት እና ከጉባኤ ቤቶች እና ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በመግባባት እና በመደማመጥ ለአንዲት ቅድስት ሐዋርያዊት እና ኩላዊት ቤተክርስቲያን ተግታችሁ እንድታገለግሉ ሲሉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም የማእከሉ ነባር አባላት አቶ ተስፋየ ማኅበረ ቅዱሳን እኔን ለአለሁበት ያደረሰኝ መገለጫዬ ነዉ በማለት በማኅበረ ቅዱሳን እንጅባራ ማእከል ስም ለኮሶበር ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤት በተለያዩ ሊቃዉንት የተፃፉ 27 መፅሐፎችን በስጦታ አበርክተዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን እንጅባራ ማእከል ሰብሳቢ አቶ ይበልጣል አበጀ ለጠቅላላ ጉባኤው መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን ያመሰገኑ ሲሆን ልዪ አስተዋፅኦ ለአደረጉ አካላት የሰርተፍኬት እና ስጦታዎችን አበርክተዋል።ጠቅላላ ጉባኤው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በመወያየትና ውሳኔዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።
በተመሳሳይ ደባርቅ ማእከል 2ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን አስታውቋል።
ሐምሌ ፳፩/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በእንጅባራ ማእከል 19ኛ ዓመት 19ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ከሐምሌ 18 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት ማካሄዱን ገልጿል።
በጉባኤው የኮሶበር መንበረ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አማረ ወንዴ ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ሰሜን ምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ተወካዮች ፣ የወረዳ ማእከላት ተወካዮች፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰ/ት/ቤት አንድነት ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የማእከሉ አባላት ተግኝተዋል።
የኮሶበር መንበረ ሥላሴ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አማረ ወንዴ እንደተናሩት ማኀበረ ቅዱሳን የትህትና እና የሥርዓት ባለቤት ነው ስለሆነም ከሰ/ት/ቤቶች ከልዩ ልዩ በጎ ማኅበራት ከገዳማት እና ከጉባኤ ቤቶች እና ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በመግባባት እና በመደማመጥ ለአንዲት ቅድስት ሐዋርያዊት እና ኩላዊት ቤተክርስቲያን ተግታችሁ እንድታገለግሉ ሲሉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም የማእከሉ ነባር አባላት አቶ ተስፋየ ማኅበረ ቅዱሳን እኔን ለአለሁበት ያደረሰኝ መገለጫዬ ነዉ በማለት በማኅበረ ቅዱሳን እንጅባራ ማእከል ስም ለኮሶበር ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤት በተለያዩ ሊቃዉንት የተፃፉ 27 መፅሐፎችን በስጦታ አበርክተዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን እንጅባራ ማእከል ሰብሳቢ አቶ ይበልጣል አበጀ ለጠቅላላ ጉባኤው መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን ያመሰገኑ ሲሆን ልዪ አስተዋፅኦ ለአደረጉ አካላት የሰርተፍኬት እና ስጦታዎችን አበርክተዋል።ጠቅላላ ጉባኤው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በመወያየትና ውሳኔዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።
በተመሳሳይ ደባርቅ ማእከል 2ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን አስታውቋል።
❤2
ባሌ ሮቤ ማእከልየመጀመሪያ ዙር የርቀት ትምህርት ተማሪዎች እና አንደኛ ደረጃ ተተኪ መምህራንን አስመረቀ።
ሐምሌ ፳፩/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ዋና ክፍል ለአንድ ዓመት መሠረታዊ የርቀት ትምህርት በአፋን ኦሮሞ እና በአማርኛ ቋንቋ በሞጁል በመጀመሪያ ዙር 35 ተማሪዎችን እና ለሁለት ወራት ሲያሠለጠናቸው የቆዩ 25 አንደኛ ደረጃ ተተኪ መምህራንን በሮቤ ፈለገ ብርሃን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአባቶች ቡራኬ አስመርቋል።
በምረቃ መርሐ ግብሩ የሮቤ ከተማ እና አካባቢዋ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አዕላፍ ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርኤል እና የወረዳ ቤተ ክህነቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ መምህር ለታ ግርማ፣ የሮቤ ፈለገ ብርሃን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መምህር አብረሐም ግርማ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል ሥራ አስ ፈጻሚ ፣ተማራቂዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ዋና ክፍል ተጠሪ መምህር ተስፋዬ ኮማ ማእከሉ በ5 ወረዳ ማእከላት አስተባባሪነት 35 ተማሪዎችን በመሠረታዊ የርቀት ትምህርት በሞጁል አሰተምሮ ያስመረቀ ሲሆን ከ148 በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ እንደሚገኝ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት በሚያስተላልፉበት ወቅት ገልጸዋል።
ከተማራቂዎች ከ1ኛ -3ኛ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ሠልጣኞች የሽልማት መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን በመጨረሻም ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጾ ላደረጉ አካላት የምስጋና እና ለተመራቂዎች የምስክር ወረቀት በሊቀ አዕላፋት ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርኤል ተበርክቶላቸዋል።
ሐምሌ ፳፩/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ዋና ክፍል ለአንድ ዓመት መሠረታዊ የርቀት ትምህርት በአፋን ኦሮሞ እና በአማርኛ ቋንቋ በሞጁል በመጀመሪያ ዙር 35 ተማሪዎችን እና ለሁለት ወራት ሲያሠለጠናቸው የቆዩ 25 አንደኛ ደረጃ ተተኪ መምህራንን በሮቤ ፈለገ ብርሃን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአባቶች ቡራኬ አስመርቋል።
በምረቃ መርሐ ግብሩ የሮቤ ከተማ እና አካባቢዋ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አዕላፍ ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርኤል እና የወረዳ ቤተ ክህነቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ መምህር ለታ ግርማ፣ የሮቤ ፈለገ ብርሃን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መምህር አብረሐም ግርማ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል ሥራ አስ ፈጻሚ ፣ተማራቂዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል ስብከተ ወንጌል አገልግሎት ዋና ክፍል ተጠሪ መምህር ተስፋዬ ኮማ ማእከሉ በ5 ወረዳ ማእከላት አስተባባሪነት 35 ተማሪዎችን በመሠረታዊ የርቀት ትምህርት በሞጁል አሰተምሮ ያስመረቀ ሲሆን ከ148 በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ እንደሚገኝ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክት በሚያስተላልፉበት ወቅት ገልጸዋል።
ከተማራቂዎች ከ1ኛ -3ኛ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ሠልጣኞች የሽልማት መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን በመጨረሻም ለመርሐ ግብሩ መሳካት አስተዋጾ ላደረጉ አካላት የምስጋና እና ለተመራቂዎች የምስክር ወረቀት በሊቀ አዕላፋት ቆሞስ አባ ክንፈ ገብርኤል ተበርክቶላቸዋል።
❤12