Telegram Web Link
በማኅበረ ቅዱሳን የከሚሴ ወረዳ ማእከል የ2017 ዓ.ም በዓለ መስቀል ከከሚሴ ማረሚያ ቤት ታራሚዎች ጋር አከበረ።

የከሚሴ ወረዳ ማእከል ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ወርቁ ጌቶ ለታራሚዎች ባስተላለፉት መልእክት ተስፋንና ጽናት ተጎናጽፈው ሊኖሩ እንደሚገባና ወረዳ ማእከሉም የጸሎትና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል፡፡

ወረዳ ማእከሉ በዓሉን ከታራሚዎች ጋር ያሳለፈው ለ7ኛ ጊዜ ሲሆን በየዓመቱ ከሌሎች መንፈሳዊ ማኅበራት፤ሰንበት ትምህርት ቤቶ ችና አጋር አካላት ጋር በመተባበር የመስቀል ፤ የልደት፤ የትንሳኤና የጥምቀት በዓልን አብሮ ያከብራል።

ታራሚዎች ወረዳ ማእከሉ በዓሉን ከነርሱ ጋር በማሳለፉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው በየክብረ በዓሉ ብትጎበኙንና መዝሙርም ብታስጠኑን ሲሉ አስተያየት ሰጥተዋል።

በዕለቱ የማእከሉ ሥራ አስፈጻሚዎች፣ የወረዳ ማእከሉ ዘማሪዎችና መምህራነ ወንጌል ተገኝተዋል።
2024/09/28 12:15:59
Back to Top
HTML Embed Code: