Telegram Web Link
የነቢያት ሥራ

ትንቢት ይናገራሉ፤ ሕዝቡን ይመክራሉ፤ ያስተምራሉ፤ ይገሥፃሉ እንዲሁም ያጽናናሉ፡፡ ‹‹አጽናኑ፥ ሕዝቤን አጽናኑ›› እንዳለ፡፡ (ኢሳ.፵፥፩) በእግዚአብሔር ውሳኔ ስለ ሚፈጸሙ ድርጊቶች ስለ መንግሥታት፣ ስለ ስለ ሕዝቡ፣ ስለ ኀጢአት፣ ወደ ፊት ስለሚፈጸሙ ክስተቶች ወዘተ በምሳሌ ወይም በድርጊት ይገልጹ ነበር፡፡ (ኢሳ.፭፥፩፣ኤር.፩፥፲፱) ስለዚህ ነቢይ ማለት አፈ እግዚአብሔር፣ መምህር፣ ሰባኪ ማለትም ነው፡፡ ስያሜውም መንፈሰ ትንቢት ላደረባቸው፣ ራእይን የማየት ጸጋ ለተሰጣቸው እውነተኛ ነቢያት የሚሰጥ ስያሜ ነው፡፡

የነቢያት አከፋፈል

ነቢያት ብዙ ወገን ናቸው፡፡ ቀደምት ነቢያት ደኃርት ነቢያት፣ ዐበይት ነቢያት ደቂቀ ነቢያት፣ እውነተኛ ነቢያት ሐሰተኛ ነቢያት፣ ወንድ ነቢያት ሴት ነቢያት፣ የቃል ነቢያት የጽሑፍ ነቢያት ወዘተ እየተባሉ ይከፈላሉ፡፡

ከአዳም እስከ ዳዊት ያሉትን ነቢያት ብዙ ጊዜ ቀደምት ነቢያት እያሉ ይጠሯቸዋል፡፡ በአጠቃላይ አበው ቅዱሳን ነቢያትን በአራት ከፍለን እንማራቸዋለን፡፡

፩. ዐሥራ አምስቱ አበው ነቢያት
፪. አራቱ ዐበይት ነቢያት፤
፫. ዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት እና
፬. ካልአን ነቢያት ናቸው፡፡
፩. ዐሥራ አምስቱ አበው ነቢያት
ዋና ዋናዎቹ አባታችን አዳም፣ ሴት፣ ሔኖስ፣ ቃይናን፣ መላልኤል፣ ያሬድ፣ ሄኖክ፣ ማቱሳላ፣ ላሜህ፣ ኖኅ፣ አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ፣ ሙሴ፣ ሳሙኤል ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ በየወገናቸው ሀብተ ትንቢት ተሰጥቷቸው ኃላፍያትን፣ መጻእያትን ሲናገሩ፣ ሕዝቡን ሲመክሩ፣ ሲያሰተምሩ፣ ሲያስጠነቅቁ፣ ሲያጽናኑ የነበሩ አበው ናቸው፡፡ ለምሳሌ ያህል፡- የመጀመሪያዎቹን ዐሥሩን አበው ከአዳም እስከ ኖኅ ያሉትን ብንወስድ፣ በደብር ቅዱስ ሆነው ልጆቻቸውን ሲመክሩ፣ ከደቂቀ ቃኤል እንዳይደባለቁ፣ ቅድስናቸውን እንዲጠብቁ፣ በደቂቀ ቃኤል ምክንያት ምድሪቱ በማየ አይኅ እንደምትጠፋ አስቀድመው እንደተናገሩ በገድለ አዳምና በመጽሐፈ ቀሌምንጦስ ላይ በሰፊው ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡

፪. አራቱ ዐበይት ነቢያት
ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ፣ ሕዝቅኤልና ዳንኤል ናቸው፡፡

፫. ዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት
ሆሴዕ፣ አሞጽ፣ ሚክያስ፣ ዮናስ፣ ናሆም፣ አብድዩ፣ ሶፎንያስ፣ ሐጌ፣ ኢዩኤል፣ ዕንባቆም፣ ዘካርያስና ሚልክያስ ናቸው፡፡ ዓበይትና ደቂቅ መባላቸው በምሥጢር ሳይሆን በይዘት ሰፊና አነስ ያለ ትንቢት ከመናገር አንጻር ነው፡፡

፬. ካልኣን ነቢያት
ኢያሱ፣ ሶምሶን፣ ዮፍታሔ፣ ጌዴዎን፣ ዳዊት፣ ሰሎሞን፣ ኤልያስ፣ ኤልሳዕ ወዘተ ናቸው፡፡

ነቢያት በከተማና በዘመን ጭምር ይከፈላሉ፡፡ ለምሳሌ በከተማ የይሁዳ፣ የሠማርያ፣ የባቢሎን ምርኮ ነቢያት ወዘተ እየተባሉ ሲከፈሉ፣ በዘመን ደግሞ
✍️ ከአዳም እስከ ዮሴፍ የዘመነ አበው ነቢያት፤
✍️ ከሙሴ እስከ ሳሙኤል የዘመነ መሳፍንት ነቢያት፤
✍️ ከዳዊት እስከ ዘሩባቤል የዘመነ ነገሥት ነቢያት፤
✍️ ከዘሩባቤል እስከ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ የዘመነ ካህናት ነቢያት እየተባሉ ይጠራሉ፡፡

ነቢያት የሚከፈሉበት ሌላው አከፋፈል ደግሞ የጽሑፍ ነቢያትና የቃል ነቢያት ሲሆን የጽሑፍ ማለት የተናገሩት የትንቢት ቃል በጽሑፍ የሰፈረ፣ የተጻፈ ሲሆን ከኢሳይያስ እስከ ነቢዩ ሚልክያስ ያሉትን ዐሥራ ስድስቱን ነቢያት የሚያመለክት ነው፡፡ እነዚህም አራቱ ዐበይትና ዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ያልናቸው ናቸው፡፡

የቃል ነቢያት የሚባሉት ደግሞ ትንቢት ተናግረዋል፤ ግን የተናገሩት ትንቢት በጽሑፍ ያልሰፈረ ያልተጻፈ ለማለት ነው፡፡ እንደ ምሳሌ የሚወሰዱት ነቢዩ ጋድ፣ ኤልያስ፣ ኤልሳዕ፣ ናታን፣ ወዘተ፡፡

ሌላኛው አከፋፈል ደግሞ ወንድ ነቢያትና ሴት ነቢያት የምንለው ሲሆን ከላይ በተለያየ መልኩ የገለጽናቸው ወንድ ነቢያት ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ በርካታ ሴት ነቢያትም መኖራቸውን እንረዳለን፡፡ ከእነዚህም መካከል የሙሴ እኅት ማርያም (ዘፀ.፲፭፥፳) የሰፊዶት ሚስት ዲቦራ (መሳ.፬፥፬)፣ በኢዮስያስ ዘመነ መንግሥት የነበረችው ሕልዳና (፪ኛነገ.፳፪፥፲፬)፣ ነቢይት ሐና (ሉቃ.፪፥፴፮)፣ የፊልጶስ አራት ደናግል ሴት ልጆች ወዘተ ሴት ነቢያት ናቸው፡፡(የሐዋ.ሥ. ፳፩፥፱፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት)

እነዚህ ሁሉ የጠቀስናቸው ሀብተ ትንቢት ያደረባቸው፣ አፈ እግዚአብሔር ሆነው የእግዚአብሔርን ቃል ለሕዝቡም ለነገሥታቱም ሲያድረሱ፣ ሲያስተምሩ፣ ሲመክሩ፣ ሲዘክሩ፣ ሲያጽናኑ አልፎም ሲገሥፁ የነበሩ ነቢያት ሲሆኑ እውነተኞች ነቢያት ናቸው፡፡ ያናገራቸውም መንፈስ ቅዱስ ሲሆን የተናገሩት ሁሉ የተፈጸመላቸው ናቸው፡፡ ከዚሁ ጋር አብሮ የሚታየው ሌላኛው ዓይነት አከፋፈል እውነተኛ ነቢያትና ሐሰተኛ ነቢያት ተብሎ ነው፡፡

ውድ አንባብያን! ሐሰተኛ ነቢያት በዘመናችን እንደ አሸን የፈሉበት ዘመን በመሆኑ ስለ ሐሰተኛ ነቢያት መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? ሐሰተኛ የሚባሉትስ ከምን አንጻር ነው? የሚለውን በክፍል ሁለት እናዳርሳችኋለን፤ ቸር እንሰንብት!
ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት ከኅዳር 15 አስከ21 ቀን 2016 ዓ.ም የሚካሔደው የምህላና የጸሎት መርሐ ግብር ከላይ በተጠቀሱት ሰባት ቀናት ከማለዳው 12:00 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 1:00 ሰዓት በምሽት መርሐ ግብር ደግሞ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ድረስ የሚከናወን ሲሆን ሕዝበ ክርስቲያኑ በየ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ በመገኘት በመርሐ ግብሩ ላይ እንዲሳተፍ እየገለጸ አጠቃላይ መርሐ ግብሩ ቀደም ሲል በተሰጠው መግለጫ መሰረት የሚፈጸም መሆኑን ያስታውቃል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት
የማኀበረ ቅዱሳን ዋና ማእከል ምዕራፍ ሁለት የሕንጻ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናወነ

ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን በኹለንተናዊ አቅሟ እንድትጠናከር ለማድረግ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። አገልግሎቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ የመጣው ማኅበሩ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ማስፈጸም የሚችሉ ማእከላት በማቋቋም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ላይ ይገኛል።

ማኅበሩ ዘመኑ የሚጠይቀውን የአገልግሎት መንገድ በመከተል በዘመናዊ አሠራር ቤተ ክርስቲያንን ማገዝ የሚችሉ በርካታ አሠራሮችን ወደ ተግባር እያስገባ ሲሆን ለዚህ ተግባር የሚያግዙ የሰው ኃይል እና የግብዓት ማሟላት ላይ በትኩረት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።ለዚህ ማሳያ የሚሆነው ደግሞ አሁን ግባታውን ለመጀመር በዝግጅት ላይ የሚገኘው የምዕራፍ ሁለት የማኅበሩ ሕንጻ ማስፋፊያ ነው።

ማኅበሩ ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ የተነገረለት አዲሱ የማኅበሩ ሕንጻ የመሬት ወለልን ጨምሮ 14 ወለሎች እንደሚኖረው የተነገረለት ሲሆን ኅዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም ግንባታውን ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተከናውኗል።
የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማስፈጸም ከፈተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ 25 ተተኪ መምህራን ተመረቁ።

በማኅበረ ቅዱሳን እና ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ ወገብረ ክርስቶስ ቤተ ከርስቲያን ፈለገ ሰላም ሰ/ት/ቤት ትብብር ከቤንች ሸኮ፣ ሸካ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት የመጡ 25 ሠልጣኞች በዛሬው ዕለት ተመርቀዋል።

ለ15 ተከታታይ ቀናት የተለያዩ ሥልጠናዎችን ሲወስዱ የቆዩት መምህራኑ በዛሬው ዕለት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ አርያም መንግሥቱ ዘለዓለም እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመርቀዋል።

በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት መልአከ አርያም መንግሥቱ ዘለዓለም  በጠረፋማ አካባቢ ያሉ ምእመናንን ለማስተማር እና ያላመኑትን በማሳመን ለማስጠመቅ የሚደረገውን ጥረት ሁሉም የቤተክርስቲያን ባለድርሻ አካላት  በባለቤትነት ሊያግዙ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ዛሬ የተመረቁት ሠልጣኞች የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት እና ቀኖና ተረድተው እንዲያገለግሉ ለማድረግ የሚችሉ ትምህርቶችን መስጠት መቻሉን ገልጸው የደብሩ አስተዳደር ከሰንበት ትምህርት ቤቱ እና ከምእመናን ጋር በመሆን በቀጣይ 72 ሠልጣኞችን ከተለያዩ አካባቢዎች ተቀብለው ለማሠልጠን ቃል ገብተዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ምክትል ኃላፊ መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን 2014 እና 2015 ዓ.ም ሐዋርያዊ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በሠራው ሥራ 86,582 ኢ አማንያንን በማስጠመቅ የቤተ ክርስቲያን ልጅነት እንዲያገኙ አድርጓል ብለዋል።

ም/ኃላፊው እንደገለጹት ዛሬ የተመረቁት ሠልጣኞች በቤንችኛ፣ ካፊ ኖኖ እና ሸኮኛ ቋንቋዎች ሐዋርያዊ አገልግሎት እንደሚሠጡ ተናግረዋል።
በመጨረሻም ማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊወ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ጽ/ቤት እና የፈለገ ሰላም ሰ/ት/ቤት የሠልጣኞቹን ምግብ ትራንስፖርት እና አስፈላጊ ወጪዎችን በመሸፈን ላደረጉት አስተዋጽኦ ምስጋናውን ያቀርባል ብለዋል።

በዚህ ሥልጠና ላይ የተካፈሉት ከደቡብ ቤንች ወረዳ10 ተሳታፊዎች ፣ ከሰሜን ቤንች ወረዳ 5 ተሳታፊዎች፣ ከጊዲ ቤንች ወረዳ 7 ተሳታፊዎች፣ ከሼይ (ሸዋ) ቤንች ወረዳ 3 ተሳታፊዎች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።
በ2016 ዓ.ም ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚገቡ እንዲሁም በማሻሻያ መርሐ ግብር ለተካተቱ ተማሪዎች የሽኝት እና የአደራ መርሐ ግብር ተከናወነ።

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በሰ/ማ/መ የአገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት እና ማኅበረ ቅዱሳን በጋራ በመሆን በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ወደ ክፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ነጥብ ላመጡ እና በማሻሻያ መርሐ ግብር ለተካተቱ ተማሪዎች የሽኝት እና የአደራ መርሐ ግብር አዘጋጅተዋል።

ኅዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ አዳርሽ ውስጥ በተከናወነው መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም በርካታ ተማሪዎች በተሳታፊነት ታድመዋል።

በዕለቱ ንግግር ያደረጉት የአገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው እንደተናገሩት ተማሪዎች ከዓለማዊ ትምህርታቸው ጎን ለጎን መንፈሳዊ ዕውቀትን እና ሕይወት መማር እናደለባቸው አሳስበው በሚሄዱበት ሁሉ መልካም ነገር እንዲገጥማቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
2024/10/01 04:50:10
Back to Top
HTML Embed Code: