Telegram Web Link
በማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ አገልግሎቱን በማጠናከር በግቢ ጉባኤያት ላይ ውጤታማ ሥራ ለመሥራትና ብቁ አገልጋዮችን ለማፍራት ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቶቹን ለማስፈጸም ይረዳውም ዘንድ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ትኬት ሽያጭ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በማሠራጨት ላይ ይገኛል፡፡ እርስዎም ትኬቱን በመግዛት ትውልድን ለመቅረጽ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሻራዎን ያኑሩ፡፡
8
የሰብአዊ ድጋፍ ጥሪ!
+++
ማኅበረ ቅዱሳን በሀገራችን ኢትዮጵያ በማኅበራዊ ቀውሶች ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እያሰባሰበ በማድረስ ላይ ይገኛል።
እርስዎም ድጋፍ በማድረግ ኃላፊነትዎችን እንዲወጡ ተጋብዘዋል።
ድጋፍ ለማድረግም፡-
በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
(Mahiber kidusan social support and rehabilitation accounts )
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400 
መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
15🙏1
በሰሜን ምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ ለተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የደረጃ ሁለት ተተኪ መምህራን ሥልጠና መጠናቀቁን ደብረ ማርቆስ ማእከል አስታወቀ

ሐምሌ ፲፮/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን ደብረ ማርቆስ ማእከል ግቢ ጉባኤ ማስተባበሪያ አዘጋጅነት ከተለያዩ የመንግስትና የግል ዩኒቨርሲቲ ለተዉጣጡ ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለሃያ ስድስት ተከታታይ ቀናት እየተሰጠ የቆየው የደረጃ ሁለት ተተኪ መምህራን ሥልጠና የምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ አባ ኤሊያስ ታደሰ በተገኙበት አስመርቋል።

ተመራቂ ሠልጣኞች ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ከቡሬ ካምፓስ፣ከጤና ካምፓስ እና ከተለያዩ የከተማ ግቢ ጉባኤ የተወጣጡ ቁጥራቸው 36 መሆናቸው ተገልጿል።

ሠልጣኞቹ በቆይታቸው ነገረ ቤተክርስቲያን ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ኦርቶዶክሳዊ የሕይወት ክህሎት፣የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት፣የስብከት ዘዴ፣ሕይወትና ክህሎት፣ ምሥጢራትና ሥርዓት፣ ነገረ-ማርያም እና ሌሎች ሥልጠናዎች እንደተሰጠም ተመላክቷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ቆሞስ አባ ኤሊያስ እንደገለጹት የተካሄደው ሥልጠና እጅግ ጠቃሚ የሆነና ሊበረታታ የሚገባው መሆኑን ጠቅሰው የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው በማለት ሠልጣኞች በተሰጠው ሥልጠና እግዚአብሔርን በመፍራት፣ ሕይወታቸውን በመምራት፣ መክሊታቸውን በማትረፍ በሚሄዱበት ሁሉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን፣ ግቢ ጉባኤዎቻቸውን፣ ወላጆቻቸውንና አገራቸውን እንዲያገለግሉ የአደራ መልእክትና አባታዊ ቡራኬ ሰጥተዋል።
31🙏4
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
4
እንጅባራ ማእከል 19ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን ገለጸ

ሐምሌ ፳፩/፳፻፲፯ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን በእንጅባራ ማእከል 19ኛ ዓመት 19ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ከሐምሌ 18 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ለተከታታይ ሦስት ቀናት ማካሄዱን ገልጿል።

በጉባኤው የኮሶበር መንበረ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አማረ ወንዴ ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ሰሜን ምዕራብ ማእከላት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ተወካዮች ፣ የወረዳ ማእከላት ተወካዮች፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰ/ት/ቤት አንድነት ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የማእከሉ አባላት ተግኝተዋል።

የኮሶበር መንበረ ሥላሴ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አማረ ወንዴ እንደተናሩት ማኀበረ ቅዱሳን የትህትና እና የሥርዓት ባለቤት ነው ስለሆነም ከሰ/ት/ቤቶች ከልዩ ልዩ በጎ ማኅበራት ከገዳማት እና ከጉባኤ ቤቶች እና ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ጋር በመግባባት እና በመደማመጥ ለአንዲት ቅድስት ሐዋርያዊት እና ኩላዊት ቤተክርስቲያን ተግታችሁ እንድታገለግሉ ሲሉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

በተጨማሪም የማእከሉ ነባር አባላት አቶ ተስፋየ ማኅበረ ቅዱሳን እኔን ለአለሁበት ያደረሰኝ መገለጫዬ ነዉ በማለት በማኅበረ ቅዱሳን እንጅባራ ማእከል ስም ለኮሶበር ፈለገ ሕይወት ጉባኤ ቤት በተለያዩ ሊቃዉንት የተፃፉ 27 መፅሐፎችን በስጦታ አበርክተዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን እንጅባራ ማእከል ሰብሳቢ አቶ ይበልጣል አበጀ ለጠቅላላ ጉባኤው መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉ አካላትን ያመሰገኑ ሲሆን ልዪ አስተዋፅኦ ለአደረጉ አካላት የሰርተፍኬት እና ስጦታዎችን አበርክተዋል።ጠቅላላ ጉባኤው በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በመወያየትና ውሳኔዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል።

በተመሳሳይ ደባርቅ ማእከል 2ኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ማካሄዱን አስታውቋል።
2
2025/10/01 10:04:58
Back to Top
HTML Embed Code: