Telegram Web Link
وَاتَّقُوا يَوْمًا تُرْجَعُونَ فِيهِ إِلَى اللَّهِ ۖ ثُمَّ تُوَفَّىٰ كُلُّ نَفْسٍ مَا كَسَبَتْ وَهُمْ لَا يُظْلَمُونَ — المُصْحَف (@AlMosahf) Jan 16, 2025
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِذَا تَدَايَنْتُمْ بِدَيْنٍ إِلَىٰ أَجَلٍ مُسَمًّى فَاكْتُبُوهُ ۚ وَلْيَكْتُبْ بَيْنَكُمْ كَاتِبٌ بِالْعَدْلِ ۚ وَلَا يَأْبَ كَاتِبٌ أَنْ يَكْتُبَ كَمَا عَلَّمَهُ اللَّهُ ۚ — المُصْحَف (@AlMosahf) Jan 16, 2025
فَلْيَكْتُبْ وَلْيُمْلِلِ الَّذِي عَلَيْهِ الْحَقُّ وَلْيَتَّقِ اللَّهَ رَبَّهُ وَلَا يَبْخَسْ مِنْهُ شَيْئًا ۚ — المُصْحَف (@AlMosahf) Jan 16, 2025
وَاسْتَشْهِدُوا شَهِيدَيْنِ مِنْ رِجَالِكُمْ ۖ فَإِنْ لَمْ يَكُونَا رَجُلَيْنِ فَرَجُلٌ وَامْرَأَتَانِ مِمَّنْ تَرْضَوْنَ مِنَ الشُّهَدَاءِ أَنْ تَضِلَّ إِحْدَاهُمَا فَتُذَكِّرَ إِحْدَاهُمَا الْأُخْرَىٰ ۚ — المُصْحَف (@AlMosahf) Jan 16, 2025
وَلَا يَأْبَ الشُّهَدَاءُ إِذَا مَا دُعُوا ۚ وَلَا تَسْأَمُوا أَنْ تَكْتُبُوهُ صَغِيرًا أَوْ كَبِيرًا إِلَىٰ أَجَلِهِ ۚ ذَٰلِكُمْ أَقْسَطُ عِنْدَ اللَّهِ وَأَقْوَمُ لِلشَّهَادَةِ وَأَدْنَىٰ أَلَّا تَرْتَابُوا ۖ — المُصْحَف (@AlMosahf) Jan 16, 2025
It's ጁምዐ
4
Whoever made this meme, should turn themselves in for being this cringe 🤢🤮
😁7👌1
Harun Media - ሀሩን ሚዲያ
Photo
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ የአክሱም ከተማ ተማሪዎች ሒጃብ ለብሰው ወደትምህርት ገበታ እንድመለሱ ጊዜያዊ ውሳኔ ሰጠ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 8/2017

የትግራይ ክልል የትምህርት ቢሮ በአክሱም ከተማ በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የተደረጉ ተማሪዎች ቀድሞ ለብሰው ይማሩበት በነበረው ስርዓት ማለትም ሒጃብ ለብሰው ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ ለአክሱም ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት በፃፈው ደብዳቤ ገልጿል።

በደብዳቤውም "በከተማችሁ ከሴት ሙስሊም ተማሪዎች የአለባበስ ሥርዓት ጋር ተያይዞ የተፈጠረው ችግር በአጠቃላይ የመማር ማስተማር ሂደት ላይ ያሳደረውን እና ለቀጣይ ሊፈጥረው የሚችለው አሉታዊ ተፅእኖ ግምት ውስጥ በማስገባት መንግስት ችግሩን በስምምነት ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ ነው" ብሏል።

ዋናው መፍትሔ በማህበረሰባችን የሚኖር በውይይት የጋራ መፍትሄዎችን መፈለግ ነው። ይህ ደግሞ ተጀምሯል ያለ ሲሆን ይህ እንደዚህ ሆኖ አሁን አጋጥሞ ያለው ችግር እና ለበርካታ ዓመታት ከወረዳና ከትምህርት ቤቶች በመዋቅራችን አደረጃጀትና አሰራር ላይ ሲነሱ የነበሩ ችግሮች በመመርያ እና አሰራር አስደግፎ በዘላቂነት ለመፍታት ትምህርት ቢሮ በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ነው ሲል ገልጿል።

መመሪያው ተጠናቆ ወደ ትምህርት ቤቶች እስከሚወርድ ድረስ ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነው የቆዩ ተማሪዎች ከእገዳው በፊት ይጠቀሙበት የነበረውን አለባበስ ተጠቅመው ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ የተወሰነ መሆኑ እናሳውቃለን ሲሉ በደብዳቤው ላይ ገልጿል።

የአዲሱ መመሪያ ይዘት ሒጃብን በተመለከተ ያካተተውን ጉዳይ ለማወቅ አልተቻለም። የአክሱም ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት ከዚህ በፊት በአክሱም ወረዳ ፍርድ ቤት የተሰጠውን የእግድ ውሳኔ አልቀበልም ማለቱ የሚታወስ ሲሆን አሁን በክልሉ ትምህርት ቢሮ የተፃፈውን ደብዳቤ ስለመቀበሉ የተባለ ነገር የለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በሂጃብ ምክንያት ከትምህርታቸው የተገፉ ተማሪዎችን አስመልክቶ በመጪው ማክሰኞ በመላው ትግራይ ሰላማዊ ሰልፍ ያካሂዳል።

© ሀሩን ሚዲያ
1
የአክሱም ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የክልሉ ትምህርት ቢሮ የሰጠውን ውሳኔ አልቀበልም በማለት በድጋሜ ሒጃብ የለበሱ ተማሪዎችን እንዳይገቡ ከለከለ!

- ሀሩን ሚዲያ፣ ጥር 9/2017

በትግራይ ክልል የአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች በሒጃብ ምክንያት የሚደርስባቸው ወከባ አሁንም ድረስ እልባት አላገኘም።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ትላንት ሐሙስ ጥር 8/2017 ዓ.ል ለአክሱም ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት የተማሪዎችን አለባበስ በተመለከተ በጻፈው ደብዳቤ ከትምህርት ገበታ ውጪ የተደረጉ ተማሪዎች ቀድሞ የነበረውን አለባበስ ተጠቅመው ትምህርት እንዲቀጥሉ ውሳኔ አሳልፎ እንደነበር ይታወቃል።

ይሁንና ምንም ዐይነት ውሳኔ አልደረሰንም ያሉ የትምህርት ቤት አስተዳዳሪዎች ዛሬ ጁመዐ ጥር 9/2017 ሒጃብ የለበሱ ሙስሊም ተማሪዎችን እንዲመለሱ ማድረጋቸውን ተማሪዎቹ ለሀሩን ሚዲያ በላኩት መረጃ ገልፀዋል።

በአክሱም ከተማ በሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ እየደረሰ የሚገኘው መንገላታት ከእለት ወደ ዕለት እየከፋ መሄዱ የተገለፀ ሲሆን እስካሁን ለጉዳዩ እልባት የሚሰጥ አካል አለመኖሩ ተገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተገናኘ የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በሂጃብ ምክንያት ከትምህርታቸው የተገፉ ተማሪዎችን አስመልክቶ በመጪው ማክሰኞ በመላው ትግራይ ሰላማዊ ሰልፍ ያካሂዳል።

© ሀሩን ሚዲያ
😡6👍2😱1
عن سمرة ، قال النبي صلى الله عليه وسلم : " رأيت الليلة رجلين أتياني فصعدا بي الشجرة، فأدخلاني دارا هي أحسن وأفضل، لم أر قط أحسن منها، قالا : أما هذه الدار فدار الشهداء ".صحيح البخاري ٢٧٩١ — صحيح الأحاديث (@Hadeeth_SA) Jan 19, 2025
1
🤣6👀2
2025/07/08 18:09:19
Back to Top
HTML Embed Code: