Telegram Web Link
ትራምፕ እንዲህ አሉ " ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከጦርነቱ ጠብቀን"

" ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከጦርነቱ ጠብቀን። ከዲያብሎስ ክፋትና ወጥመዶች ከልለን። በትህትና እንጸልያለን እግዚአብሔር ይገስጸው፣ አንተ የሰማይ ሠራዊት አለቃ ሆይ፣ በእግዚአብሔር ኃይል፣ የነፍስን ጥፋት እየፈለጉ በዓለም ላይ የሚንከራተቱትን ርኩሳን መናፍስትን ሁሉ ወደ ሲኦል ጣላቸው"

ይህ የቀድሞው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትዊተር ገፃቸው ያሰራጩት መልዕክት ነው።

@sheger_press
@sheger_press
ንግድ ባንክ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ ተግባራዊ አደረገ!

ግዙፉ መንግስታዊ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርግ አስታዉቋል ።

ባንኩ ከመስከረም 21፤2017 ዓ.ም. ጀምሮ ምርትና የአገልግሎት ዓይነቶች ላይ በሚከፈል የአገልግሎት ክፍያ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ የተጨመረባቸው መሆኑን እንሳዉቃለን ቢልም በምን ያህል መጠን እንደሆነ ግን አልገለፀም።

የገንዘብ ሚኒስትር አዋጁ ተግባራዊ እንዲደረግ ለመንግሥት ፋይናንስ ተቋማት በሐምሌ 1 ቀን 2016 ዓ.ም. በፃፈው ደብደቤ ላይ እንደገለፀው ከሰኔ 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ በተደረገው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ላይ ሙሉ በሙሉ በፌዴራል መንግስቱ በጀት የሚተዳደር የመንግስት መስሪያቤቶችን እንደሚያካትት ገልፆ ነበር ።

ይህን ተከትሎ መንግስት በቅርቡ ባወጣው አዲስ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሕግ ቁጥር 1341/2016 መስረት ባንኮች በሚሰጧቸው አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲጣል በመታወጁ ንግድ ከዛሬ ጀምሮ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ የተጨመረባቸው መሆኑን ነዉ ያስታወቀው።

ከአዲሱ የዉጪ ምንዛሪ ለዉጥ ጋር ተያይዞ መንግስት ከያዛቸው ስር ነቀል ለዉጦች መካከል የታክስ ዘርፉ አንደኛው መሆኑ ይታዉቃል። በዚህ በበጀት ዓመት በታክስ 1.15 ትሪሊየን ብር ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን ይህ ደግሞ የበጀት ዓመቱ ሲጀመር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከነበረው 502 ቢሊየን ብር አንፃር ከእጥፍ በላይ የጨመረ እንዲሆን አድርጓታል ።

በዚህም በቅርቡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ጨምሮ ኢትዮቴሌኮም እንዲሁም ሌሎች የመንግስታዊ ተቋማት በሚሰጧቸው አገልግሎት ላይ የታሪፍ ማሻሻያ እያደረጉ እንደሚገኙ ይታወቃል ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Breaking

አሁን ማምሻውን ኢራን እስራኤል ላይ የባለስቲክ ሚሳኤል ጥቃቶችን አድርሳለች::

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
#ሰበር

እስራኤል ከኢራን ሚሳኤሎች መወንጨፏቸውን አስታወቀች

የእስራኤል ጦር በመላ ሀገሪቱ የሚሳኤል ሳይረን እየተሰማ መሆኑን ያሳወቀ ሲሆን ከኢራን ሚሳኤል ተወንጭፋል ብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
የእስራኤል መከላከያ ኃይል ጥቃቱ መጀመሩን ተከትሎ ለዜጎቹ ባስተላለፈው መልዕክት “የሚወጡ መመሪያዎችን በንቃት እንዲከታተሉ” አሳስቧል።

የኢራን የሚሳዔል ጥቃት መጀመሩ ተከትሎ የእስራኤል ጦር የአገር ውስጥ ዕዝ በአንዳንድ አካባቢዎች ለሚኖሩ ዜጎች ወደ መከላከያ ስፍራዎች እንዲገቡ የሚያዝ “ነፍስ አድን” ያለውን መመሪያ በአጭር የጽሁፍ መልዕክት አስተላልፏል።

የጦሩ ቃል አቀባይ ዳንኤል ሃጋሪ ደግሞ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ነዋሪዎች በአቅራቢያቸው ወደሚገኙ ከጥቃት የመሸሸጊያ ስፍራዎች በመግባት ተጨማሪ መመሪያዎችን እንዲጠባበቁ መክረዋል።

ቃል አቀባዩ ጨምረውም የእስራኤል የአየር ጥቃት መከላከያ ሥርዓት “ሙሉ ለሙሉ በስራ ላይ ሆኖ የሚተኮሱ ሚሳዔሎችን በመለየት እያከሸፈ” መሆኑን ተናግረዋል።

@sheger_press
@sheger_press
ባይደን እስራኤል ራሷን ከኢራን ጥቃት ለመከላከል አሜሪካ ለመርዳት ዝግጁ መሆኗን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እስራኤል ራሷን ከኢራን የሚሳኤል ጥቃት ለመከላከል እና በአካባቢው የሚገኘውን የአሜሪካን ጦር እገዛ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

ዩናይትድ ስቴትስ እስራኤልን ከእነዚህ ጥቃቶች ለመከላከል እና በአካባቢው የሚገኙ የአሜሪካን ሰራተኞችን ለመጠበቅ እንዴት እንደተዘጋጀች ከምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ እና ከዋይት ሀውስ ብሔራዊ ደህንነት ቡድን ጋር ተወየይተናል ሲሉ በኤክስ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።

@sheger_press
@sheger_press
ኢራን በእስራኤል ላይ ከ 240 በላይ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን መተኮሷ ተዘገበ

ምሽቱን ኢራን በእስራኤል ላይ ከፍተኛ የሚሳኤል ድብደባን ፈጽማለች። ኢራን ከ 240 እስከ 250 የባለስቲክ ሚሳኤሎችን ተኩሳለች የተባለ ሲሆን ብዙዎቹ ቢከሽፉም በእስራኤል ምድር ላይ የወደቁ ሚሳኤሎች መኖራቸዉን ግን ዳጉ ጆርናል ከስፍራው የቀጥታ ስርጭት ዘገባ ከሚሰሩ የዜና አዉታሮች ታዝቧል።

አሁ ላይም ኢራን ሌላ ዙር ጥቃት በእስራኤል ላይ ካልፈጸመች የአየር ጥቃቱ ቆሟል የተባለ ሲሆን በጥቃቱ የደረሰዉ ጉዳት ግን እስካሁን አልታወቀም። ኢራን ጥቃቱን በእስራል ላይ ያደረገችዉ በሁለት አቅጣጫዎች ነዉ ተብሏል።

ቴልአቪቭ ፤ ለቴርሃን ጥቃት ምን አይነት ምላሽ ትሰጣለች የሚለዉ አሳሳቢዉ ጉዳይ ሲሆን ጦርነቱን ሀያላኑ ሀገራት እንዳይቀላቀሉት አስግቷል። የእስራኤል መከላከያ ሀይል በበኩሉ ከ 180 በላይ ሚሳኤሎች መተኮሳቸዉን እንዳረጋገጠ ኤቢሲ ኒዉስ ዘግቧል።

እስራኤል የኢራን የአየር ጥቃት መቆሙን ተከትሎ ዜጎች ከሚሳኤል መሸሸጊያዎች እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፋለችም ተብሏል። እስራኤል ሶስት የአየር ጥቃት መከላከያ ያላት ሲሆን ሶስቱን የጸረ ሚሳኤል መከላከያን የጣሱ የኢራን ሚሳኤሎች ግን በእስራል ላይ ቀላል የማይባል ጉዳት እንደሚያደርሱ ዳጉ ጆርናል ታዝቧል።

@sheger_press
@sheger_press
በእስራኤል ዋና ከተማ ቴላቪቭ በተከፈተ የጅምላ ተኩስ ስድስት ሰዎች ተገደሉ

ኢራን በእስራኤል ላይ ከፈፀመችው የሚሳኤል ጥቃት በተለየ ሁኔታ፣ በቴል አቪቭ የጅምላ ተኩስ ተከስቷል።

ዛሬ ማምሻውን ታጣቂዎች በከተማው ጎዳና ላይ በሰዎች ላይ ተኩስ ከፍተዋል ሲል ፖሊስ የገለፀ ሲሆን የእስራኤል መገናኛ ብዙሃን ቢይንስ ስድስት ሰዎች መሞታቸውን ዘግበዋል። ቢያንስ ሰባት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸው የተዘገበ ሲሆን አንዳዳዶቹ በአስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ መባሉን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።

በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ የተለጠፉት ምስሎች እንዳሳዩት ታጣቂው በጃፋ አካባቢ በሚገኝ የባቡር ጣቢያ ላይ መሬት ላይ ተኝተው በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ ሲተኩስ ታይቷል። ፖሊስ የጥቃቱን ምክንያት “ሽብር” ሲል ገልጾታል።
መስማት የተሳናትን የ ስምንት አመት ልጅ እና የአእምሮ ውስንነት ያለባትን የ አስራ ስድስት አመት ልጅ ላይ የአገድዶ መድፈር ጥቃት የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ዳዋ ወረዳ ውስጥ መስማት የተሳናትን የስምንት አመት ልጅ እና በጎሮ ወረዳ የአስራ ስድስት አመቷን የአእምሮ ውስንነት ያለባትን ልጅ አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ ላይ የእስራት ቅጣት መተላለፉን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ አስታወቀ።

እንደ ደቡቡ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ ገለፃ ተከሳሽ ፈይሳ ከበደ የተባለው ግለሰብ ሰኔ 1ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰአት ላይ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ዳዋ ወረዳ ቡሳ 01 ቀበሌ የስምንት አመቷን መስማት የተሳናትን ልጅ አባብሎ በመውሰድ የመድፈር ጥቃት እንደፈፀመባት ተገልጿል። ተከሳሹ መስማት የተሳናት የስምንት አመት ልጅ ላይ የመድፈር ጥቃት ከፈፀመ በኋላ የስምንት አመቷ መስማት የተሳናት ልጅ የተፈፀመባት ድርጊት መቋቋም አቅቷት ስትጮህ የአካባቢው ሰዎች ደርሰው ድርጊቱን ለማስጣል ሲሞክሩ የመድፈር ጥቃት ፈፃሚው ሮጦ ለማምለጥ ቢሞክርም በህብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

ፖሊስም በህብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር የዋለውን ተከሳሽ ላይ የምርመራ መዝገቡን በማጣራት ተጎጂዋን የስምንት አመት ልጅ ወደ ጤና ጣቢያ በመላክ በማስመርመር የህክምና እርዳታ እንድታገኝ አድርጓል። በህክምና ማስረጃ መሰረት በታዳጊዋ ላይ የመደፈር ጥቃት ሙከራ መከናወኑን የሚገልፅ በመሆኑ እና በአይን እማኝ ምስክርነት የምርመራ መዝገቡን በማጣራት ለአቃቤ ህግ መላኩን ገልፀዋል።አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከለትን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀል ህግ 627 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት ለአቅመ ሄዋን ባልደረሱ እንስቶች ላይ የሚፈፀም የመድፈር ጥቃትን በመጥቀስ ክስ መስርቷል። በአቃቤ ህግ የተመሰረተውን ክስ ሲመለከት የነበረው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽን በ6 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።

በተመሳሳይ በደቡብ ምዕራብ  ሸዋ ዞን ጋልዮ ሞጆ ቀበሌ ውስጥ በአስራ ስድስት አመቷ የአይምሮ ውስንነት ባለባት ልጅ ላይ የመድፈር ጥቃት በመፈፀም ክብረ ንፅህናዋን የወሰደው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገልፆል።ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰአት ላይ ተከሳሽ ጌታቸው ታደሰ የተባለው ግለሰብ የ አስራ ስድስት ዓመቷን የአይምሮ ውስንነት ያለባትን ልጅ በጉልበት እጇን በመጠምዘዝ ወደ ሰዋራ ስፍራ ወስዶ የመድፈር ጥቃት እንንዳደረሰባት በማስረጃ መረጋገጡን ገልፆል። ተጎጂዋ የደረሰባትን ጥቃት መቋቋም አቅቷት ስትጮህ የሰሙ የአካባቢው ሰዎች ደርሰው ተከሳሹን ወዲያውኑ እጅ ከፍንጅ በመያዝ ለፖሊስ ማስረከባቸውን ተገልጿል። ፖሊስም የድርጊቱ ፈፃሚ በመያዝ ጥቃት የደረሰባት ታዳጊ የአይምሮ ውስንነት ያለባት ልጅ የክብረ ንፅህናዋ እንደተወሰደ በማረጋገጥ ማስረጃውን ለአቃቤ ህግ መላኩን የፖሊስ መምሪያው ገልፆል። 

አቃቤ ህግ ከፖሊስ የተላከለትን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀል ህግ 620 ንሁስ አንቀፅ 2 ቸአይምሮ ውስንነት ባለባቸው ሰዎች ላይ በሚፈፀም የመድፈር ጥቃት መሠረት በማድረግ ክስ ይመሰርታል። በአቃቤ ህግ የተመሠረተውን ክስ ሲከታተል የነበረው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድቤት ተከሳሽ ጌታቸው ታደሰ በአቃቤ ህግ የቀረበበት ክስ ሙሉ በሙሉ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ ዘጠኝ አመት እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲል የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ ገልፆል።
በእነ ዶክተር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ የተሰጠው እግድ እንዲጸና ትዕዛዝ ተሰጠ

👉የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በመስከረም 08 ቀን 2017 ዓ.ም የተሰጠው እግድ ሊነሳ #አይገባም በማለት የእነ ዶር #አሸብር ወልደ ጊዮርጊስን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ እግዱ እንዲፀና ትእዛዝ ሰጠ

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሙሉ ትዕዛዝ ከላይ ተያይዟል።

@sheger_press
@sheger_press
ኢራን በእስራኤል ላይ የሚሳኤል ጥቃት መፈፀሟን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ ጨመረ

ኢራን በእስራኤል ላይ የባልስቲክ ሚሳኤሎችን ከተተኮሰች በኋላ የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል ፣ይህም በመካከለኛው ምስራቅ የነዳጅ አቅርቦትን ሊያስተጓጉል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል ።

ብሬንት ክሩድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለነዳጅ ዘይት ዋጋ ቁልፍ መለኪያ ሲሆን አንድ ያልተጣራ ድፍድፍ ነዳጅ በበርሚል ከ1 በመቶ በላይ ጨምሮ ወደ 74.40 ዶላር ከፍ ብሏል። ማክሰኞ በግብይት ወቅት ከ 5 በመቶ በላይ ጨምሯል። እንደ ዩናይትድ ስቴትስ ኢነርጂ አስተዳደር መረጃ ኢራን ከአለም ሰባተኛዋ የነዳጅ አምራች ሀገር ስትሆን በኦፔክ የነዳጅ ዘይት አምራቾች ውስጥ ደግሞ ሶስተኛዋ ትልቋ አባል ነች።

ነጋዴዎችም በክልሉ ውስጥ የሚፈጠር ማንኛውም ወታደራዊ ሃይል በሆርሙዝ ወሽመጥ የባህር ዳርቻ የመርከብ ጉዞ ላይ ተጽእኖ ሊያሳድር ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። በኦማን እና በኢራን መካከል ያለው የመርከብ ማጓጓዣ መንገድ  20 በመቶ የሚሆነው የዓለም አቅርቦቶች የሚጓጓዙበት አለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ቁልፍ መስመር ነው።

ሌሎች የኦፔክ አባላት ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ፣ ኩዌት እና ኢራቅ ወደ ውጭ የሚላኩትን ዘይት በብዛት በባህር ሰርጡ በኩል ይልካሉ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
"ምናለ ጎበዝ ተማሪ ባልነበርኩ” እላለሁ

“ከሰው አልጨመርም። አብዝቼ እተክዛለሁ። ፊደል ያልቆጠረ ብዙ የማውቀው ሰው ቤት ንብረት አለው። የተሻለ ሕይወት ይመራል። እኔ ለምን ተማርኩ እላለሁ - አንዳንዴ። እንደሱ አይባልም - አውቃለሁ። ግን ምን ላድርግ? ወደ አእምሮዬ የሚመጣውን ነው የምነግርህ።

ውስጤ ጠንካራ ሆኖ ነው ከራሴ ያለሁት እንጂ ጭንቅላቴ እኮ ልክ አይደለም።

እንደ ባይተዋር ነው የምኖረው።

አንዳንዴ ለብቻዬ እያወራሁ ራሴን አገኘዋለሁ።

ጓደኛ የለኝ፣ ምን የለኝ። ሰው ሆነህ ከሰው ጋ መጨመር ካልቻልክ ማበድ ማለት አይደለም?

ከወር-ወር ኪሴ ባዶ ነው።ከቤት የማልወጣውም ለዚያ ነው። ታክሲ ውስጥ ሰው ባገኝስ ብዬ እሳቀቃለሁ። ከዚህ ሁሉ ለምን ቤት አልቀመጥም ብዬ ነው ያለሁ።

በቀደም ትዝ ሲለኝ ለባለቤቴ የተጋባን ቀን ከገዛሁላት ስጦታ ውጭ ገዝቼላት አላውቅም።

ባትነግረኝም ሞራሏ መጎዳቱ አይቀርም። ለልጄም እንደዚያው። ከዚህ በላይ ምን የሚያሳዝን ነገር አለ?

እኔ መምህር በመሆኔ እና እነሱ የመምህር ቤተሰብ በመሆናቸወ ተጎድተዋል። ምንም ጥያቄ የለውም። አንዳንዴ ‘ምናለ ድሮ ጎበዝ ተማሪ ባልነበርኩ’ የምለውም ለዚያ ነው።

ዘገባው የBBC አማርኛ ነው

@sheger_press
@sheger_press
ሰበር : መንገድ ተዘጋ ከባዱ ውጊያ ተጀምሯል | ዘመነ ካሴ ከባዱን ትእዛዝ ሰጠ | የብልፅግና ሰራዊት ተደመ-ሰሰ የመጨረሻው ጦርነት ተጀመረ ሙሉ ዜናውን አሁኑኑ ከስር ባለው ሊንክ አድምጡ! 👇👇👇
https://youtu.be/bdq-QobRnvU?si=unkgwFq8dtjw_mkE
ኢትዮጵያ የጭነት አስተላላፊዎች ማህበራት ዓለም አቀፍ ፌዴሬሽን (FIATA) የ2027 ዓለም አቀፍ ጉባኤን ለማስተናገድ ተመረጠች

ሀገሪቱ ይህን አለም አቀፍ ጉባኤ ለማካሄድ መመረጧ በአፍሪካ አህጉር በሎጂስቲክስ ዘርፍ እየጎለበተ የመጣውን ሚናዋን በጉልህ የሚያመላክት ነው ተብሏል።

የኢትዮጵያ የጭነት አስተላላፊና የመርከብ አገልግሎት ወኪሎች ማህበር ይህን ጉባኤ በሀገሪቱ እንዲያሰናዳ መታጨቱ ለኢትዮጵያ ብሎም ለመላ አህጉሪቱ ጠቀሜታው የግላ መሆኑም ተነግሯል።

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው ጉባኤ ላይ ከ800 በላይ የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች፣ የዘርፉ ታላላቅ አመራሮችና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉበት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ኢትዮቴሌኮም በሲም ካርድ ዋጋ ላይ  ጭማሪ አደረገ‼️

ኢትዮቴሌኮም ከዚህ ቀደም የጠፋ ሲም ካርድን ለማዉጣት 15 ብር የሚጠይቅ ቢሆንም አሁን ግን  በአዲሱ ማሻሻያ 85 ብር እንዲሆን አድርጓል።

በተመሳሳይ አዲስ ሲም ካርድ ለማዉጣት ይጠየቅ የነበረዉ 30 ብር አሁን ግን 85 ብር መሆኑ ተሰምቷል።

ተቋሙ ከሚሰጣቸው አገልግሎት ዝቅተኛ ዋጋ የሚጠይቁት ማለትም በ 3 እና በ 5 ብር የሚገዙ ፓኬጆች ላይ ምንም አይነት ዋጋ ጭማሪ አለመደረጉ ተገልጿል።

@sheger_press
@sheger_press
"ምዕመናን ገንዘባቸውን የሚሰጡት ለሃይማኖት ማስፋፊያ እንጂ ለዘረፋ አይደለም።" ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ

ቅዱስ ፓትርያርኩ ለአጣሪ ኮሚቴው የሥራ መመሪያ ሰጡ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚስተዋለውን የሙስናና ብልሹ አሰራር በዝርዝር በማጥናት የመፍትሔ ሐሳብ እንዲያቀርብ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤት የተቋቋመው አጥኚ ኮሚቴ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትና ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጋር ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን የሠራቸውን ሥራዎች ሪፓርት በማቅረብ በቀጣይ በሚያከናውናቸው ተግባራት ዙሪያ በመወያየት የሥራ መመሪያ ተቀብሏል።

ኮሚቴው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚስተዋለው የመልካም አስተዳደር ችግር ከውስጥ አልፎ በአደባባይ መነጋገርያ በመሆኑ በጥናት ላይ በተመሠረተ አግባብ ተቋማዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችልና የቤተ ክርስቲያናችንን ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲደራጅ የሚያደርግ የመፍትሔ ሐሳብ ለማቅረብ የሚያስችለውን ዕቅድ በማውጣት ወደ ተግባር መግባቱን የኮሚቴው ሰብሳቢ መ/ሰ ቆሞስ አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ (ዶር) እና ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው ባቀረቡት ሪፖርት ገልጸዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርኩ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሰጡት አባታዊ የሥራ መመሪያ "ምዕመናን ገንዘባቸውን የሚሰጡት ለሃይማኖት ማስፋፊያ እንጂ ለዘረፋ አይደለም” ያሉ ሲሆን ስለሆነም ሕግና ሥርዓትን አክብራችሁ፣ በእውነተኝነት ለቤተክርስቲያን፣ለእግዚአብሔርና ለራሳችሁ ብላችሁ ሳታፍሩና ሳትፈሩ ሥራችሁን ሥሩ። ሥራው ታማኝነት"ጥብዓት" ያስፈልጋል ብለዋል።

ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ጋር ሆናችሁ በጋራ ሥሩ ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ ጠንከር ያለ መድኅኒት ሊሆን የሚችል ጥናት ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር እንደምታቀርቡ እምነቴ የጸና ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም የተላካችሁበት ሥራ ያለ ውጤት የሚቀር መሆን የለበትም።

ቤተክርስቲያን የተዋረደችበት ጊዜ ማብቃት አለበት ያሉት ቅዱስነታቸው ቤተክርስቲያናችን ራሷን አንጽታ ለሌሎች መልካም አብነት መሆን አለባት ካሉ በኋላ ዓለማዊያን የሚሰሩት ሥህተት እንዳይኖር በተግባር የምታስተምር ተቋም እንጂ በሙስና የምትታማ መሆን የለበትም ብለዋል ሲል የቤተክርስቲያኗ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አስታውቋል፡፡

ልጆቼ እውነቱን ለማውጣት ታጥቃችሁ ሥሩ በሙስና ህመም ለምትሰቃየው ቤተክርስቲያን መድኃኒት ፈልጉላት በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን የቀጠሉት ቅዱስነታቸው አንመረመርም ማለት ራሱን ችሎ ወንጀል ነው ካሉ በኋላ ይህ ሥራ ለእናንተም ታሪክ ነው።

እውነትን መሰረት አድርጋችሁ በመሥራት ታሪክ አስመዝግቡ ብለዋል። በመልዕክታቸው ማጠቃለያ ላይም ወደ እዚህ ተቋም የሚገቡ ሁሉ ይህን ያህል ጊዜ ቆይተን ይህን ያህል ይዘን እንውጣ የሚሉ እንጂ ለቤተክርስቲያን የሚቆረቆሩና የሚያስቡ እንዳልሆኑ ይታወቃል ካሉ በኋላ የተሰጣችሁን ኋላፊነት በትጋት ፈጽሙ ብለዋል።

@sheger_press
@sheger_press
አሳዛኝ ዜና‼️

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ጉባላፍቶ ወረዳ 015 ቀበሌ ደቦት ልዩ ቦታው እቧዮች ኪዳነምህረት መስከረም 22/2017 ዓ/ም ምሽት ላይ ከባህር ዳር ወደ ወልድያ መስመር ወደ መቅደላ ዩኒቨርስቲ የሚሄዱ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ጭኖ  ሲጓዝ የነበረ አባዱላ መኪና ተገልብጦ ከጫነው 21 ሰው 7 የሞተ ሲሆን 14 ተማሪዎች ቆስለው ወደ ጤና ጣቢያና ሆስፒታል ተወስደው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/10/03 19:29:06
Back to Top
HTML Embed Code: