Telegram Web Link
ሸኽ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን ለ400 ሠራተኞቹ ከ100 ሺ ብር እስከ 500 ሺ ብር ሰጥተዋል!

ሸኽ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሰራተኞች እና አመራሮች ላከናወኑት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ አመራሮችና ሰራተኞቹ እውቅና ሰጥቷል።

በዚሁ ወቅት ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በዙም ባስተላለፉት መልዕክት፤ የተቋሙ ሰራተኞች እና አመራሮች ላከናወኑት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል። ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡም ገልፀዋል።

በመድረኩ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2016 በጀት ዓመት የዕቅዱን 90 በመቶ ማሳካቱ ተጠቅሷል፡፡ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 400 ሠራተኞቹ ለእያንዳንዳቸው ከ100 ሺ ብር እስከ 500 ሺ ብር ስጦታ ተበርክቷል።

@sheger_press
@sheger_press
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 499ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ነገ ጀምሮ በቱርክ አንካራ ከተማ በሶማሊያ መንግስት እና ኢትዮጵያ ሊያደርጉት የነበረው ውይይት ሊራዘም እንደሚችል መረጃዎች እየወጡ ነው::

ይህ ስብሰባ ለሌላ ጊዜ የተራዘመበት ምክንያት ሁለቱም ወገኖች በአቋማቸው ላይ እስካሁን ምንም አይነት ለውጥ ባለማሳየታቸው ነው ተብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በካዛንችስ እና አዋሬ ፥ ከህንፃዎች እና አንዳንድ በደንብ ከተያዙ መኖርያ ቤቶች በቀር ሁሉም ፈራሽ ናቸው መባሉ ተሰማ

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር አመራሮች ባሳለፍነው ሳምንት ካዛንችስ ተገኝተው ነዋሪዎችን ባነጋገሩበት ወቅት ካዛንችስ እና አዋሬ ውስጥ ከህንፃዎች እና አንዳንድ በደንብ ከተያዙ መኖርያ ቤቶች በቀር ሁሉም ፈራሽ መሆናቸው እንደተነገራቸው ዳጉ ጆርናል ከመሠረት ሚዲያ ሰምቷል። ይህን የሚያስረዳ የድምፅ ሪከርድ ደርሶኛል ሲልም የዜና ምንጩ ዘግቧል።

ከበርካታ ነዋሪዎች የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው በቅርብ ቀናት ካዛንችስ ከስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ ጀርባ ያለው አካባቢ ሙሉ በሙሉ ሊፈርስ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

"መቼ እንደሚፈርስ ግን ትክክለኛው ግዜ አልተነገረንም" ያሉት ነዋሪዎቹ ይህም "እንቅልፍ ነስቶናል፣ ከዛሬ ነገ መጥተው ውጡ ሊሉን ይችላል" ብለው ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ተናግረዋል።

Via መሠረት ሚዲያ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዶናልድ ትራምፕ በነበሩበት አካባቢ የተኩስ እሩምታ እንደተሰማ ተገለፀ

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፍሎሪዳ በሚገኘው የትራምፕ አለም አቀፍ የጎልፍ ክለብ ውስጥ ጎልፍ እየተጫወቱ በነበረበት ወቅት በአካባቢው ድንገተኛ የተኩስ እሩምታ እንደተሰማ ተገልጿል፡፡

የዶናልድ ትራምፕ የምርጫ ዘመቻ ግንኙነት ኃላፊ ስቴቨን ቼዌነግ፤ ትራምፕ በቅርበት በነበሩበት አካባቢ የተኩስ ድምፅ እንደተሰማ አረጋግጠዋል፡፡

ከክስተቱ በኋላ ዶናልድ ትራምፕ ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የገለፁት ኃላፊው፤ አሁን በጉዳዩ ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ማቅረብ እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካ የሚስጥራዊ ደህንነት ተቋም (ሰክሬት ሰርቪስ) ጉዳዩን ከምዕራብ ፓልም ቢች ከተማ ፖሊስ ጋር በመሆን እየመረመረ መሆኑን ገልፆ፤ አሁን ላይ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ደህና መሆናቸውን ማስታወቁን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡

ከሁለት ወራት ገደማ በፊት በዶናልድ ትራምፕ ላይ የግድያ ሙከራ ከተደረገ በኋላ ለሊት ያጋጠመው ክስተት በትራምፕ ላይ ያነጣጠረ ይሁን አይሁን እስካሁን ግልጽ አለመሆኑም ነው የተገለፀው፡፡

ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ ህዳር ወር ለሚደረገው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በፔንሲልቬንያ የምረጡኝ ቅስቀሳ እያደረጉ በነበሩበት ወቅት የግድያ ሙከራ እንደተሰነዘረባቸው የሚታወስ ነው፡፡

የBernstein ተንታኞች ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ የ bitcoin ዋጋ በአመቱ መጨረሻ ላይ 90,000 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተንብየዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
“በጦርነቱ ከአንድ ሚልዮን በላይ ትግራዋይ አለቀ  ተብሎ የሚወራው ማስረጃም ሆነ ጥናት የለውም።ለፖለቲካ ፉጆታ የተፈበረከ ነው።
ከተኩስ ማቆም ውጭ ያለውን የፕሪቶሪያ ስምምነት አንቀበለውም ብሏል። ትጥቅ መፍታትም ሆነ ሌላው በስምምነቱ ላይ መቀመጡንና መፈረማቸውን ቢያምንም  ከተኩስ ማቆም ውጭ ያለውን "እንታገለዋለን" ብሏል። " መጀመሪያ ስንሰማ ሁሉንም ያስደነገጠ ነው" ብሏል።
- ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለሆራይዘን ሚዲያ ከተናገሩት የተወሰደ

@sheger_press
@sheger_press
የኢትዮጵያ አየር መንገድን በፑንትላንድ እንዳያርፍ ተከለከለ‼️
👉ይህ ክልከላ ሌሎች አውሮፕላንችንም ያካትታል።
ይህንን ክልከላ የጣለው የሱማሊያ ፌዴራል መንግስት ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ በመንግስትና በፑንትላንድ አስተዳደር መካከል በተፈጠረው ውዝግብ የተነሳ ነው፡፡ ውዝግቡን ተከትሎ የሱማሊያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን ከዛሬ ጀምሮ በፑንትላንድ የሚገኘው የቦሳሶ አየር ማረፊያ ዝግ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የፑንትላንድ የፀጥታ አካላት የቦሳሶ አየር ማረፊያ አስተዳደርና ደህንነት ከቁጥጥራቸው ውጭ መሆኑን በመግለፅ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በዚያ ለሚጠቀሙ አውሮፕላኖች ማስጠንቀቂያ ሰጥተው እንደነበር ተዘግቧል፡፡ ይሁንና ይህንን ማስጠንቀቂያ ቸል በማለት በረራቸውን የቀጠሉት የኢትዮጵያ አየር መንገድና የዳሎ አየር መንገድ ብቻ የነበሩ ሲሆን ዛሬ እነዚህም ቦሳሶ እንዳያርፉ ከሱማሊያ ሲቪል አቪየሽን እገዳ ተጥሎባቸዋል፡፡

ይህ የዛሬው እገዳ በሱማሊያና በፑንትላንድ መካከል ያለውን የፖለቲካ ሽኩቻ አንድ ደረጃ ከፍ ያደረገ መሆኑን የፖለቲካ ታዛቢዎች ተናግረዋል፡፡ የአየር ማረፊያው በመዘጋቱ በርካታ መንገደኞች ለእንግልት የተዳረጉ ሲሆን ሲቪል አቪየሽኑ ሌላ ማስታወቂያ እስከሚያወጣ ድረስ ዝግ ሆኖ እንደሚቆይ አስታውቋል፡፡

@sheger_press
@sheger_press
በአዲሱ ዓመት በአዲስ ክህሎቶች ራሳችሁን ብቁ አድርጉ። በሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ ላይ የ 20% ቅናሽ ለወንዶች : 5,706 ብር የነበረው አሁን በ 1,141 ብር ብቻ ያግኙ።

- 6000+ tech and non tech ኮርሶች
- በ ቀጣሪዎች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ሰርተፍኬቶች
- በተለያዩ ፕሮጀክቶቻችሁ ላይ ከአቻ ባልደረቦቻችሁ ጋር አብራችሁ የምትሰሩበት እድል
- ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚመሩ የስልጠና ቡድኖችን
- በየወሩ ነጻ የ6 GB የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ

በዚህ አዲስ ዓመት ግቦችን ብቻ አታስቀምጡ፣ ግቦቹን አሳኩት። አሁኑኑ ይመዝገቡ : https://bit.ly/4cQrem2

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ: https://www.tg-me.com/+3nNaOCMHiXgyMTA0
Forwarded from Sheger Press️️
Make the most of the New Year with New Skills. Invest in your future with Safaricom Talent Cloud’s exclusive 80% scholarship for women, originally 5,706 birr, now just 1,141 birr.

Build your future with:
- 6,000+ tech and non tech courses
- Certifications recognized by top employers
- A supportive learning community
- Expert coaching at every step
- 6 GB free internet monthly

Don’t just set goals this New Year, achieve them. Register now at https://bit.ly/4cQrem2 and make 2017 your year of success!

For more information, join our Telegram channel: https://www.tg-me.com/+3nNaOCMHiXgyMTA0
በ2017 ዓ/ም መማር ለምትፈልጉ አመልካቾች በሙሉ

በአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል በመጀመሪያ ዲግሪ በ2017 ዓ/ም መማር ለምትፈልጉ አመልካቾች በሙሉ፤

በ2017 ዓ/ም በቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ ግብር በትምህርት ሚኒስቴር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምደባ እንደማይኖር ይታወቃል።

በመንግስት ስኮላርሺፕ እንዲሁም በግል ከፍላችሁ በዩኒቨርሲቲያችን መማር ለምትፈልጉ በሙሉ የአ.አ.ዩ የሚያወጣውን የመግቢያ ፈተና (UAT) እንዲሁም ሌሎች መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባችኋል፡፡

በዚህም መሠረት በዩኒቨርሲቲያችን ድረ ገጾች
(www.aau.edu.et ወይም https://portal.aau.edu.et) ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር የማመልከቻ መስፈርቶች በማሟላት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

• የመመዝገቢያ ቀናት እስከ መስከረም 8/ 2017 ዓ.ም ድረስ ይሆናል

• የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀናት ወደፊት በ ዩኒቨርሲቲያችን ዌብ ሳይት፤ የምዝገባ ፖርታል እንዲሁም በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ የሚገለጽ ይሆናል::

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
‹‹ የእነ ዶ/ር ደብረጺዮን ቡድን ከፍተኛ የስልጣን ጥመኛ ነው ›› ባይቶና

በህወሃት ነባር አመራሮችና በጊዚያዊ አስተዳደሩ ሃላፊዎች መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ ተከትሎ የተለያዩ አስተያየቶች መሰጠታቸው እንደቀጠለ ነው፡፡

የባይቶና አባይ ትግራይ ፓርቲ ምክትል ሊመንበር የሆኑት አቶ ዮሴፍ በርሄ በትግራይ እየተከሰቱ ላሉ ፖለቲካዊ ቀውሶች የአንበሳውን ድርሻ የሚወስደው ነባሩና በዶክተር ደብረጺዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ቡድን ነው ብሎ ፓርቲያቸው እንደሚያምን ገልጸዋል፡፡

በክልሉ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እንዳይኖር፣ስርአት አልበኝነት እንዲበራከትና መሰል ችግሮች እንዲፈጠሩ በታችኛው መዋቅር ያሉና ነባሩን የህወሃት መዋቅር የሚደግፉ አመራሮች ፈተና ሆነዋል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ አንጻር ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሻለ የፖለቲካ አመለካከት አለው ለማለት ያስደፍራል ያሉት ምክትል ሊቀመንበሩ ያም ቢሆን ግን ችግሮችን ከመፍታትና የህዝብን ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ ሁለቱ ቡድኖች ስልጣንን የመጀመሪያ ጉዳይ አድርገው መሻኮታቸው ግባቸው ምን እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነው ብለዋል፡፡

ላለፉት 50 ዓመታት ትግራይን ወጥሮ የያዘው የአንድ ፓርቲ አስተሳሰብ መወገድ እንዳለበት እናምናለን ያለው  ፓርቲው ይህንን ለማድረግም የሚጠበቅብኝን የቤት ስራ እየሰራሁ ነው ሲል ገልጿል፡፡
አዲስ ማለዳ

@sheger_press
@sheger_press
የደብረፂዮኑ የህወሓት ክፋይ ዛሬ ባወጣው መግለጫ "ይቅርታ ጠይቀው ወደ ፓርቲው እንዲቀላቀሉ የሰጠኋቸውን የአንድ ወር ጊዜ ሳይጠቀሙበት ወሩ በመገባደዱ ከፓርቲው አባርሬያቸዋለው" ያላቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል !

ከተባረሩት ውስጥ አቶ ጌታቸው ረዳም ይገኙበታል።

@sheger_press
@sheger_press
ጥቆማ‼️

ቴሌግራምን በመጠቀም ብቻ በርካቶች በርካታ ብር በማግኘት ላይ ናቸው።

እናንተም ይህን ቻናል በመቀላቀል ሙሉ ትምህርት ማግኘት ትችላላቹ።

Join us👇👇👇👍
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
አስቸኳይ ስብሰባ በሶማሊያ እየተካሄደ ነው‼️

የሶማሊያ የፌደራል መንግስት ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ፣የፓርላማ አፈ ጉባኤ ሼክ አዳነ ማዶቤ እና ጠቅላይ ሚንስትር ሃምሳ አብዲ ባሬ አስቸኳይ ስብሰባ እያካሄዱ መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል። ይህ ስብሰባ በሶማሊያ እና በደቡብ ምዕራብ አስተዳደር መካከል ባለው ውጥረት ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል።

ዛሬ ከሰአት በኋላ የደቡብ ምዕራብ ፕሬዝዳንት አብዲካሲስ ላፍታጋሬን እና የሶማሊያ ፓርላማ አፈ-ጉባኤ ሼክ አዳነ ማዶቤ በስልክ ተወያይተው የነበረ ቢሆንም ያለስምምነት መጠናቀቁ ተዘግቧል።

መረጃው እንደሚያመለክተው ሼክ አዳነ ማዶቤ ላፍታጋሪን ወደ ሞቃዲሾ እንዲመጡ ቢጠይቁም ላፍታጋሬን ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉን ነው የተገለፀው።

በውይይታቸውም ሁለቱ ባለስልጣናት እላፊ ቃላት መለዋወጣቸው የተነገረ ሲሆን የሁለቱ ወገኖች ግጭት ምን ያህል የሰፋ እንደሆነ ያሳያል ተብሏል::

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዜና ዕረፍት‼️

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት የሀዘን መልዕክት ሀገራቸውን በሞያቸውና በሚፈለግባቸው መስክ ሁሉ ሲያገለግሉ በኖሩት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸዋል።

ፈጣሪ ነብሳቸውን በአጸደ ገነት ያኑር፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸዉ መጽናናትን እመኛለሁ ብለዋል።

በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በዋና ዳሬክተርነት ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ፍርድ ቤቱ እነ ዮሀንስ ዳንኤል የጠየቁትን የዋስትና መብት ከለከለ

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ የግዜ ቀጠሮ የወንጀል ችሎት እነ ዮሀንስ ዳንኤል የጠየቁትን የዋስትና መብት ከልክሏል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀው የነበረ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱም በዛሬው ችሎት የዋስትና መብቱን ከልክሏል።

ችሎቱ የክስ መዝገቡን ለመመልከት ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡

የፍትህ ሚኒስቴር አቃቤ ህግ ዳንኤል ዮሐንስን ጨምሮ በስድስት ግለሰቦች ላይ ሶስት ክሶችን መመስረቱ ይታወሳል፡፡

@sheger_press
@sheger_press
📍ጎንደር ከተማ

ከሌሊት ጀምሮ በጎንደር አንዳንድ የከተማው ክፍል አካባቢዎች በመከላከያ ሰራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ መኖሩን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት በጎንደር ከተማ “ገንፎ ቁጭ”ና ማራኪ በተባሉ አካባቢዎች ከባድ ጦር መሣሪያ ጭምር ከሌሊት ጀምሮ እየተተኮሰ ነው፡፡

አንድ የከተማዋ ነዋሪ እርሳቸው ባሉበት ቀበሌ 18 በሚባለው አካባቢ የቀላል መሣሪያ ድምፅ እንደሚሰማ አመልክተው፣ ራቅ ብሎ ደግሞ የከባድ መሣሪያ ድምፅ ይሰማል ብለዋል፡፡ ሌላ ነዋሪ በተመሳሳይ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች የተኩስ ልውውጥ የሚመስል ድምጽ ይሰማል ብለዋል፡፡ ትናንትና በአዘዞና በጎንደር ሆስፒታል አካባቢ ተኩስ እንደነበርም ገልጠዋል፡፡ የዛሬው ከባድ እንደሆነ ያመለከቱት እኚሁ ነዋሪ የከባድ መሣሪያው የተኩስ ድምፅ (እርሳቸው እንደገመቱት የመድፍ ድምፅ) መሬት ያንቀጠቅጣል ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡ ሱቆችና የከተማ ውስጥ እንቅስቃሴዎች በከተማዋ የተገቱ ቢሆንም ፒያሳ በተባለው የከተማው ክፍል የተወሰኑ ባለሦስት እግር ተሸከርካሪዎች ሲንቀሳቀሱ ማየታቸውን አስረድተዋል፡፡

ባለፉት ሁለት ሳምንታት በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ዮሐንስ፣ ሽንፋ፣ ኮኪትና ገንዳ ውኃ ዙሪያ ተመሳሳይ ውጊያዎች በመንግስትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ሲካሄዱ እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል፡፡(DW-Amharic)

@sheger_press
@sheger_press
2024/09/29 13:26:42
Back to Top
HTML Embed Code: