Telegram Web Link
መንግሥት መፍትሔ ያልሰጠው ግን በተደጋጋሚ የቀረበ ጥያቄ👇

👉"ሰራተኛው ኑሮውን እንዴት እንደሚመራ ግራ ተጋብቷል" ኢሰማኮ

የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል አለመወሰን ለሰራተኞች የመኖር እና የአለመኖር ጉዳይ ሆኗል ሲሉ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ አስታወቁ።

በአሁኑ ወቅት በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኙ ሰራተኞች ደመወዝ 5 ሊትር ዘይት እንኳን አይገዛም ያሉት የኢሰማኮ ፕሬዝዳንት አቶ ካሳሁን ፤ በተለይ የፋብሪካ ሰራተኞች ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን አብራርተዋል።

አቶ ካሳሁን ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲስተካከል የቀረቡ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ምላሽ አለማግኘታቸውንና በቅርቡም ጥያቄው በድጋሚ ለመንግስት መቅረቡን ተናግረዋል።

ኮንፌደሬሽኑ ከዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ባሻገር የገቢ ግብር ቅነሳን የሚመለከት ጥያቄ ቢኖረውም በአፋጣኝ ይመለሳሉ ወይ በሚለው ዙሪያ ስጋት አለው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ለሰራተኛው በቶሎ መልስ ይሰጠው ዘንድ ጠይቀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የሱማሊያዉ ፕሬዝዳንት ክተት አወጁ‼️

የሱማሊያዉ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼህ መሀመድ ሁሉም የሶማሊያ ዜጋ እና አመራር ለወታደራዊ ግዳጁ ይዘጋጂ ሲሉ ቀጭን ትእዛዝ አስተላልፈዋል ፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መረጃ‼️

እስካሁን ከ1,000 በላይ የግብፅ ኮማንዶዎች ሶማሊያ ማረፋቸውን የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የዜና አገልግሎት መረጃ ያመላክታል።

ትናንት የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አምስተኛ ምዕራፍ ሙሌትን በመቃወም ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ደብዳቤ ያስገቡ ሲሆን በደብዳቤው ላይ "ግብጽ ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ባለችው ግድብ ምክንያት የውሃ ደኅንነቷን ለማረጋገጥ አስፈላጊው የሆነ እርምጃ የመውሰድ መብት አላት"ብለዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አስመራ የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ጀምሮ እንደሚያቋርጥ አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ በረራውን ያቋረጠው በኤርትራ ውስጥ አገልግሎቱን ለመስጠት ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ የአሰራር ችግር ነው፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዜና ሹመት

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ለተለያዩ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጥተዋል።

በዚህ መሠረት፦

1. አቶ አወቀ አስፈሬ ሁነኛው - የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ

2. አቶ ተስፋሁን ሲሳይ መንግስቴ - የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ

3. አቶ ማስተዋል አሰሙ ወንድማገኘሁ - በዞን ምክትል አስተዳዳሪ ማዕረግ የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሕዝብ ግንኙነትና አደረጃጀት አማካሪ

4. አቶ ጌታዬ ሙጬ ደርሰህ - የሰሜን ጎጃም ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል፡፡

ተሿሚዎች በተለያዩ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነቶች የሠሩ ሲሆን የላቀ ዕውቀት፣ ብቃት፣ ቁርጠኝነት እና ታታሪነት ያላቸው ስለመሆኑም ተገልጿል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በኢትዮጵያ ሲሰለጠኑ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጦር አባላት ስልጠናቸውን አጠናቀው መመረቃቸው ተገለጸ

ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ #የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጦር አዳዲስ ምልምል አባላት ከኢትዮጵያ መከላከያ ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠናቸውን ጨርሰው መመረቃቸው ተገለጸ።

ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የተመረቁት የሶማሊንድ ወታደሮች በኢትዮጵያ ከአንድ አመት በፊት ጀምሮ በተከታታይ ዙር የተጠናከረ ስልጠና ሲሰጣቸው ከነበሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት መካከል መሆናቸውን እና 8ኛ ዙር ሰልጣኞች መሆናቸውን ሆርን ዲፕሎማት በድረገጹ አስነብቧል።

በታላቅ ድምቀት በተካሄደው የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የሁለቱም ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት መታደማቸውን የጠቆመው ዘገባው በሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ወታደራዊ ትብብር አጉልቶ ያሳየ ነው መባሉን አስታውቋል።

በምረቃ ስነስርአቱ ላይ በክብር ከታደሙት እንግዶች መካከል የሶማሌላንድ ብሄራዊ ጦር አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኑህ እስማኤል ታኒ ይገኙበታል ያለው የድረገጹ ዘገባ የጦር አዛዡ በምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ መገኘት ሶማሌላንድ ብሔራዊ የመከላከያ አቅሟን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ያሳየ ነው ነው ሲል ገልጿል።ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በርካታ የሶማሊላንድ ወታደሮች በተከታታይ በኢትዮጵያ ስልጠና መውሰዳቸውንም አውስቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ከጎንደር ከተማ አሥተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት   የተሰጠ  መግለጫ‼️

እስካሁን በዘረፋ እና እገታ ወንጀል የተጠረጠሩ 92 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ከቅርብ ጊዚያት  ወዲህ  በከተማችንና አካባቢው የተለያዩ   ወንጀሎች  መከሰታቸውና  የብዙ ወገኖቻችን ሰላምና ደህንነት የሚያውክ  ድርጊት እየተፈፀመ  ከመሆኑ ጋር ተያይዞ  ወገኖቻችንን  ያሳዘነና  ልብ  የሰበረ  መሆኑ ይታዎቃል። በተለየም ደግሞ ራሳቸውን  መከላከል  በማይችሉ  በሴቶች፣ በህፃናት እና  በአረጋውያን   ላይ ያነጣጠረ አፈና፣  እገታ  እና  ግድያ ሲፈጸም ቆይቷል።

የከተማችን ሕዝብ በተለያዩ ጊዚያት  የችግሩን መንስኤ በውል በመለየት  በጥፋተኞች ላይ የሕግ የበላይነትን  እንድናስከብር የገለጸልንን ሐሳብ መነሻ በማድረግና ተጨማሪ ሥራዎችን በመሥራት በእገታ፣  በግድያና በዘረፋ  ወንጀል የተጠረጠሩ  49 ግለሰቦችን    በቁጥጥር ሥር አውለናል ።

ነሐሴ 27/16 ዓ.ም በከተማችን በተፈጠረው ችግር ምክንያት  ስለተጎዱ ወገኖቻችን ጉዳዩን አጣርተን የምንወስደውን ሕጋዊ እርምጃ ውጤቱን ለሕዝባችን የምናሳውቅ ይሆናል ።

ሌሎች ቀሪ ተጠርጣሪዎችን ለመቆጣጠር ሥራ  እየሠራን ባለንበት ወቅት የከተችንን ሰላም እና ደህንነት  የማይሹ ኃይሎች  የግል ጥቅማቸውን ለማጋበስ ሲሉ ከጎንደር እሴት ባፈነገጠ ሁኔታ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም የእናትና ልጅ ግድያ ተፈፅሟል። ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም ከእናቷ ጡት ነጥቀው የሁለት ዓመት  ህፃን በማገት  300 ሺህ ብር ከተቀበሉ  በኋላ   ገድለው ከወላጆቿ ግቢ ጥለዋታል።

የእናቷን ጡት  ሳትጠግብ በጠዋቱ  ሕይወቷን በተነጠቀችው ህፃን  ልጃችን፣ ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም በዚሁ  አረመኔና ጨካኝ ቡድን  ሕይወታቸውን  ባጡ የእናትና  ልጅ  ሕልፈተ ሕይወትና ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም   በተፈጠረው ችግር ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን የፀጥታ ምክር ቤቱ የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለተጎዱ ቤተሰቦች ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና  ለመላው የከተማችን ሕዝብ  መፅናናትን እንመኛለን።

የጋራ ፀጥታ ምክር ቤቱ  የተከሰተውን ግጭት  ለማስቆም ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት በወንጀሉ የተሳተፉ አካላትን ለሕግ የማቅረብ እና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ  ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው።

ወንጀለኞችን ለመቆጣጠር፣ የሕግ የበላይነትን  ለማረጋገጥ እና የከተማችንን ሰላም ለመጠበቅ ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ ድምፅ አልባ  መሣሪያ እና ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ  መንቀሳቀስ፣  በተደራጀም ይሁን በተናጠል በከተማችን ወንጀል   መፈፀም ፍፁም ሕገ ወጥና  የተወገዘ ተግባር ነው ። 

የተከበራችሁ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ወጣቶች የሰው ሃብት እና ንብረት ዘርፈው ለመክበር  የቋመጡ  ኃይሎች ከተማውን ለመዝረፍ  የተሰለፋ መሆኑን ተገንዝባችሁ ከመንግሥት ጎን በመቆም የምትወዷትን ከተማችሁን ከአጋችና ከዘራፊ   ቡድን እንድትጠብቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን"ብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
ጥቆማ‼️

ቴሌግራምን በመጠቀም ብቻ በርካቶች በርካታ ብር በማግኘት ላይ ናቸው።

እናንተም ይህን ቻናል በመቀላቀል ሙሉ ትምህርት ማግኘት ትችላላቹ።

Join us👇👇👇👍
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
ትናንት በጎንደር ከተማ የሕፃን ኖላዊት ግድያን ለመቃወምና ሀዘናቸዉን ለመግለጽ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ  ቢያንስ አምስት ሰዎች መገደላቸውን እና ሶስት ሰዎች ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸውን ከጎንደር ከተማ ነዋሪዎች የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል ።

@sheger_press
@sheger_press
ፋኖ እና መንግሥትን ለድርድር የሚያመቻቸው ምክር ቤት ከአሜሪካ አምሳደር ጋር ዛሬ ይነጋገራል ‼️

ገጥመውኛል ካላቸው ውስብስብ ፈተናዎች መካከል በመንግሥት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ያለው ስር የሰደደ አለመተማመን አንዱ ነው።

ሌላኛው ምክር ቤቱ ገጥመውኛል አካላቸው ችግሮች መካከል የፋኖ ታጣቂዎች አንድ ወጥ አደረጃጀት አለመኖር ነው። የፋኖ ታጣቂዎች አደረጃጀት የወሎ፣ የሸዋ፣ የጎንደር እና የጎጃም በሚል በተናጠል አደረጃጀትና መሪ የሚንቀሳቀሱ መሆናቸውን ምክር ቤቱ በግምገማ ሰነዱ ላይ ጠቅሷል።

እንዲሁም በክልሉ እና በአጎራባች ክልሎች የቀጠለው አለመረጋጋት እና ሁከት ለሰላም ምክር ቤቱ እክል እንደሆነበት ይገልፃል። ክልሉ እንደ በትግራይ እና ኦሮሚያ ክልሎች በኩል የብሔር ግጭት አውድ መቀጠሉ ለሰላም ምክር ቤቱ ጥረት እንቅፋት መፍጠሩን ያስረዳል።

ካውንስሉ ከዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡ ጋር ወደ ውይይት ከማምራቱ በፊት በመንግሥት በኩል ከክልል እስከ ፌደራል ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መክሯል። በክልል  ደረጃ ከአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ ጋር እንዲሁም በፌደራል ደረጃ ከሰላም ሚኒስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ጋር ከሰሞኑ መወያየቱን የዋዜማ ምንጮች አስታውሰዋል።

@sheger_press
@sheger_press
Update‼️

በአዲስ አበባ አፄ ቴዎድሮስ አደባባይ ለዕድሳት ተብሎ የተነሳው የሴባስቶፓል መድፍ ሀውልት ወደ ቦታው ተመልሷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ከሸዋ አማራ የሚወጡ የአዉደ ግንባር መረጃዎችን በፍጥነት በታማኝነት የሚያደርስ ቻናል ላስተዋዉቃችሁ👇👇👇👇

https://www.tg-me.com/SNN_merja
https://www.tg-me.com/SNN_merja
ማይክ ሀመር በአፍሪካ ቀንደ ወቅታዊ ሁኔታ ለመምከር ወደ #ኢትዮጵያ እና #ኬንያ እንደሚመጡ ተጠቆመ፣ በብራሰልስ ከአውሮፓ ህብረት ጋርም እየመከሩ መሆኑ ተገልጿል
#
#የአሜሪካ መንግስት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ማይክ ሀመር በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ለመምከር ወደ ኢትዮጵያ እና ኬንያ እንደሚመጡ ተገለጸ።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ማይክ ሀመር በብራሰልስ፣ አዲስ አበባ እና ኬንያ ለአስር ቀናት ይቆያሉ።

ትላንት ነሃሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ሀመር #ብራስልስ የገቡ ሲሆን ዋነኛ አጀንዳቸውም በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከአውሮፓ ህብረት እና የአሜሪካ አጋር ከሆኑ ተቋማት ጋር መምከር ነው ተብሏል።

ሀመር #በናይሮቢ በሚኖራቸው ቆይታ ከኬንያ ባለስልጣናት ጋር በቀጠናው የጸጥታ ሁኔታ እንደሚመክሩ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው አትቷል።

ሀመር በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከአፍሪካ ህብረት እና ኢጋድ ባለስልጣናት ጋር በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ እንደሚመክሩ መስሪያቤቱ በመግለጫው አመላክቷል።

ኢትዮጵያን በተመለከተ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው እንዳስታወቀው ሀመር በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ዙሪያ ከሁለቱ ተፈራራሚ አካላት ጋር ይመክራሉ ብሏል።

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማስቻል አሜሪካ የፌደራል መንግስቱን እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለማገዝ አሁንም ቁርጠኛ ናት ያለው መስሪያቤቱ በመግለጫው #በአማራ እና #በኦሮምያ ክልል ግጭቶች ዙሪያ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ ጠቁሟል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በጎንደር ከተማ የቀጠለው እገታ‼️

በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በአዘዞ ማርያምበር ቀበሌ ትናንት ከምሽቱ 1:30 ገደማ 4 ሰዎች ታግተው ተወሰደዋል‼️

ሁለቱ በመጠጥ ሽያጭ የሚተዳደሩ ሴቶች ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው።

አንደኛው ከዚህ በፊት ፖሊስ የነበረና ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚሰራ ሰው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ባለቤቱ ገቢዎች የምትሰራ ግለሰብ መሆናቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press
2024/10/02 16:33:19
Back to Top
HTML Embed Code: