Telegram Web Link
ታገቱ‼️

ዛሬ ጠዋት በኦሮሚያ ክልል ከገብረ ጉራቻ እና ቱሉ ሚልኪ መሀከል አንድ የህዝብ አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪ ከሾፌር ረዳት ጋር በዘራፊ ወንበዴዎች በታጠቁ ሀይሎች ታፍነው መወሰዳቸው ተሰምቷል።

@sheger_press
@sheger_press
ምንም አይነት የደሞዝ ጭማሪ ሳይደረግ የሸቀጦች እና የምግብ አይነቶች ዋጋ ላይ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ እስከ 50 ፐርሰንት ጭማሪ በተፈጠረበት ሁኔታ እንደገና ሌላ ታክስ በውሀ፣ ኤሌክትሪክ፣ ትራንስፖርት ወዘተ ላይ ማዥጎድጎድ ምንድን ነው?

ሰዉን ባትፈሩ ፈጣሪን...!

EliasMeseret

@sheger_press
@sheger_press
ምን አይነት ዘመን ላይ ነው ያለነው ግን⁉️

ያሳዝናል ይህ ድርጊት ዛሬ ጠዋት ገርባ የተከናወነ ነው

ደቡብ ወሎ ቃሉ ወረዳ ገርባ ከተማ ቀጨማ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ አሁነ ላይ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለች አንድ እናት ነሐሴ 17/2016 የወለደችውን ህፃን ልጅ ሽንት ቤት ጥላ ዛሬ ነሐሴ 23/2016 ተገኝቷል።

የአካባቢው ፖሊሶችና የገርባ ጤና ጣቢያ ባለሙያዎች ከማህበረሰቡ ጋር  የህፃኑን አስክሬን ከሽንት ቤት ወጥቶ በክብር እንዳሳረፈ ገልፀዋል።

ሴቶች ወልዳችሁ የማታሳድጉትን አትፀንሱ:ተከላከሉ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Blum‼️

በዚ ሰአት ከBlum የተሻለ ኤርድሮፕ የለም

እኔ በግሌ ከኖትኮይንም ከዶግስም የተሻለ ይሆናል ብዬ የማስበው Blum ብቻ ነው

በተለያየ በብዙ አካውንት ስሩት ፤ በእርግጠኝነት ብዙ ነው የምታተርፉበት 😊

Blum ላልጀመራቹ  በዚ ጀምሩ👇👇👇

https://www.tg-me.com/blum/app?startapp=ref_JhjvJ1zEys

https://www.tg-me.com/blum/app?startapp=ref_JhjvJ1zEys‌‌

ስለ አጨዋወቱ ለማወቅ ይህንን ቻናል ይቀላቀሉ👇👇
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደሩ የተሿሚዎችን ምደባና የአስተዳደሩን ሌሎች ተግባራት በሚያደናቅፉ አካላት ላይ ሕጋዊ ርምጃ እንደሚወስዱ አስጠንቅቀዋል።

ጌታቸው ይህን ማስጠንቀቂያ ያስተላለፉት፣ የሕወሓት አመራሮች የጊዜያዊ አስተዳደሩን አዳዲስ ሹመቶች እንደማይቀበሉ መግለጣቸውን ተከትሎ ነው።

ጌታቸው ትናንት ባወጡት መግለጫ፣ የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካዔል የሚመሩት ቡድን በክልሉ ሥርዓት አልበኝነትን ለማስፈን ጥረት እያደረገ ይገኛል በማለት ከሰዋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሕዝቡን ባግባቡ የማገልገል ሃላፊነቱን ለመውጣት በተለያዩ የክልሉ መዋቅሮች ሹም ሽሮችን ማድረግ እንደሚቀጥልም ጌታቸው ጠቁመዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቱሉ ሚልኪ እና ገርበ ጉራቻ ከተማ መካከል በተለምዶ "ታታ" ተብሎ በሚጠራ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ የተሳፈሩ ተሳፋሪዎችን በሙሉ ዛሬ ረፋዱ ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ታፍነው እንደተወሰዱ ዋዜማ ከአካባቢው ነዋሪዎች ሰምታለች።

ታጣቂዎቹ፣ የአንድ አምቡላንስ ሹፌር እና አንድ የጤና ባለሙያ ጭምር አፍነው መወሰዳቸውን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል፡፡

የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሱ መነሻውን ከአማራ ክልል አድርጎ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ እንደነበር ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል፡፡

የመከላከያ ሠራዊት አባላት ድርጊቱ ከተፈጸመ በኀላ ከአካባቢው መድረሳቸውንና ኾኖም ታጋቾችን ማስለቀቅ እንዳልቻሉም ለመረዳት ተችሏል።

ነዋሪዎቹ፣ አካባቢው ካሁን ቀደምም ተመሳሳይ የአፈና ድርጊቶች ሲፈጸሙበት እንደቆየ ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press
Update‼️

ትናንት ጠዋት አካባቢ ከጎጃም ወደ አዲስ አበባ በባስ ሲጓዙ የነበሩ ተሳፋሪዎች በኦሮሚያ ክልል ከገብረ ጉራቻ እና ቱሉ ሚልኪ መሀከል አንድ የህዝብ አውቶብስ ሙሉ ተሳፋሪ ሾፌርና ረዳቱን ጨምሮ በታጣቂዎች መታገታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

የታጋቾቹ ቁጥር አጠቃላይ 60 የሚሆኑ ሲሆን ቤተሰቦቻቸው በጭንቀት እያለቀስን ለመቀመጥ ተገደናል ብለዋል።

አጋቾቹ የት እንዳደረሷቸው እስካሁን ምንም የምናውቀው ነገር የለም ብለዋል። ታጣቂዎቹ እገታውን ተረጋግተው እና ወደ ሰማይ ጥይት እየተኮሱ ጭምር እንደፈፀሙት ምንጮች ተናግረዋል።

ከታገቱት ሰዎች አብዛኞቹ ህፃን የያዙ ሴቶች እና አዛውንቶች ናቸው። (ayu)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በማረቆ 7 ሰዎች ተገደሉ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረቆ ልዩ ወረዳ ማንነትን መሠረት ያደረገ ነው በተባለ ጥቃት አራት የአንድ ቤተሰብ አባላትን ጨምሮ ሰባት ሰዎች ተገደሉ ፡፡

ግድያው የተፈጸመው በልዩ ወረዳው ዲዳ ሀሊቦ በተባለ ቀበሌ ውስጥ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡

የሟቾቹ የቅርብ ቤተሰብ አባል መሆናቸውን ለዶቼ ቬለ የተናገሩትና አቶ ሁሴን ለመንጎ የተባሉ የዲዳ ሀሊቦ ቀበሌ ነዋሪ ታጣቂዎቹ ጥቃቱን ባለፈው ማክሰኞ የፈጸሙት ሟቾቹ ሌሊት በተኙበት የተኩስ እሩምታ በመክፈት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በጥይት ከተመቱት አሥራ አንድ ሰዎች መካከል የሰባቱ ህይወት ወዲያ ማለፉን የጠቀሱት የዓይን አማኙ “ ከሟቾቹ መካከል አራቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ ሁለቱ ህጻናት ናቸው ፡፡ ቀብራቸውም ትናንት ሐሙስ ተከናውኗል “ ብለዋል ፡፡

ጥቃቱ ማንነትን መሠረት ያደረገ ፣ ዘግናኝና ታቅዶ በህጻናትና ሴቶች ላይ የተፈጸመው መሆኑን የጠቀሱት የሟች ቤተሰብ አሁን ላይ በጥቃቱ የቆሰሉት አራት ሰዎችን ደግሞ በወራቤ ሆስፒታል አስገብተናል ” ብለዋል ፡፡

ዘገባ ሸዋንግዛዉ ወጋየሁ ከሃዋሳ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ግብጽ ጦር መሳሪያዎችን፣ ወታደራዊ ቁሳቁሶችንና ወታደሮቿን ወደ ሱማሊያ መላክ መቀጠሏን የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ጋዜጣ ዘ ናሽናል ዘግቧል።

ከማክሰኞ እስከ ትናንት ምሽት ድረስ ወታደሮችንና ጦር መሳሪያዎችን የጫኑ ስምንት የግብጽ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ሞቃዲሾ ማረፋቸውን ከምንጮቹ እንደሰማ ዘገባው አመልክቷል።

ግብጽ ጸረ-ታንክ ሚሳይሎችን፣ ተወንጫፊ ሮኬቶችን፣ ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎችን፣ ራዳሮችንና ድሮኖችን ወደ ሱማሊያ የመላክ እቅድ እንዳላት መስማቱቱንም ዘገባው ጠቅሷል።

ግብጽ ወታደሮቿን ከሞቃዲሾ ውጭ በፌደራል ግዛቶች በቋሚነት የማሠማራት እቅድ ይኑራት አይኑራት ለጊዜው ግልጽ ባይኾንም፣ የሱማሊያን ወታደሮች የማሰልጠን ዓላማ እንዳላት ግን ብሉምበርግ ምንጮችን ጠቅሶ ሰሞኑን ዘግቦ ነበር።

@sheger_press
@sheger_press
ክቡርነትዎ፣

ሀገራችን ለም እና ቆንጆ ናት። ይሁንና:

- ህዝቡ ልጆቹን ሞፈር አሸክሞ 'ሰላም አውርዱልን' እያለ ከፈጣሪው አልፎ የሰው ልጅን እየለመነ ነው፣

- በትናትናው እለት ብቻ ሰሜን ሸዋ ላይ በርካታ ሰዎች ታግተው ተወስደዋል፣ በየቀኑ ለቁጥር የሚታክቱ ዜጎች በታጣቂዎች እንደ እንስሳ እየተነዱ ወደ ጫካ ይወሰዳሉ፣

- እርስዎ የወጡበት የአማራ ክልል ውስጥ እንኳን በየቀኑ ለቁጥር የሚታክት ህዝብ በጥይት እያለቀ ነው፣

- በጦርነት የተዳከመ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ በኑሮ ጫና እያለቀሰ ነው፣

- ዛሬ እንኳን ወደ ኦሞ ዞር ብንል ወንዝ ሞልቶ ህዝብ ከዛሬ ነገ ተዋጥኮ ብሎ የድረሱልኝ ጩኸት እያሰማ ነው።

እውነት አሁን ያለንበት ግዜ የምድር ገነት መሆናችንን እንድናስብ እና ውበቷን እንድናጣጥም የሚያረገን ነው አንገት የሚያስደፋ ሁኔታ ውስጥ ነን?

We need some soul searching!

EliasMeseret

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
🚨ATTENTION!!! 🚨

🌀 የዋጋ ግሽበት ከመቼውም በላይ እየጨመረ ይገኛል :: #Ethiopia ከዓለም በዋጋ ግሽበት 10 ኛ ደረጀ ላይ ተቀምጣለች :: በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ፤ ብሮትን ባንክ ውስጥ በማስቀመጥ በየሰከንዱ ዋጋ ሲያጣ አትዩት!!

🌀 ብሮትን አሰሩት፤ በኢትዮጵያ ትልቁ የኢኮኖሚ ሴክተር ላይ ኢንቨስት በማረግ በያመቱ ትርፍ የውሰዱ!!!

"ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ...."
💰💰 አክሲዮን ድርሻዎችን በመግዛት የግዙፍና አትራፊ ድርጅቶች ባለቤት ይሁኑ፣ለልጅ ልጅ የሚተላለፍ ሐብት ያፍሩ፣ገንዘብዎትን ከግሽበት ይጠብቁ፤እጥፍ ድርብ ትርፍ ያግኙ!

💰💰 በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ኢንቨስት በማድረግ በአማካይ ከ30 እስከ 45 ፐርሰንት(Dividend + Capital gain) ትርፍ ማግኘት ይቻላል!

🛑የባንክ ባለቤት በመሆን 30%-45% ማትረፍ ይፈልጋሉ?
🛑መሉ መረጃውን ከላይ በፎቶ ተያይዞዋል ፈጥነው አክሲዮን በመግዛት አትራፊ ይሁኑ ለበለጠ መረጃ ከታች ባለው ስልክ መደወል ይችላሉ።
  📲0913013439📲
  📲0913013439📲

ለበለጠ መረጃ በTelegram ይቀላቀሉን:
👉 www.tg-me.com/stockBKGH or
👉 www.tg-me.com/stockEthio
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ የመንግስት መ/ቤቶች ንብረት ያላግባብ በሀላፊዎች እጅ እንደሚገኝ በኦዲት መረጋገጡ ተገለጸ!

የኦዲት ምርመራው 13 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት በሀላፊዎች እጅ እንደሚገኝ አሳይቷል፡፡በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 269 ተቋማት ላይ በተደረገ የንብረት ቆጠራ ወደ 24 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት በጉድለት መገኘቱም ተጠቁሟል።ጉድለት የተገኘባቸው የተቋማት ሃላፊዎች ላይም እርምጃ እንደተወሰደባቸውም ተነግሯል።

የአዲስ አበባ ከተማ የመንግስት ንብረት አስተዳደር_ባለስልጣን የህንፃና ንብረት ኦዲት ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ምሩጽ ታዬ፤ በተቋማቶች ላይ ከተገኘው ጉድለት ውስጥ ወደ 10.9 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት እንዲመለስ ተደርጓል ብለዋል።አቶ ምሩፅ አያይዘውም በተቋማቱ ከተመዘገበው ንብረት ላይ ጉድለት የተገኘባቸው ሃላፊዎች ከስራ ገበታ እንዲባረሩ እና በህግ እንዲጠየቁ ተደርጓል ማለታቸውን የሸገር ሬድዮ ዘገባ ያሳያል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ፑቲን እንዲታሰሩ ተጠየቀ❗️

ዩክሬን የሩሲያው ፕሬዝደንት ብላድሚር ፑቲን በሚቀጥለው ሳምንት ሞንጎሊያን በሚጎበኙበት ወቅት ሀገሪቱ በቁጥጥር ስር እንድታውላቸው ጠይቃለች።

ፑቲን አለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት(አይሲሲ) የእስር ማዘዣ ካወጣባቸው ወዲህ የፍርድ ቤቱ አባል ወደ ሆነች ሀገር የሚያደርጉት ይህ ጉብኝት የመጀመሪያቸው ይሆናል።
ፍርድ ቤቱ በፑቲን ላይ የእስር ማዘዣ ያወጣባቸው የዩክሬን-ሩሲያ ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የዩክሬን ህጻናትን ያለፍቃዳቸው ወደ ሩሲያ በመውሰድ የጦር ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ምክንያት ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

ቴሌግራምን በመጠቀም ብቻ በርካቶች በርካታ ብር በማግኘት ላይ ናቸው።

እናንተም ይህን ቻናል በመቀላቀል ሙሉ ትምህርት ማግኘት ትችላላቹ።

Join us👇👇👇👍
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
ባጃጅ ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ለውጥ ማድረግ እንደሚጠብቅባቸው የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳሰበ

AMN - ነሐሴ 25/2016 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የባለሶስት እና አራት እግር ወይም ባጃጅ ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ለውጥ ማድረግ እንደሚጠብቅባቸው የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳስቧል።

ቢሮው በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት የከተማዋን የትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ በበላይነት ይመራል፣ ይቆጣጠራል እንዲሁም የአሰራር ስርዓት ይዘረጋል።

ቢሮው አሁን ያለውን የባለሶስት እግር ወይም ባጃጅ ተሽከርካሪዎችን የሕግ ጥሰቶችን እና የደንብ መተላለፎችን ለመከላከል እና አገልግሎት አሰጣጡን ለመቆጣጠር እንዲያስችል ከዚህ ቀደም በህጋዊ ማህበር በመደራጀት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ባለንብረቶች ተሽከርካሪው ከነበረበት ክልል ክሊራንስና የአዲስ አበባ ነዋሪነት ማረጋገጫ መታወቂያ በማቅረብ ምትክ የአዲስ አበባ ሰሌዳ ማውጣት እንደሚገባ አሳውቋል።

ይህንን አሟልተው እስኪገኙ ማንኛውም የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በከተማዋ ከነገ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ቢሮው በጥብቅ አሳስቧል።

ወደ አገልግሎት ለመመለስ ቀደም ሲል አገልግሎቱን ሲሰጡበት ከነበረው የትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስፈላጊውን ህጋዊ መረጃ በማሟላት ቢሮው በሚያስቀምጠው የአሰራር ስርዓት መሰረት አገልግሎቱን መስጠት እንሚቻል ቢሮው በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ ባወጣው መልዕክት አሳውቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 23:36:34
Back to Top
HTML Embed Code: