Telegram Web Link
Ava Coin‼️

Ava coin 100% የተረጋገጠና ከ7 ቀን በኋላ List የሚደረግ ፕሮጀክት ነው።

July 30 List የሚደረግ ሲሆን ልክ እንደ Notcoin Claim ለማድረግ ምንም እንደማያስከፍሉ አሳውቀዋል

list ሊደረግ ጥቂት ጊዜ ስለቀረው እናንተም ቶሎ ጀምሩ👇👇

በዚ Link ጀምሩ👇👇
https://www.tg-me.com/avagoldcoin_bot?start=0505479c43fb59089e2d
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ፋኖ‼️

ፋኖቁጥራቸዉ በዉል ያልታወቁ ሰላማዊ ሰዎችን ገድሏል ሲል የሟቾችን የስም ዝርዝር በማዉጣት ጭምር የአማራ ክልል መንግስት ከሰሰ

በሰሜን ጎጃም ዞን ፣ በደቡብ ሜጫ ወረዳ ልዩ ስሙ ገርጨጭ በሚባል አካባቢ ነዋሪ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ለተለያዩ ስራዎች ወደ ባህር ዳር አቅንተዉ ሲመለሱ የሰላም ኮሚቴ አባላት ለመሆን ነው በሚል ምክንያት የሀይማኖት መሪዎችን ፣ የሀገር ሽማግሌዎችንና እናቶችን ፋኖ ገድሏል ሲል ወንጅሏል።

ዳጉ ጆርናል ከክልሉ መግለጫ እንደተመለከተዉ ከሆነ ተገደሉ የተባሉ ሰዎች ቁጥር ባይጠቀስም የክልሉ መንግስት የተወሰኑትን ስማቸዉን ጠቅሷል።

ፋኖ ሰላማዊ ናቸዉ የተባሉ ሰዎችን ከ።ግደሉ በፊት በእንብርክክ በማስኬድ ኢ-ሠብዓዊ የሆነ ቅጣት በመቅጣትና የደከመ ሰውነታቸውን አንገላቷል ሲል ተንቀሳቃሽ ምስዕልም በገጹ ላይ ማጋራቱን ዳጉ ጆርናል ታዝቧል።

የጭካኔው ሰለባ ከሆኑት መካከልም የወረዳው ቤተ ክህነት ስራ አስኪያጁ መርጌታ ግሩም ፣ የሀገር ሽማግሌ አቶ አዘነ አድማሱ ፣ የሀገር ሽማግሌ አቶ አስማማው አቤ ፣ ወ/ሮ የኔአየሁ ዳኛው የተባሉ የከተማው ነዋሪ ይገኑባቸዋል ሲል ግድያ የተፈጸመባቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል፡፡

በተጨማሪም 13 ሰዎች አሁንም በእስር ላይ የሚገኙ ሲሆን ታግተዉ እንደሚገሙም አመላክቷል።

የክልሉ መንግስትም በተፈጸመዉ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ ድርጊቱን የፈፀሙ ሰዎችን ለህግ የሚያቀርብ መሆኑን እየገለፅን ለተጎጅ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝቷል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ጎፋ‼️😥

በጎፋ ዞን በደረሰ የመሬት ናዳ የሟቾች
ቁጥር ከ265 በላይ መድረሱ ተነገረ


30 ሰዎች በአፈር ናዳ ውስጥ ይገኛሉ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበል በትላንትናው እለት ሀምሌ 15 ከረፋዱ 4:00 ሰዓት አካባቢ በደረሰ የመሬት ናዳ የሟቾች ቁጥር ከ265 በላይ መድረሱ ተገልጿል፡፡

በቀበሌው ናዳው ከደረሰ በኋላ የሠው ህይወት ለመታደግ ወደ በስፍራው ለነፍስ አድን ተግባር የተሰበሰቡ የአካባቢው ነዋሪዎች የአደጋው ሰለባ መሆናቸውን  ከደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት የተገኘው መረጃ ያመላክታል። 

በትላንትናው እለት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የተለያዩ የፖሊስ አባላትን ይዘው ወደ ቦታው ሲያመሩ ተንሸራተው የነበረ ሲሆን በገመድ ተጓትተው  በህይወት መትረፍ መቻላቸው ተሰምቷል።

ከተለያዩ አካባቢዎች ለእርዳታ የመጡ ነዋሪዎች በቀበሌው በርካቶች በመሆናቸው የነዋሪዎች ቁጥር በውል እንደማይታወቅ ነው የተነገረው፤ በአደጋው ሰለባ ከሆኑት ሰዎች መካከል የወረዳው ፖሊስ አባላትን ጨምሮ ሴቶችና ሕፃናት የሚገኙ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የአስክሬን ፍለጋና የነፍስ አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልፆል።

@ethio_mereja_news
በእያካባቢያችሁ የምታዬቸዉን አስተዳደራዊ የኢኮኖሚ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ችግሮችን  ጥቆማ አድርሱን፡፡
  ጉዳዩን ተከታትለን ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል ፡፡ለጥቆማ👇
      @ETHIO_JOURNAL
የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባትን የ10 ዓመት ህፃን ልጅ አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ የአዕምሮ ውስንነት ያለባትን የ10 ዓመት ህፃን ልጅ ላይ የአስገድዶ መድፈር ጥቃት የፈፀመው ግለሰብ በእስራት መቀጣቱን የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ገልጿል።

የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሳሊም ቱጂሀን ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደገለፁት ተከሳሽ አብዲ አህመድ የተባለው ግለሰብ ታህሳስ 7 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ሳምሴ አካባቢ ላይ ወንጀሉን ፈፅሟል።ግለሰቡ የ10 ዓመቷን ልጅ ወደ ጫካ በመውሰድ የመድፈር ጥቃት ፈፅሞባታል።ድርጊቱን ፈፃሚ ግለሰብ ሮጦ ሊያመልጥ ሲል በአካባቢው የጥበቃ አባላት በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል።

ጉዳት የደረሰባት የ10 ዓመት ልጅ ከፍተኛ የሆነ የማህፀን ግርግዳ መሰንጠቅ እንዳጋጠማት በተደረገ የምርመራ ውጤት ተረጋግጧል።እንዲሁም ሽንቷን መቋጣጠር የማትችልበት ሁኔታ ላይ መሆኗ የህክምና ውጤቷ እንደሚያመላክት ገልፀዋል።

ፖሊስ በህፃኗ ላይ የተደረገውን የምርመራ ውጤት እና የሰው ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢህግ ልኳል።አቃቢህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ ለምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ መስርቷል።

ክሱን ሲመለከት የነበረው የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ አብዲ መሀመድ የአዕምሮ ውስንነት ባለባት ታዳጊ ላይ የፈፀመው የመድፈር ጥቃት ሙሉ በሙሉ በአቃቢህግ ማስረጃ አረጋግጧል።

በዚህም ፍርድ ቤቱ ሀምሌ 12 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ13 ዓመት እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን  አቶ ሳሊም ቱጂሀን ጨምረው ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ህወሓት የቀደመ ሕጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ አንጂ እንደ አዲስ መመዝገብ እንደማይፈልግ አስታወቀ!

ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በፖለቲካዊ ውሳኔ የነበረው ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስለት እንጂ እንደ አዲስ መመዝገብ እንደማይፈልግ የፓርቲው ቃል አቀባይ አቶ አማኑኤል አሰፋ ተናገሩ።አቶ አማኑኤል ባለፈው ግንቦት ወር በምርጫ ሕጉ ላይ የተደረገው ማሻሻያ፤ “የተሰረዘውን [የህወሓት] ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ የሚያስችል ሳይሆን በልዩ ሁኔታ እንደ አዲስ ለመመዝብ የሚያስችል ነው” ሲሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምከር ቤት ያጸደቀው ይህ አዋጅ፤ ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጽ ተግባር ተሳትፎ የነበረ የፖለቲካ ቡድን በፓርቲነት የሚመዘገብበትን ሂደት በዝርዝር ያስቀመጠ ነው።አቶ አማኑኤል “ሕጋዊ ሰውነት እንዴት እንደሚመለስ በምርጫ ሕጉ ግልጽ ስላልሆነ ተጨማሪ [የሕግ] ማዕቀፍ በማዘጋጀት የተሰረዘው ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስ ይደረጋል የሚል ንግግር ነበር” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“ያንን [የሕግ ማዕቀፍ] እየጠብቅን እያለ ማሻሻያ አዋጁ ወጣ” የሚሉት አቶ አማኑኤል፤ “ማሻሻያ አዋጁ [ግን] የተሰረዘውን [የህወሓት] ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ የሚያስችል ሳይሆን በልዩ ሁኔታ እንደ አዲስ ለመመዝብ የሚያስችል ነው” ብለዋል።
ኤርትራ‼️

ኤርትራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመስከረም በኋላ ወደ አስመራ እንዳይበር ክልከላ አደረገች

በኤርትራ የትራንስፖርት እና ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስቴር የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመስከረም 20/ 2017 በኋላ ወደ አስመራ እንዳይበር ማገዱን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፡ “በኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ ስልታዊና በተቀናጀ መንገድ፤ የተጓዦች ሻንጣዎች ላይ ስርቆት መፈጸምና መዘግየት፤ ዘረፋ እንዲሁም የበረራዎች ሰዓት መዘግየትና ካሳ አለመስጠት” እየተፈጸመ ነው ብሏል።

በተጨማሪም የበረራ ትኬት ዋጋ ላይ ተገቢ ያልሆነ ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን ጠቅሷል።

@sheger_press
Hamster‼️

hamster ለምትጫወቱ በሙሉ የግድ ይህን ቻናል መቀላቀል ይኖርባችኋል።

ሁሉንም በዝርዝር ይከታተሉ👇👇
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰሜን ቤንች ፣ ሼይ ቤንችና ሚዛን አማን በ3 ቀበሌዎች ሰሞኑን በተከታታይ በጣለው ዝናብ 28 የመኖሪያ ቤቶች የመሰንጠቅና የመደርመስ አደጋ እንደደረሰባቸውና እስካሁን 208 ለአደጋ ተጋላጭ ሰዎችን ከስፍራው ማውጣት መቻሉን ዞኑ አስታውቋል። ተጨማሪ 4 ቀበሌዎች በከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙም ተሠምቷል።

በክልሉ ጎፋ ዞን ሰኞ ረፋድ በደረሰ የመሬት ናዳ ከ265 በላይ ሠዎች ህይወታቸውን አጥተዋል።

@sheger_press
@sheger_press
ይህ ድርጊት ከባህል፣ከእሴት፣ከስነልቦና አኳያ ሲታይ በርካቶች "ፀያፍ ድርጊት" መሆኑን አውስተዋል‼️

እነዚህ በምስሉ ላይ የሚታዩት አባቶች እና እናቶች እንዲህ በጉልበታቸው እንዲሄዱ ተደርገው በኋላም የተወሰኑት የተገደሉት "የአማራ የሰላም ካውንስል አባል ናችሁ" በሚል ምክንያት ነበር። ድርጊቱ የተፈፀመው የፋኖ ሀይሎች በሚገኙበት ጎጃም ውስጥ ደቡብ ሜጫ ላይ መሆኑ ታውቋል።

ድርጊቱን አዛኝ የሚያደርገው የድርጊቱ ሰለባዎች ከሰላም ካውንስሉ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች እና የአንድ የጤና ተቋም (NGO) ሰራተኞች መሆናቸው ነው።

ከተገደሉት ውስጥ የወረዳ ቤተ ክህነት ስራ አስኪያጁ መርጌታ ግሩም፣ የሀገር ሽማግሌ አቶ አዘነ አድማሱ፣ የሀገር ሽማግሌ አቶ አስማማው አቤ፣ ወ/ሮ የኔአየሁ ዳኛው የተባሉ የከተማው ነዋሪ ይገኙባቸዋል ተብሏል፣ ሌሎች 13 አሁንም በእስር ላይ ይገኛሉ።

ኤልያስ መሰረት

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Update‼️

የኤርትራ አቬሽን ባለስልጣን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ከመስከረም 20/2017ዓ.ም በኋላ እንዲያቆም መወሰኑን ቀደም ብዬ መዘገቤ ይታወሳል።

በዚህ ዙሪያ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህንን ውንጀላውን እንደማይቀበል እና የስም ማጥፋት እንደሆነ ገልጿል።

አየር መንገዱ "በሰማነው ድንገተኛ ውሳኔ አዝነናል፣ በውሳኔው ዙርያ ማብራርያ ለማግኘት ሙከራዎች እያደረግን ነው" ብሏል።

#ኤልያስመሰረት

@ethio_mereja_news
በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ የደረሰውን ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋን በተመለከተ ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ባገኘነው ወቅታዊ መረጃ መሰረት

- አስከሬናቸው የተገኙ ወገኖች ቁጥር 194 ደርሷል
- 600 የሚሆኑ ዜጎች ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል
- የፌደራል መንግስት በኮሚሽኑ በኩል ከ3000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች 520 ኩንታል ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች እርዳታ አቅርቧል
- 100 ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ጥቅል አድርሷል። እያንዳንዱ ጥቅል ለ5 ሰዎች ያገለግላል።
- በአጠቃላይ 5.7 ሚሊዮን ብር የሚገመት የሰብዓዊ ድጋፍ አድርጓል።
ከዚህ በዘለለም ኮሚሽኑ ተጨማሪ የነፍስ አድን ስራው እንዲቀጥልና በአደጋው የስነ-ልቦና ጉዳት የደረሰባቸውም እንዲያገግሙ ከአካባቢው አስተዳደር ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል። ወደ ስፍራው የተላከው አጣሪ የጥናት ቡድን ሁኔታውን እያየ ተጨማሪ ድጋፍ የሚያደርግ ይሆናል።

ተጨማሪ መረጃዎችን ለህዝብ ይፋ ማድረጉንም ይቀጥላል።እስከዛሬዋ እለትም የአካባቢው ማህበረሰብ የሟቾች አስከሬንን በማፈላለግ፣ የተጎዱትን በመንከባከብና ለተፈናቀሉትም መጠለያ በማዘጋጀት በፍፁም ሰብአዊነት ላበረከተው አስተዋፅኦ መንግስት ታላቅ ምስጋና ያቀርባል።

-የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

@ethio_mereja_news
2024/10/01 04:19:51
Back to Top
HTML Embed Code: