Telegram Web Link
በነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ

ከዛሬ ከሀምሌ 3 ቀን 2016 ዓም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ከአውሮፕላን ነዳጅ በስተቀር በቤንዚን፣ በኬሮሲን፣ በነጭ ናፍጣ፣ በቀላል ጥቁር ናፍጣና በከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጎል። በዚህም መሰረት

👉 ቤንዚን …………ብር 82.60 በሊትር

👉 ነጭ ናፍጣ..... ብር 83.74 በሊትር

👉 ኬሮሲን ……….. ብር 83.74 በሊትር

👉 የአውሮፕላን ነዳጅ ……... ብር 70.83 በሊትር

👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ……… ብር 65.48 በሊትር

👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ……… ብር 64.22 በሊትር ሆኗል።

የአለም ገበያ ላይ እየታየ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መሠረት ከሀምሌ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ሥራ ላይ የሚውለው የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማሰተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

@ethio_mereja_news
"በተደረገ ጥብቅ ኦፕሬሽን ከ167 ታጋች ተማሪዎች መካከል 160ዎቹ ተለቀዋል"--- የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ

"እውነት ይሆን?" ብዬ የታጋቾች ቤተሰቦችን፣ የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ወንጌላዊያን ህብረትን እና የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንትን ማምሻውን ጠየቅኩ። ምላሹ ይህን ይመስላል:

"አሁንም ልጆቻችን በእገታ ስር ናቸው፣ የማስለቀቂያ ገንዘብ ከህዝብ እየለመንን ነው። በዚህ ግዜ እንዲህ አይነት መረጃ ማውጣት የጭካኔ ስራ ነው"--- የታጋቾች ቤተሰቦች

"ታግተው ያሉ በርካታ ተማሪ አልተለቀቁም፣ ተለቀቁ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ከየት እንደመጣ አናውቅም። እንደውም አሁን ተማሪዎቹን ወደ ወለጋ እንደወሰዷቸው እየሰማን ነው"--- የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ወንጌላዊያን ህብረት

"አንዴ መረጃ ሰጥቻለሁ፣ እኔ ጋር ለምን ትደውላላችሁ?"--- የደባርቅ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር አስማማው ዘገዬ

Via EliasMeseret

@Merkato_media
ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከል ባለሃብቶችንና የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ይጎዳል በማለት እንደተቃወመ ሪፖርተር ዘግቧል።

ኮሚሽኑ ለትራንስፖርት ሚንስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ የሕግ ድንጋጌ ሳይኖርና ግልጽ ሕግ ሳይወጣለት ከበላይ አካል በተሰጠ ትዕዛዝ ብቻ ነዳጅ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ማገድ አግባብነት የለውም በማለት ቅሬታውን እንደገለጠ ዘገባው ጠቅሷል።

ውሳኔው፣ በግብርና፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር፣ በአበባ እርሻ ልማት፣ በቱሪዝም፣ በማኑፋክቸሪንግና ግንባታ በተሠማሩ ባለሃብቶች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጥሯል ተብሏል። ኮሚሽኑ፣ ላንዳንድ ኢንቨስትመንቶች ከባሕሪያቸው አንጻር በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዲያስገቡ እንዲፈቀድላቸው መጠየቁን ጋዜጣው አመልክቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ጥይት በፔርሙስ‼️
በፔርሙዝ ዉስጥ ተሸሽጎ ሊዘዋወር የነበረ የዲሽቃ ጥይት በቁጥጥር ስር ዋለ‼️
በቦረና ዞን ነገሌ ከተማ በፔርሙዝ ዉስጥ በመደበቅ ለማዘዋወር የተሞከረ የዲሽቃ ጥይት በቁጥጥር ስር መዋሉን የነገሌ ቦረና  ከተማ አስተዳደር  ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አስቻለዉ ቡልቻ ተናግረዋል።

ዋና ኢንስፔክተሩ ከነገሌ ከተማ ወደ አዶላ ዋዩ ሲጎዝ ነበረበ ኮድ 3 72685 ኦሮ የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ዶልፊን ተሽከርካሪ ላይ በተደረገ ፍተሻ በፔርሙዝ እና በጫማ ዉስጥ ተደብቆ ሊዘዋወር የተሞከረ የዲሽቃ ጥይት መያዙን ገልጸዋል።
ፖሊስ የጦር መሳሪያዉን ለማዘዋወር የሞከረዉን ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑንም  የነገሌ ቦረና  ከተማ አስተዳደር  ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አስቻለዉ ቡልቻ ተናግረዋል።

የኮንትሮባንድ እና የህገወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች በየጊዜዉ ስልታቸዉን እየቀያየሩ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸዉም ተመላክቷል።
#ብስራትሬዲዮ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ቡርኪናፋሶ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚከለክል ረቂቅ ህግ አወጣች!!

የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ ጁንታ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን የሚከለክልና በህግ ተጠያቂ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ አወጣ።

በኢብራሂም ትራወሬ የሚመራው የሚኒስትሮች ምክርቤት ሳምንታዊ ስብሰባውን ሲያደርግ በረቂቅ የቤተሰብ ህግ ላይ መክሯል።

በዚህም የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ ወደ ስራ እንዲገባ ወስኗል ነው የተባለው። የሀገሪቱ ጊዜያዊ የፍትህ ሚኒስትር ኢዳሶ ሮድሪክ ባያላ፥ “ከዛሬ ጀምሮ ግብረሰዶማዊነትና ተያያዥ ተግባራት የተከለከሉና በወንጀል የሚያስጠይቁ ናቸው” ማለታቸውንም ሬውተርስ ዘግቧል።

የሚኒስትሮች ምክርቤት ያጸደቀው ረቂቅ ህግ ወደ ስራ እንዲገባ በፓርላማ መጽደቅና የሀገሪቱ የሽግግር ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ትራወሬ ለህዝብ ይፋ ሊያደርጉት ይገባል።

የምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ከ2022 ጀምሮ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን በያዙ መሪዎች እየተመራች ነው።(አል ዐይን)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሄራዊ ባንክ ትናንት 19 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው የሰነዶች ጨረታ ማካሄዱን አስታውቋል።

16 ባንኮች በተካፈሉበትና ትርፍ ገንዘብ ከባንኮች ለመሰብሰብ ባለመው የሰነድ ጨረታ፣ የባንኩ ሰነዶች በ15 በመቶ የወለድ ተመን ተሽጠዋል።

ባንኩ፣ ከባንክ ገበያው ትርፍ ገንዘብ ለመሰብሰብ ወይም ተጨማሪ ገንዘብ ለመልቀቅ በወር ኹለት ጊዜ የገንዘብ ፖሊሲ ነክ ጨረታ እንደሚያካሂድ ያስታወቀው ማክሰኞ'ለት አዲስ የገንዘብ ፖሊሲ ባስተዋወቀበት ወቅት ነበር።

ባንኩ፣ በወለድ ላይ የተመሠረተ የገንዘብ ፖሊሲ መከተል ከጀመረ ወዲህ፣ በ15 በመቶ ወለድ የሰነዶች ጨረታ በማውጣት ትርፍ ገንዘብ ሲሰበስብ የትናንቱ የመጀመሪያው ነው።

@sheger_press
@sheger_press
Samsung  Galaxy  note  3
አዲስ  አንደታሸገ 
32  gb
3 gb ram
ዋጋ 4000  ብር በማከፋፈያ ዋጋ
Call me 👇👇👇👇
☎️ 0909255008
☎️ 0912739699
ተጨማሪ ስልኮችን  ለመመልከት
አና ስልክ ለመሽጥ ከፈለጉ 👇 ቤተሰብ ይውኑ
👉https://www.tg-me.com/used_phone_ethiopian
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ ሕገወጥ ተግባራት እየተበራከቱ በመሄዳቸው ጊዜያዊ አስተዳደሩን የሚፈታተኑና የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ወንጀሎችን ለማጣራት ኮሚቴዎችን በማቋቋም ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ለማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ ለማቅረብ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን ገልጧል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የክልሉ ፖሊስ በሕገወጥ የብረት ማዕድን ንግድና ሌሎች ሕገወጥ ድርጊቶችና ወንጀሎች የተሳተፉ ተጠርጣሪዎችንም በቁጥጥር ሥር ማዋል ጀምሬያለኹ ብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
"የአዲስ አበባ ሰሞነኛ ድምቀቶች" የሚል ፖስት ላይ መሬት ላይ ከተሰራው ፕሮጀክት ይልቅ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተፈበረከ ምስልን (ያውም ጎላ፣ ጎላ ባለ መልኩ) እንዲህ ማቅረቡ አስፈላጊነቱ ምንድን ነው?

ምናልባት ሀሳቡ "ወደፊት እንደዚህ ይሆናል" ወይም "ለመሆን እቅድ አለ" ከሆነም በደፈናው የAI ፎቶ ማስቀመጥ ሳይሆን እሱን በፅሁፉ ውስጥ በግልፅ ማስፈር ያስፈልጋል።

በባለስልጣናት፣ ውሳኔ ሰጪ አካላት፣ ፖለቲከኞች፣ የቢዝነስ ሰዎች... ወዘተ የሚጋሩ መረጃዎች ትክክለኛ የሆኑ፣ ወቅትን የጠበቁ እንዲሁም ሊያደርሱ የሚችሉትን spill over effeft ያገናዘቡ ሊሆን ይገባል... በተለይ መረጃ ለህዝብ ለማድረስ ተብለው የተቋቋሙ እንደ ኮሚኒኬሽን ሚኒስቴር ያሉ ተቋማት ይህን ሊተገብሩ ይገባል።

EliasMeseret

@sheger_press
@sheger_press
Merkato Media:
በአማራ ክልል ያሉ የአዉደ ዉጊያ ዉሎ መረጃዎችን እየተከታተለ ወደ እናንተ የሚያደርስ ቻናል ልጠቁማችሁ

👇👇👇
https://www.tg-me.com/SNN_merja
https://www.tg-me.com/SNN_merja
<<...መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን፣ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለሕዝባችን ደኅንነት እንዲሰጥልን ...ምሕላ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷ "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ

ሲኖዶሱ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ።


በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል።ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ለእግዚአብሔር ምልጃን ለማቅረብ ነው።


"ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ።

እግዚአብሔር  መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን፣;ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ ለቤተ ክርስቲያናችን ፍቅር አንድነት፣ ለሕዝባችን ደኅንነት እንዲሰጥልን ከአንድነት ገዳማት ኅብረት በቀረበው ጥያቄ መነሻነት ምሕላ ማወጅ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል " ብሏል።


በዚህም በመላ የሀገራችን ክፍልና ሌሎች አህጉራተ ዓለም የሚገኙ መነኰሳትና መነኰሳይያት ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ለሰባት ተከታታይ ቀናት በቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ ሃይማኖታዊና ቀኖናዊ ትውፊት መሠረት የገዳማት ኅብረቱን ጥሪ ተቀብለው የምሕላ ጸሎት እንዲያደርሱ ጥሪ አቅርቧል።

በጤና ችግር ምክንያት ካልሆነ በስተቀርም እስከ ዕርበተ ፀሐይ በመጾም ሱባኤ እንዲይዙ ፣ ቋሚ ሲኖዶስ ከአደራ ጋር አሳስቧል።


ከዚህ በተጨማሪ ሁሉም የቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና ምእመናን ሀገራዊ ሰላምን፣  መረጋጋትን እና ፍቅር አንድነትን ለማስፈን ጾምና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የሚያደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ መልዕክት ተላልፏል፡፡
በአማራ ክልል የሚገኙ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት ለማቋቋም ዓለም አቀፍ ተቋማት የተካተቱበት ኮሚቴ ተቋቋመ-

የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት አመራር ኮሚሽን፣ በኢትዮጵያ በመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮችን ቁጥር አስመልክቶ የተባበሩት መንግሥታቱ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ)፣ ከሰሞኑ ያወጣውን ሪፖርት መቃወሙን ዋዜማ ተረድታለች።
ጉድ በል ጎንደር

የፖርቹጋሉ ሉዊስ ናኒ እና ናይጄሪያዊው ንዋንክዎ ካኑ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብተዋል ።

ሁለቱ ታዋቂ የእግር ኳስ ተጫዋቾች ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የመቻል 80ኛ አመት የምስረታ በዓል ላይ ተካፋይ እንዲሆኑ በተደረገላቸው ግብዣ መሠረት መሆኑን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።
የፌደራል እና የሚመለከታቸው የክልል መንግስታት የግዛት ወሰናቸው ባሉባቸው አካባቢዎች የሚፈጸሙ የእገታና አፍኖ የመሰወር ድርጊቶችን እንዲያስቆሙ፣ የእገታና አፍኖ የመሰወር ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎችን በሕግ ተጠያቂ እንዲያደርጉ እና ለዜጎች ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርጉ ኢሰመጉ ጥሪ አቀረበ።

ኢሰመጉ በተለያዩ ጊዜያት በሚያወጣቸው አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫዎች በዜጎች ላይ የሚፈጸመው እገታና አፍኖ የመሰወር ተግባር በሀገራችን በአሳሳቢ ደረጃ እየተስፋፋ ያለ ጉዳይ መሆኑን እና በዚህም የተነሳ የሰዎች በሕይወት የመኖር መብት፣ የአካል ደህንነት መብት እና ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ መሆኑን በመረጃ በማስደገፍ በተደጋጋሚ መግለጫዎችን ማውጣቱን አስታውሷል።

ቢሆንም ግን የሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መንግስታት በግዛት ክልልቸው የሚፈጸመውን እገታ እና አስገድዶ መሰወር ለማስቆም በሚፈለገው ደረጃ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ባለማድረጋቸው ይህ ድርጊት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ማህበረሰቡን ለከፍተኛ ምሬት እና እንግልት እየዳረገው ይገኛል፡፡

የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ ቤተሰቦቻቸው በመመለስ ላይ እያሉ ገብረ ጉራቻ አካባቢ በታጠቁ አካላት የታገቱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ከታገቱ ተማሪዎችም መካከል የተወሰኑት ተማሪዎች የተጠየቀዉን መክፈል በመቻላቸውና በተለያዩ ምክንያቶች ከአጋቾች ማስለቀቅ መቻሉን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ የተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ በኢትዮጵያ በመጠለያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮችን ቁጥር በተመለከተ ከቀናት በፊት ያወጣውን ሪፖርት ተቃውሞታል።

ኮሚሽኑ፣ በመጠለያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች 3 ነጥብ 2 ሚሊዮን እንደኾኑ ለዋዜማ ተናግሯል።

ኮሚሽኑ፣ የቢሮው ሪፖርት "የቆየ እና በትክክለኛ ጥናት ላይ ያልተመሠረተ ነው" በማለት አጣጥሎታል።

የተመድ ቢሮ በሪፖርቱ፣ 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ተፈናቃዮች በመጠለያዎች እንደሚገኙ ገልጦ ነበር። ኮሚሽኑ፣ ከጥቂት ወራት በኋላ ሌላ ቆጠራ ሲደረግ የተፈናቃዮች ቁጥር መቀነሱ እንደማይቀርም ገልጧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በትግራይ የታጠቁ ኃይሎችና የውጭ ዜጎች ከሚሳተፉበት የወርቅ ሕገወጥ ቁፋሮና ኮንትሮባንድ ጋር በተያያዘ ከሚያዝያ ወዲህ ብቻ ከ20 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ በምርመራ ማረጋገጡን ሪፖርተር ዘግቧል።

በተለይ እንዳባጉና ወረዳ የሚገኘው የትግራይ ጀኔራሎች የሚቆጣጠሩት "ራህዋ" የወርቅ ማውጫ ከፍተኛ ሕገወጥ የወርቅ ቁፋሮና ኮንትሮባንድ እንደሚካሄድበትና ተዋናዮቹ የቀድሞ የሕወሃት ተዋጊዎች፣ ወጣቶች፣ ስደተኞችና ቻይናዊያን እንደኾኑ ዘገባው ጠቅሷል።

ዘገባው፣ በሰሜን ምዕራብ ትግራይ በ"ሒንጻት" የወርቅ ማውጫ ከኹለት ወራት በፊት በቀድሞ የሕወሃት ታጣቂዎችና በጥበቃዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት 22 ሰዎች እንደሞቱ መስማቱን ገልጧል።

ሕገወጡ ወርቅ ወደ አዲስ አበባ፣ አሥመራ፣ ሐርጌሳ፣ ናይሮቢ እና ካምፓላ እንደሚሸጥና ከዚያም መዳረሻው ዱባይ እንደኾነ ምንጮች ስለመናገራቸው በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።

@sheger_press
@sheger_press
2024/09/29 15:38:42
Back to Top
HTML Embed Code: