Telegram Web Link
በራያ አላማጣ ከተማ ዛሬ ለሊቱን በርካታ የህወሓት ታጣቂዎች ወደ ከተማዋ መግባታቸውን የአይን እማኞች ገልፀውልኛል።

በከተማ በሚገኙ ምስራቅ ፀሀይ፣ታዳጊዋና ሹሜ በርሄ ትምህርት ቤት ከሰፈረው ታጣቂ በተጨማሪ ምድረገነት ትምህርት ቤት ዛሬ ለሊቱን በርካታ ታጣቂዎች ገብተው ሰፍረዋል ብለዋል።

ትናንት የራያ ህዝብ በከተማዋ የሚገኙ የህወሓት ታጣቂዎች ከቀናት በፊት አንድ የመብራት ሀይል ሰራተኛ የነበረ ወጣትን በመግደላቸው ምክንያት ትናንት ህዝቡ በአደባባይ ወጥቶ ቅሬታውን ማሰማቱ አይዘነጋም። ዛሬ ለሊቱን ታጣቂዎች በተኮሱት ተኩስ አራት ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል ጉዳት አድርሰዋል ብለዋል።

በከተማዋ የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶች ታጣቂዎቹ ስለሰፈሩባቸው ትምህርት ከተዘጋ ወራቶች ሊቆጠሩ ነው ብለዋል(አዩዘሀበሻ)።
#ጋምቤላ‼️

በጋምቤላ ከተማ የታጣቂዎች ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ገለጹ!!

በጋምቤላ ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት ዐርብ፣ ታጣቂዎች በአንድ የመዝናኛ ክበብ ውስጥ በከፈቱት ተኩስ፣ ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸውን፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልም፣ የጥቃቱ ሰለባ የኾኑ ሰዎችን ተቀብሎ እያከመ መኾኑንና፣ ከመካከላቸው ከባድ ጉዳት የደረሰበት አንድ ሰው፣ ለተሻለ ሕክምና ወደ አዲስ አበባ ተልኳል፡፡

የክልላዊ መንግሥቱ፣ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ደግሞ፣ በጥቃቱ ዘጠኝ ሰዎች መቁሰላቸውን አረጋግጦ፣ ጥቃት ፈጻሚዎቹ ግን “እስከ አሁን አልተያዙም፤” ብሏል፡፡

@ethio_mereja_news
ኤርትራ በሌሊት ብቻ የሚሰራ የኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት መጀመሯ ተሰማ

👉🏼 የሙሉ ሌሊት ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች እስከ 105 ዶላር ድረስ መክፈል ይጠበቅባቸዋል ተብሏል


ኤርትረ በትናንትናው እለት የሌሊት ኢንተርኔት አገልግሎት መስጠት መጀመሯን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

ኤርትራ በሌሊት ብቻ ይሰጣል ባለችዉ የኢንተርኔት አገልግሎት እጅግ ዉድ ሊሰኝ እንደሚችል የኢንተርኔት እና የኮምፒውተር ባለሙያ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በሰከንድ 512 ኪሎ ባይት ድረስ አገልግሎት ይሰጣል የተባለዉ ኢንተርኔት በቤት ስልክ መስመር የሚመጣ ሲሆን ተጠቃሚዎች ወደ ሞባይል እና ኮምፒውተሮቻቸዉ ማገናኘት እና መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።

ኤርትራ በትናንትናው እለት ሌሊቱን ያስጀመረችዉ የኢንተርኔት አገልግሎት ባለሙያዎች ገለጻ ዘንድ ቀርፋፋ ነዉ የተሰኘዉን ነዉ።

ሁለት አይነት የኢንተርኔት ማስተላለፊያ መስመሮች ያሉ ሲሆን ኤዲኤስኤል (ADSL) በሲርናል ኢንተርኔት የሚደርስበት ሲሆን ቀርፋፋ የኢንተርኔት አገልግሎት የሚሰጥበትም ነዉ። በአንጻሩ በፋይበር የሚተላለፈዉ ኢንተርኔት በብርሃን አጋዥነት አገልግሎት የሚሰጥበት ሲሆን እጅግ ፈጣኑም እንደሆነ ባለሙያዉ ገልጸዋል።

ታድያ ኤርትራ አስጀመረችዉ የተባለዉ የኢንተርኔት አገልግሎት ኤዲኤስኤል (ADSL) የተሰኘዉን ነዉ። ይህ አሁንም በኢትዮጵያ አገልግሎት እየሰጠ ቢሆንም ቀርፋፋዉ አገልግሎት መሆኑን ባለሙያዉ ገልጸዋል።

ከሌሊቱ 4 ሰዓት እስከ ንጋት 12 ሰዓት ድረስ ከ 512 እስከ 1 ሜጋባይት ድረስ በሰከንድ ኢንተርኔት የሚያስጠቅነዉን አገልግሎት ለማግኘት ኤርትራውያን 1575 ናቅፋህ ወይንም 105 የአሜሪካ ዶላር መክፈል አለባቸው ተብሏል።

የተለያዩ አገልግሎቶች ይሰጣሉ የተባለ ሲሆን ተጠቃሚዎች እስከ 10 ጊጋ ባይት ድረስ የሆነና ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎትን ማግኘት ካሻቸዉ ደግሞ 4200 ናቅፋህ ወይንም 280 የአሜሪካ ዶላር ከፍያ መፈጸም እንዳለባቸው ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከተሰራጨው ማስታወቂያ ላይ መታዘብ ችሏል።

@ethio_mereja_news
መንግሥት በመጭው 2017 በጀት ዓመት 971 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር አጠቃላይ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል።

የቀጣዩ ዓመት በጀት ከዘንድሮው በጀት ጋር ሲነጳጸር የ21 ነጥብ 1 በመቶ ጭማሪ እንዳለው ገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሺዴ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል።

451 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር የሚኾነው በጀት ለመደበኛ በጀት 283 ነጥብ 2 ቢሊየን ለካፒታል እንዲኹም 236 ነጥብ 7 ቢሊየኑ ለክልሎች የበጀት ድጎማ እንደተያዘ ተገልጧል።

ለመደበኛ ወጪ ከተያዘው በጀት ውስጥ፣ 128 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ለመደወዝ፣ ለአበል እና
ለልዩ ልዩ ክፍያዎች እንደተመደበም አሕመድ አብራርተዋል።

@ethio_mereja_news
መንግሥት በቀጣዩ በጀት ዓመት ለአዲሶቹ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ለሲዳማ ክልሎች የሚመደብላቸው የፌደራል በጀት ድጎማ በቀድሞው የደቡብ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ክልል የፌደራል በጀት ድጎማ ቀመር መሠረት እንደሚቀጥል አስታውቋል።

የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ፣ አገሪቱ አዲስ የሕዝብ ቆጠራ እስክታካሂድ ድረስ የፌደራል በጀት ድጎማ ቀመሩ በነበረበት እንደሚቀጥል የቀጣዩን ዓመት በጀት አስመልክተው ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ተናግረዋል።

በተለይ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚገኙ በርካታ ዞኖች ዘንድሮ ገጥሞናል ባሉት የበጀት እጥረት ሳቢያ፣ ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ለመክፈል ተቸግረው እንደከረሙ ሲገልጡ ነበር።

@ethio_mereja_news
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በመጪው ሐምሌ ወር መጀመሪያ ይሰጣል

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በመጪው ሐምሌ ወር መጀመሪያ እንደሚሰጥ ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴርና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፈተናውን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ተፈራ ፈይሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ የዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ፈተና ከትግራይ ክልል ውጭ ባሉ አካባቢዎች ሐምሌ 3 ቀን 2016 ይጀመራል።

በዚህም መሠረት ከሐምሌ 3 እስከ 5 የሶሻል ሳይንስ ፈተና የሚሰጥ ሲሆን የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ደግሞ ከሐምሌ 9 እስከ 11/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ነው የገለፁት።

በትግራይ ክልል ደግሞ በሁለት ዙር ፈተናው የሚሰጥ ሲሆን ሐምሌ 2 ተጀምሮ ሐምሌ 12 እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ዲጂታላይዜሽንና የአይሲቲ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዘላለም አሠፋ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የዘንድሮው ዓመት የ12ኛ ክፍል ፈተና በኦንላይንና በወረቀት እንደሚሠጥ ተናግረዋል።

በዘንድሮው ዓመት 701ሺህ 489 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተናን እንደሚወስዱ ተገልጿል።

ትምህርታቸውን ዘግይተው የጀመሩና በተለያዩ ምክንያቶች በዚህ መርኃ ግብር መሰረተ ፈተና ላይ መቀመጥ ለማይችሉ ተማሪዎች ሁለተኛ ዙር ፈተና እንደሚዘጋጅም ጠቁመዋል።

@sheger_press
"ካለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የመገናኛ ዘዴዎችን መጥለፍ፣ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመመርመር የሚያስችል ረቂቅ ህግ ለፓርላማ ቀረበ‼️

በወንጀል የተገኘ ንብረትን ሕጋዊ ከማስመሰል ወይም ሽብርተኝነትን በገንዘብ ከመርዳት ወንጀል ጋር በተያያዘ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መገናኛዎችን እና ደብዳቤዎች ለመጥለፍ ለመርማሪዎች ፈቃድ የሚሰጥ ረቂቅ አዋጅ ለተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ።

አዲሱ ረቂቅ በሥራ ላይ ያለውን በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ የሚሽር ነው።

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ መርማሪ አካል “አስቸኳይ ሁኔታ ካጋጠመው” የሚመለከተውን የዐቃቤ ሕግ ተቋም የበላይ ኃላፊ በማስፈቀድ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የመገናኛ እና የደብዳቤ ልውውጦችን መጥለፍ ይችላል።

መገናኛዎችን እና የደብዳቤ ልውውጦችን መጥለፍ ከወንጀሎቹ ጋር በተያያዘ ተግባራዊ ከሚደረጉ የምርመራ ዘዴዎች መካከል ናቸው።

በባንክ ሂሳቦች እና በሌሎች ተመሳሳይ ሂሳቦች ላይ ክትትል ማድረግ፣ የኮምፒውተር ሥርዓቶችን፣ መረቦችን ሰርቨሮችን መለየትም በተመሳሳይ ሌሎች የምርመራ ዘዴዎች ናቸው።

ከዚህ በተጨማሪም በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራም (undercover operation) በተመሳሳይ በአዋጁ የተጠቀሰ የምርመራ ዘዴ ነው::

@ethio_mereja_news
ህወሃት ይቅርታ ጠየቀ

ህወሃት ከጦርነቱ ቀደም ብሎ በ2013 ዓ.ም ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ውጪ ያካሄደው ህገወጥ ምርጫ ስህተት መሆኑን በማመን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የይቅርታ ደብዳቤ መፃፉን የውስጥ ምንጮች ገልፀዋል።

ህወሀት በምርጫ ቦርድ የፓርቲነት ህጋዊ ሰውነቱ ተነስቶ እንደነበር ይታወቃል።
ባለፈው ሳምንት ህወሃት ወደ ህጋዊ ፓርቲ ሊመለስ የሚችልበት ህግ በህዝብ ተወካዮች ምክር መፅደቁን ተከትሎ በዚህ ውሳኔ ህወሃት ደስተኛ መሆኑን መግለፁ አይዘነጋም።

አሁን ላይ ህወሃት ህጋዊ ፓርቲ ሆኖ በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለመመዝገብ መደላድል ስለተፈጠረ ከዚህ ቀደም በ2013 ዓ.ም በትግራይ ያካሄደው ህገወጥ ምርጫ ድርጅቱ በወቅቱ ያካሄደው ምርጫ ስህተት መሆኑን በማመኑ ሰሞኑን ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የይቅርታ ደብዳቤ እንዳስገባ የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።(ayu)

@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል አመት በሞላው ግጭት በተለይ ትምህርት ስራ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ  አሳድሯል።

ዛሬ የሰሜን ሸዋ ዞን እንዳስታወቀው በ9 ወረዳዎች የሚገኙ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ለፈተና አልተቀመጡም።ማስፈተን የተቻለው በ14 ወረዳዎች ብቻ ማስፈተን እንደተቻለ ዞኑ አሳውቋል።

ከምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ በተገኘ መረጃ መሰረት ዘንድሮ በዞኑ ከሚገኙ 996 አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 32ቱ ብቻ ክፍት ሆነው ተማሪዎቻቸው የተቀበሉት።

ት/ቤት መገኘት ከነበረባቸው 539,000 የሚሆኑ ተማሪዎች 13,000 ብቻ ናቸው እየማሩ የሚገኙት ብሏል ።

በዞኑ 593 ት/ቤቶች 38,203 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ፈተና እንደሚወስዱ ቢታቀድም በ10 ት/ቤቶች  431 ተማሪዎች ብቻ ናቸው ፈተና የወሰዱት።

ከ407 በላይ ት/ቤቶች እንዲወድሙና ለመማር ማስተማር አገልግሎት እንዳይሰጡ ሆነዋል።

ከ290.3 ሚሊዮን በላይ የት/ቤቶች ሀብትና ንብረት ወድሟል።

ከርቀት ሆኖ ሲታይ ለሌሎች ቀላል መስሎ የታየው የአማራ ክልል ግጭት በመቶ ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት እና በቢሊየን ለሚቆጠር ሀብት ውድመት ምክንያት ሆኗል።አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች እንደቀጠለ ነው።የፈጠነ የንግግር መፍትሄ ቢወሰድ መልካም ነው።(wasu mohammed)

@sheger_press
@sheger_press
የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች የተለያዩ የኦንላይ ስራዎች መስራት ከፈለጋቹ በሸገር አድሚኖች የተከፈተው ቻናል አሁንኑ ይቀላቀሉ 👇👇

በርግጠኝነት ታተርፉበታለቹ👇👇

http://www.tg-me.com/sheger_crypto
እንቁላል ጣይ ዶሮ የሰረቀው ታዳጊ የ1 አመት ከ8 ወር እስር ተቀጣ

በምእራብ ጉጂ ዞን ሀምባላ ወረዳ ቢምቱ ከተማ  02 ቀበሌ ውስጥ አንድ ዶሮ ሲሰርቅ የተያዘው ግለሰብ ላይ የእስራት ቅጣት መወሰኑን የሀምባላ ፖሊስ አስታወቀ።

የሀምባላ ወረዳ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል እንደገለፀው ተከሳሽ ሮቤል ሽብሩ የተባለው የ18 አመት ታዳጊ ወጣት ሰኔ 3 ቀን 2016አ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ የአንድ ግለሰብን እንቁላል የምትጥል ዶሮ ሰርቆ በመውሰድ ሲሮጥ እጅ ከፍንጅ መያዙ ተገልጿል።

ግለሰቡ በፖሊስ የምርመራ መዝገብ በአስቸኳይ የተጣራበት ሲሆን የምርመራዉም መዝገብ ለአቃቢ ህግ ተልኳል።

አቃቢ ህግም ወድያውኑ ክስ መስርቶበት በአስቸኳይ ችሎት ውሳኔ እንዲሰጠው በመጠየቁ እንቁላል ጣይ ዶሮ የሰረቀው ታዳጊ ሮቤል ሽብሩ ሙሉ ለሙሉ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ1 አመት ከ8 ወር እስራት እንዲቀጣ  የሀምባላ ወረዳ ፍርድ ቤት ውሳኔ ማስተላለፉን የሀምባላ ወረዳ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን የላከው መረጃ ያመላክታል።

#ዳጉ_ጆርናል

@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ከ1 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸው ተገለፀ!

የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት እንዳስታወቀው በክልሉ ባለፉት 11 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ ተጠቅተዋል።የክልሉ ጤና ቢሮና የከተማ አስተዳደሩ ጤና መምሪያ ኃላፊዎችም በበኩላቸው በክልሉ የወባ በሽታ በከፋ ሁኔታ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ገልፀዋል።የክልሉ ጤና ተቋማት ኃላፊዎች እንደገለፁት በክልሉ ያለው ግጭት ሳቢያ በተደጋጋሚ የመንገዶች መዘጋጋት የወባ ሥራ ቁጥጥርን አዳክሞታል።የመድኃኒት ስርጭትን ደግሞ አስተጓጉሎታል።ይህም ችግሩ እንዲባባስ አድርጓል።ህብረተሰቡ ወባን ለመከላከል ያለው ዝቅተናኛ ግንዛቤና ቸልተኝነት ደግሞ ሌላው ምክንያት ነው ሲሉ ሀላፊዎቹ ገልፀዋል።

የክልሉ መዲና የባህርዳር ነዋሪዎች በበኩላቸው በከተማው የወባ ስርጭት መበራከቱን ይገልጻሉ።የባህር ዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት መለአከ ብርሐን ፍሰሐ ጥላሁን «አሁን በባሕር ዳር ወባ ከቤቴ ጀምሮ አለ፣ ህፃናት እየታመሙ ነው፣ ባሕር ዳር ውስጥ ግንቦት ወር የወባ መነሻ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ፣ ለህክምና ሰዎች ወደ ጤና ተቋም ሲሄዱ ወባ እየተገኘባቸው ነው፡፡» ብለዋል፡፡የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪ ኃላፊ ወ/ሮ ዓለም አሰፋ ሰሞኑን ለዶቼ ቬሌ እንደተናገሩት ህብረተሰቡ ያለው የትንኝ መከላከያ የአልጋ አጎበር አጠቃቀም ዝቅተኛ በመሆኑና ሌሎች የመከላከል ስራዎችን ቸል በማለቱ በሽታው በብዛት በከተማዋ መታየቱን አስረድተዋል፡፡ባለፈው ሳምንት 7ሺህ ሰዎች የወባ ምርመራ አድርገው በ2ሺህ 460 ሰዎች ላይ በሽታው ተገኝቷል ብለዋል፡፡

[DW]
Hamster‼️

Hamster ለምሰሩ የዕለቱ 5 million coin ያልወሰዳቹ

በዚ Link ተለቆል መመልከት ትችላላቹ👇👇

https://www.tg-me.com/sheger_crypto/231
ፓስፖርት እናስወጣላችኋለን እያሉ ግለሰቦችን ሲያጭበረብሩ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ‼️

ፓስፖርት እናስወጣላችኋለን እያሉ ግለሰቦችን ሲያጭበረብሩ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋሉ። 
 
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ሊውሉ የቻሉት በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ልዩ ቦታ ኢሚግሬሽን አካባቢ ለግለሰቦች ፓስፖርት እናስወጣለን በማለት ሲያጭበረብሩ እንደነበረ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል። 
 
ነዋሪነታቸው አዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 የሆኑት አስራት አጎን አይዛ እና ስንታየሁ ለይኩን ኃይሌ የተባሉ ግለሰቦች የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ኢንተለጀንስ ዋና መምሪያ አባላት ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሠራተኞች በደረሰው ጥቆማ መሠረት ባደረጉት ክትትል ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እየጣራባቸው ይገኛል። 
 
ኅብረተሰቡ ከመሰል ወንጀሎች ራሱን በመጠበቅ አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሲመለከት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት በጀመረው በዜጎች መረጃ መቀበያ (EFPAPP) ወይም በነፃ የስልክ መስመር 991 በመጠቀም ለፖሊስ መረጃ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@ethio_mereja_news
ኢትዮጵያ ምንም አይነት “የአቪዬሽን ደህንነት ስጋት የሌለባት ሀገር” ናት ሲል የዓለም አቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ኦዲተሮች ማረጋገጫ ሰጥቷል ተባለ

የዓለም አቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ኦዲተሮች ባለፉት 10 ቀናት የአቪዬሽን ኢንዱስትሪውን ደህንነት መፈተሻቸውን የገለጹት በብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት የሲቪል አቪዬሽን ደህንነት መምሪያ ዳይሬክተር አስራት ቀጀላ ፍተሻው የተከናወነው ከግንቦት 26 እስከ ሰኔ 6 መሆኑን አስታውቀዋል።

በቦሌ ኤርፖርት እና በሌሎች አየር ማረፊያዎች በተደረገው ኦዲት ኢትዮጵያ ምንም አይነት የአቪዬሽን ደህንነት ስጋት የሌለባት መሆኑን የድርጅቱ ገምጋሚዎች መገልፃቸውን ዳይሬክተሩ የፍተሻውን መጠናቀቅ አስመልክተው በሰጡት መግለጫ አመላክተዋል።

እንዲስተካከሉ አስተያየት የተሰጠባቸውን የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያ እና ሌሎች ጉዳዮች በፍጥነት እንደሚስተካከሉም ጠቁመዋል።

ከሲቪል አቪዬሽን ደህንነት አንፃር በድርጅቱ መስፈርት መሰረት በቁጥር የተሟላ የኦዲቱ ሪፖርት በቅርቡ አዘጋጅተው እንደሚያስረክቡ ተጠቅሷል።

ይህ የኦዲት ውጤት በዘርፉ ለመሰማራት ለሚፈልጉ አካላት ወደ ስራ እንዲገቡ፣ ለሀገሪቱ የቱሪዝም እና የአቪዬሽን ዘርፍ እድገት አስተዋፅኦው የላቀ ነው ተብሏል። ለዚህ ውጤት መገኘት በዘርፉ በቅንጅት የሚሰሩት የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የብሔራዊ መረጃ ደኅንነት አገልግሎት፣ ፌደራል ፖሊስ ፣ ጉሙሩክን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሚና ትልቅ እንደነበርም በመግለጫው ተጠቅሷል።

@ethio_mereja_news
ተፈቶል‼️

ለረጅም ወራቶች በእስር ላይ የነበረው ገጣማ በላይ በቀለ ወያ ተፈቷል።

እንኳን ለቤትህ አበቃህ ወንድማችን 🙏

@sheger_press
#Notcoin

❤️Telegram wallet verify ማድረግ ያልቻላችሁ ወይም tonkeeper ላይ notcoin ያላችሁ መሸጥ የምትፈልጉ

😄 በዚህ አናግሩን 👉 @Birukepromo

❤️ልብ ይበሉ

በእነዚህ user name መጥታችሁ ስትገበያዩ ገንዘባችሁ 100% ይሰጣችኋል (ሀላፊነቱን @sheger_press ይወስዳል)

ክፍያው እንደ ስምምነታችሁ ይፈፀማል

በእነዚህ ሰዎች ለመገበያየት ስትሄዱ ያላችሁ ስክሪንሽት አድርጋችሁ ማሳየት ግድ ነው

ton space ቤታ ከሆነ ኮይናችሁ ደግሞ 0.2 ክፍያ ስለሚጠይቅ ቶን ኮይን ከሌላችሁ ቅድሚያ ከፍላችሁ መውሰድ

notcoinu ልካችሁ ስትጨርሱ አድሚኑ በተስማማቹበት ዋጋ ብራችሁ መልሶ ያስገባል!!


🚫ለማጭበርበር የምትመጡ ካላችሁ ወዲያው Block ሰለምናረጋችሁ አትልፉ እንዳመጡ!!

ሲቀጥል የማትሸጡ አትምጡ ጊዜያችን አታቃጥሉ

ለተለያዩ ONLINE ስራዎች ለመስራት ይህን ቻናል ይቀላቀሉ👇👇
https://www.tg-me.com/sheger_crypto
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ህውሀት‼️

ህውሃት ዛሬ ባወጣው ግለጫ እኔ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድን ይቅርታ አልጠየኩም።በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጨው ስህተት ነው ሲል ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ህውሃት ሁለት ክንፍ አለው አንዱ የተሳሳተ መረጃን የሚሰጥና የሚያሳስት ቡድን ሌላኛው የተሰጠውን የተሳሳተ መረጃ የሚያርም እንደሆነ እየተሰማ ነው።

ከዚህ የሚያተርፈው ሁሌ ስሙን ከሚዲያው ላለማጥፋት የሚያደርገው አንዱ ስልት መሆኑ ብዙዎች እየገለፁት ነው።

ለአብነትም ከሰሞኑ ከፓርቲው መከፋፈል ጋር በተገናኘ የሰጠው መግለጫ ተጠቃሽ ሆኖ ቀርቧል።

ሌሎችም በርከት ያሉ ጉዳዮች እየተነሱ ነው።(wasu)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አዲስ ታሪፍ‼️

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን፣ አዲስ የተዘጋጀ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማሻሻያ ረቂቅ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ለሚንስትሮች ምክር ቤት እንደሚያቀርብ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል።

ባለሥልጣኑ፣ የሃይል አቅራቢ ተቋማት ባቀረቡት የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማሻሻያ ጥናት ላይ የቅድመ ግምገማ ሂደቱን አጠናቆ፣ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት ግብዓቶችን እያሰባሰበ መኾኑን ገልጧል።

የታሪፍ ማሻሻያውን አዘጋጅተው ያቀረቡት፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ናቸው።(wazema)

@ethio_mereja_news
2024/09/29 21:32:16
Back to Top
HTML Embed Code: