Telegram Web Link
አቶ የሽዋስ አሰፋ መታሰራቸው ተሰምቷል‼️

በአንድ ወቅት ሰማያዊ ፓርቲን አፍርሰው ወደ ኢዜማ ሲቀላቀሉ "ከትንንሽ ፓርቲ መሪነት ይልቅ የትልቅ ፓርቲ አባል መሆን ይሻላል" በሚል ንግግራቸው ስማቸው ጎልቶ የሚነሳው የሽዋስ አሰፋ ትናንት ግንቦት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት አንድ ሰዓት ካዛንቺስ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ ተይዘው እንደተወሰዱ ከቤተሰቦቻቸው ተሰምቷል።

አሁን ላይ ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንዲመገኙ ለማወቅ ተችሏል።ለእስር ያበቃቸው ጉዳይ በግልፅ አልታወቀም።

@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

Online ስራ መስራት ከፈለጉ ሸገር Crypto ቻናልንን ይቀላቀሉ።

በርግጠኝነት ይወዱታል👇

JOin 👉 https://www.tg-me.com/sheger_crypto
አመራሩ ተገደሉ‼️

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የኤፍራታና ግድም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ አልብስ አደፍራሽ በቀን 24/9/2016 ዓ.ም ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በቤታቸው እያሉ በተተኮሰባቸው ጥይት ህይወታቸው ማለፉን ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘሁት መረጃ ያመላክታል(አዩዘበሀሻ)።
ነፍስ ይማር

@sheger_press
@sheger_press
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዝደንት ኢሳያስ በደቡብ ኮሪያ ዋና ከተማ ሴኡል ይገኛሉ‼️

ሁለቱ መሪዎች በደቡብ ኮሪያ የአፍሪካ  የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ደቡብ ኮሪያ ሴኡል ይገኛሉ።

ኢሳያስ አፈውርቂ ትናንት ወደ ሴኡል ያቀኑ ሲሆን ጠ/ሚ አብይ አህመድ ዛሬ ጠዋት ደቡብ ኮሪያ ሴኡል መድረሳቸው ታውቋል። በደቡብ ኮሪያ የሚካሄደው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ነገ ይጀመራል።

@ethio_mereja_news
" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ረቂቁ ከባለፈው መጠነኛ ማሻሻያዎች ተደርጎበት መቅረቡን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

በመጀመሪያው ረቂቅ አዋጅ ያልነበረና የመንግሥትንና የክልሎችን ግዴታና ኃላፊነት በመዘርዘር የተቀመጠው ክፍል አንዱ ነው።

በዚህ ክፍል ላይ መንግሥት በሃይማኖት አስተምህሮና የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንደማይችል ተደንግጓል፡፡

በተጨማሪ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት ተደንግጎ የነበረው የረቂቅ አዋጁ ክፍል ከተሻሻለው ረቂቅ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

ነገር ግን ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ፦

የሃይማኖት ተቋሙን ኦዲት ሪፖርት ለሰላም ሚኒስቴር እንዲያቀርብ፣

የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ #በ3_ወራት የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር እንደሚኖርበት የተቀመጠው የረቂቁ ክፍል በተሻሻለው ላይ #ተካቷል፡፡

ሌላኛው ተሻሽሎ የቀረበው የረቂቅ ክፍል አለባበስን እና የተማሪዎች አመጋገብን ጨምሮ በማንኛውም የትምህርት ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚደረግ ሃይማኖታዊ ተግባር የመንግሥትና ሃይማኖት መለያየት መርህንና የሃይማኖት ነፃነትንም በጠበቀ መንገድ መከናወን አለበት የሚለው ነው፡፡


የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረኩ የመጨረሻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በመንግሥት እና በሃይማኖት መካከል ያለው ልዩነት ምን ድረስ እንደሆነ ሳይታወቅ ቆይቷል ብለዋል።

አዋጁን ማዘጋጀትም ያስፈለገው ይህን ጉዳይ በግልጽ ለማስቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

(Reporter Newspaper)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በምስራቅ ሃረርጌ ዞን ከእድሜ እኩያው ጋር በተፈጠረ ፀብ የግድያ ወንጀል የፈፀመዉ ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን በደኖ ወረዳ ጎሮ ቀበሌ ውስጥ ከእድሜ እኩያው ጋር በተፈጠረ ፀብ ቅራኔ ውስጥ ገብቶ የተጣላውን ልጅ አባት በመግደል የተከሰሰ ግለሰብ በፅኑ እስራት መቀጣቱን የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታውቋል ።

የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ሃላፊ አ/ቶ  ሳሊም ሙክታር ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ተከሳሽ አልኸዲን ሃማዝ የእድሜ እኩያውን ወላጅ አባት ላይ የግድያ ወንጀል መፈፀሙን ገልፀዋል ።ተከሰሹ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ የተጣላውን የእድሜ እኩያውን ለማጥቃት ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲሄድ በማጣቱ በያዘው ስለታማ መሣሪያ አ/ቶ ሙሃመድ አብዱልመጅድ ጭንቅላታቸውን በመምታት ከፍተኛ ጥቃት አድርሶባቸዋል ።

ተከሳሹ በወቅቱ ጉዳቱን በማድረስ ተሰውሮ የነበረ ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው አ/ቶ ሙሃመድ በአካባቢው ማህበረሰብ ትብብር ህክምና ቢያገኙም ህይወታቸው ማለፉ ተጠቁሟል ። ፖሊስ በበኩሉ ተጠርጣሪውን ክትትል በማድረግ በቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በህክምና ማስረጃ በማጠናከር ለዓቃቤ ህግ ይልካል ።

ዓቃቤ ህግም የደረሰውን የምርመራ መዝገብ ተንተርሶ በተከሳሹ ላይ ክስ መስርቶበታል ። ዓቃቤ ህግ የመሠረተውን ክስ ሲመለከት የቆየው የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ ሲል ብይን ሰጥቷል ። 

ፍርድ ቤቱ ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎችም ያስጠነቅቃል በማለት ተከሳሽ አልኸዲን ሃማዝ በ15 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል ።

@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

Hamster‼️

Guys ይህ ትልቅ ብር ማግኛ ኤርድሮፕ ነው እየተባለ ይገኛል

በርግጠኝነት እንገራቹ ይህ List መሆኑ አይቀሬ ነው ።

አሁንኑ በመጀመር ታፕ ታፕ አድርጉ

ያልጀመራቹ ጊዜው ሳይረፍድ  አሁንኑ በዚ ሊንክ ጀምሩት👇

ለመጀመር👇👇
https://www.tg-me.com/hamsTer_kombat_bot/start?startapp=kentId1204288009


አጨዋወቱን ለከበዳቹ ዝርዝሩን በዚ ቻናል ያገኙታል👇👇
https://www.tg-me.com/sheger_crypto
"እባካችሁ ወጣቶች አትቀመጡ፣ስራ ለመፍጠር ሞክሩ፣እኛ ነፃ ስልጠናና ሌሎች እገዛዎችን እናደርጋለን"EDI

ኢዲአይ ከሰሞኑ ከወዳጆቼ ጋር ለትውውቅና አጭር ስልጠና ጋብዞንን ነበር። በቅድሚ ትውልድን ወደ ስራ ፈጣሪነት ለማስገባት የተቋቋመ በመሆኑ ለተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ትልቅ አክብሮት አለኝ።

የኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሺፕ ኢንስትቲዩት(EDI) ይባላል።ከፊል-ራስ-ገዝ የምርምር አስተሳሰብ በኢኮኖሚ ጥናት እና የፖሊሲ ትንተና ፣ ምርምር እና ፖሊሲ ማጠናቀር ፣ አቅም መፍጠር፣ የእውቀት ሽግግር እንዲካሄድ በስራ ፈጠራ ላይ የሚያሰለጥን እና የሚያማክር ተቋም ነው።

በኢትዮጵያ የሚዲያ ኢንድስትሪ ውስጥ ለሚመጣው አዲስ የኢንተርፕርኒያል ሚዲያ አስተሳሰብ የድርሻውን ለመወጣት ነበር ያሰባሰበን።የሚዲያ አንቀሳቃሾቹ በኢኮሲስተም ውስጥ ዋና ተዋናይ መሆን እንዲችሉ ባላቸው ላይ ጥሩ ግንዛቤን ያስጨበጠ ቆይታ ነበር።
"እባካችሁ ወጣቶች አትቀመጡ፣ስራ ለመፍጠር ሞክሩ፣እኛ ነፃ ስልጠናና ሌሎች እገዛዎችን እናደርጋለን" ከተቋሚ የስራ ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ሲነገር የነበረ ሃሳብ ነው።የEDI ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀሰንን ጨምሮ አሰልጣኞችና አስተባባሪዎች እነ ዳኒ ትውልድ ላይ እየሰራችሁት ያለው መልካም ስራ ለሌሎችም ምሳሌ ነውና በርቱልን።(wasumohammed)

@ethio_mereja_news
መረጃ‼️

እስክንድር ነጋ ከመንግስት ሰዎች የሰላም ድርድር ሂደት መጀመሩ ታውቋል

እስክንድር ነጋ የፋኖ ታጣቂዎችን ወክሎ ከመንግስት ድርድር መጀመሩ ተገልጿል። በ3ኛ ወገን አመቻችነት እስክንድር ነጋ ከመንግስት ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ያልሆነ የድርድር ሂደት መጀመሩ ተጠቁሟል።

መንግስት ከእስክንድር ጋር እያደረገ ያለው ድርድር የሚሳከ ከሆነ ከእስክንድር ቡድን ጋር ከሸዋ የሻለቃ መከታው ቡድን፣ ከወሎ የምሬ ወዳጆ እና የኮ/ል ፈንታሁን ቡድኖች፣ ከጎጃም የማስረሻ ሰጤ እና የማንችሎት ቡድኖች፤ ከጎንደር በሻለቃ ሀብተ ወልድ የሚመራ ቡድን ወደ በድርድርሩ እንዲሳቱፉ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።

ከሰላም ውጪ ሌላ አማራጭ መንገድ የለም! ሰላም ለኢትዮጵያ(natnael)

@ethio_mereja_news
ጎንደር

ሚያዚያ 4/2016 ዓም ከረፋዱ 5:00 አካባቢ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ ጀርባ ከፀጥታ አካላት ጋር በነበረ የተኩስ ልውውጥ ህይወታቸው ያለፈው 2 የፋኖ አባላት ዛሬ በጎንደር ቤተሰቦች አስከሬናቸውን ሳያገኙ ፍትሃትና ባህላዊ የሽኝት ሥነ ሥርዓት አካሂደዋል።።

ናሁሰናይ አንዳርጌ እና አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጥ ከተገደሉ በኃላ ወላጆቻቸው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት አስከሬናቸውን አግኝተው ቀብር ለመፈጸም ፌደራል ፖሊስ ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ድረስ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ ሳያገኙ 2 ወር ለሚጠጋ ጊዜ መጠበቃቸውን እና በመጨረሻም ተስፋ መቁረጣቸውን ተናግረዋል።

ዛሬ ግንቦት 26 ቀን 2016 ዓ.ም. ጎንደር ውስጥ የናሁሰናይ አንዳርጌ አስከሬኑ በሌለበት በባህላዊ መንገድ በቤተሰብና በወዳጆች ፍትሃቱና የሽኝት ሥነ ሥርዓቱ በአባ ጃሌ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

አንድ የቤተሰብ አባል ደግሞ " ለቀስተኛው ካለ አስከሬን በተካሄደው የስንብት ሥነ ሥርዓት ላይ ለመታደም ወደ ቤተ-ክርስቲያን እያመራ ሳለ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች የናሁሰናይ ፎቶ እና ስም ያለበትን 2 ባነር በኃይል ተቀብለዋል። ከዚህ ውጭ ምንም የተፈጠረ ነገር የለም " ብለዋል።

የአቤኔዘር ጋሻው የሽኝት በተመሳሳይ ቤተሰቡ አስከሬኑ ባላገኘበት ሁኔታ ቀደም ብሎ መከናወኑን የቤተሰቡ አባላት ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ አማርኛ አስነብቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሪያል ማድሪድ ደጋፊዎችን በማጓጓዝ የታሪክ አካል በመሆናችን ተደስተናል አለ

"ዓለምን በአንድ ቋንቋ የሚያግባባው እግር ኳስ ከነገሰበት የአውሮፓ ክለቦች ሻምፒዮና መንደር ተገኝተናል። ትልቁን ዋንጫ ለ15ኛ ጊዜ በማሸነፍ ድልን የተጎናጸፈው የሪያል ማድሪድ ክለብ ደጋፊዎች ምርጫ በመሆን ደጋፊዎቹን ከማድሪድ ወደ እግር ኳሱ ድግስ እንግሊዝ ምድር በማጓጓዝ የዚህ ታሪክ አካል በመሆናችን ደስ ይለናል።
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሀገር ውስጥ እና በዓለም እየሰጠ ከሚገኘው መደበኛ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት በተጨማሪ የቻርተር በረራዎችን በመስጠት ተመራጭ አየር መንገድ መሆኑን በማስመስከር ላይ ይገኛል።" ሲል የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።
ethiopianairlines

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መንግስት ከ 2 ሚሊዮን በላይ አሽከርካሪዎችን በተለያዩ ምክኒያቶች ቀጥቶ ከ 1.1 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘ

የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የ 9 ወራት የስራ የስራ እና እቅድ አፈጻጸሙን ባቀረበበት በዛሬው ም/ቤት ጉባዔ ላይ በወራቱ 2 ሚሊዮን 17 ሺህ 930 አሽከርካሪዎች በተለያዩ ምክንያቶች መቀጣታቸውን የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር አለሙ ስሜ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ በሪፖርታቸዉ ከተቀጡ አሽከርካሪዎች 1 ቢሊዮን 129 ሚሊዮን 544 ሺህ 187 ብር መንግስት ገቢ አግኝቷል ማለታቸውን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

በወራቱ በሀገር አቀፍ ደረጃም በድግግሞሽ 9 ሚሊዮን 854 ሺህ 902 ተሽከርካሪዎች ላይ የቴክኒክ ቁጥጥር መደረጉንም ገልጸዋል። በተጨማሪም ከ 103 ሺህ በላይ በሆኑት አሽከርካሪዎች ላይም ድንገተኛ የአልኮል ፍተሻ ተደርጓል ብለዋል።

በተጨማሪም ባልታወቁ እና የሶስተኛ ወገን በሌላቸዉ አሽከርካሪዎች በደረሱ የትራፊክ አደጋዎች ለተጎዱ ሰዎች ሙሉ በሙሉ የካሳ ክፍያ ማግኘታቸውንም የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትሩ ዶ/ር አለሙ ስሜ መናገራቸውን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

@ethio_mereja_news
በአዲስ አበባ ከተማ የአከራይ እና ተከራይ ህጋዊ ውል ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚጀመር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል።

የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ መጽደቁ ይታወቃል፡፡

በዚህም አስተዳደሩ አዋጁን በመመሪያ በማስደገፍ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅቶቹን ማጠናቀቁ ተገልጿል።

ከሰኔ 1 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የግል ቤት አከራዮች ከተከራዮቻቸው ጋር ህጋዊ ሰነዶቻቸውን ይዘው በመቅረብ ምዝገባ ማድረግ ይችላሉ ተብሏል።

ቤት አከራዮች ፦

➡️ ህጋዊ የምዝገባ ውል ለመፈጸም ወደ ወረዳ ጽ/ቤቶች በሚሄዱበት ወቅት ቤቱ የራሳቸው ስለመሆኑ ወይንም ህጋዊ ተወካይ መሆናቸውን የሚገልጽ ሰነድ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።

ተከራዮች ፦

➡️ ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ወይም ሌላ ህጋዊ ማንነታቸውን የሚያረጋግጥ ሰነድ ይዘው መቅረብ አለባቸው።

በስራ ሰዓት መመዘግብ የማይችሉ አከራይና ተከራዮች ቅዳሜና እሁድ እንዲሁም በስራ ቀን ማታ ከ12 ሰዓት በኋላ ህጋዊ የውል ምዝገባውን መፈጸም ይችላሉ።

Source: tikvahethiopia

@ethio_mereja_news
አዲስ አበባ😭

በፌስቡክ ስሙ አቤነዘር ይባላል በትክክለኛ ስሙ አቤል ሲሆን ሰሞኑን አዲስ አበባ በ22 አካባቢ በመኪና ታገዘ ዝርፊያ ሰለባ ሆኖ ነበር። ሞባይሉ ነጥቀው ሲሮጡ እሱም ሲከተል በመኪና ገጭተው ጥለውት አመለጡ።በሀኪም ሲረዳ ቆይቶ ህይወቱ አለፈ።ያሳዝናል።ሞባይል ነጥቀውና በትንሽ ገንዘብ ሞባይል የሚሸጡ እንዲሁም በየአካባቢው የተሰሩቁ ሞባይል የሚገዙ የሌባ ተባባሪዎችን ለህግ ማቅረብ ይገባል።ለአቤል ቤተሰብ መፅናናቱን ይስጥል።(wasumohammed)

@sheger_press
ኢሰመኮ፣ በአማራ ክልል ታውጆ ከነበረው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር በተያያዘ መንግሥት አስሮ ያቆያቸውን ሰዎች የመልቀቁን ሂደት እንዲቀጥል ዛሬ ባወጣው አጭር መግለጫ አሳስቧል።

ኢሰመኮ፣ "ወደ መደበኛው የሕግ አተገባበር ሂደት መመለስ"፣ በአዋጁ በአንዳንድ የክልል አካባቢዎች ተጣሉ "የእንቅስቃሴ ገደቦች እንዲነሱ" እና "ማኅበረሰባዊ አገልግሎቶች" ወደነበሩበት እንዲመለሱ ጠይቋል።

ኢሰመኮ ይህንኑ ጥሪውን ያስተላለፈው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ጥር 24 ለአራት ወራት ያራዘመው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የቆይታ ጊዜ ግንቦት 24 ቀን መጠናቀቁን ተከትሎ ነው።

@ethio_mereja_news
2024/09/28 23:17:50
Back to Top
HTML Embed Code: