Telegram Web Link
አቡነ ሉቃስ በተከሰሱበት የቅስቀሳ ወንጀል በ6 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነ

አቡነ ሉቃስ በተከሰሱበት የቅስቀሳ ወንጀል ጥፋተኛ በተባሉበት ድንጋጌ በሥድስት ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነ።

የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ሕገ-መንግሥታዊና በሕገ-መንግሥት ሥርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች የሚመለከተው ችሎት ነው።

የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጀነራል ዐቃቤ ሕግ በአቡነ ሉቃስ ላይ ከሦስት ወራት በፊት÷ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 247 (ሐ) እና አንቀጽ 258 (ሀ) ሥር እና የወንጀል ሕግ አንቀጽ 251 (ሐ) የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል የሚሉ ሁለት ክሶች ማቅረቡ ይታወሳል፡፡

ተከሳሹ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ-ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል እና የምሥራቅ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ በጠቅላይ ቤተክኅነት የገዳማት መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ-ጳጳስ ሆነው በማገልገል ላይ እያሉ ስለ ሰላም እና አንድነት የመስበክ ሐይማኖታዊ ግዴታቸውን በመተው ታኅሣስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በአሜሪካ ቴክሳስ እና አካባቢው በሚገኝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ-ክርስቲያን ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ቤተ-ክርስቲያን ታቦት ወጥቶ በቆመበት ዐውደ-ምኅረት ላይ የአመፅ ቅስቀሳ ማድረጋቸውን የክስ ዝርዝሩ ያስረዳል፡፡

የዐቃቤ ሕግን ማስረጃ የተመለከተው ፍርድ ቤትም የተከሰሱባቸው ክሶች በአንቀጽ 247 (ሐ) ሥር ተጠቃልሎ የጥፋተኝነት ፍርድ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፡

በመሆኑም ዐቃቤ ሕግ ካቀረባቸው ሦስት የቅጣት ማክበጃ አስተያየቶች መካከል ፍርድ ቤቱ አንዱን የቅጣት ማክበጃ አስተያየት በመያዝ እና ተከሳሹም የቀደመ የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው መሆኑን መነሻ በማድረግ አንድ የቅጣት ማቅለያ ተይዞላቸው ዛሬ በዋለው ችሎት የቅጣት ውሳኔ ተሰጥቷል።

በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ በእርከን 23 ሥር በሥድስት ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ በሌሉበት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ (በታሪክ አዱኛ)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ወሳኝ ጥቆማ እንዳያመልጣቹ‼️

ቴሌግራም ብቻ በመጠቀም ምንም ብር ሳታወጡ ገቢ የምታገኙበት መንገድ እያመቻቸን እንገኛለን።

አሁንኑ በዚ ቻናል ይቀላቀሉ👇👇
Join us 👉 https://www.tg-me.com/sheger_crypto
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ያሳልፈው ውሳኔ "ትክክለኛ" እርምጃ ነው አሉ‼️ 

የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባሉ ጌታቸው ረዳ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የዛሬው ውሳኔ ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ የተደረገ አንድ እርምጃ ነው አሉ።

ጌታቸው ረዳ በይፋዊ የኤክስ ገፁ እንዳሰፈረው፤ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ይፋ የተደረገበትን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መግለጫ በማያያዝ "የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ ሰላምን ለማጠናከር ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ አንድ እርምጃ የተራመደ ነው" በማለት ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press
የአማራና የኦሮሚያ ክልሎች በሚዋሰኑበት የሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እያደረሱባቸውና በርካቶች እየተፈናቀሉ እንደኾነ ነዋሪዎች ለዋዜማ ሪፖርተር ተናግረዋል።

በተለይ ሰረርኩላ እና ቱቲን የመሳሰሉ ቀበሌዎች ነዋሪዎች፣ የትምህርትና ጤና አገልግሎቶችን ማግኘት እንዳልቻሉ ተናግረዋል።

ነዋሪዎች ጥቃቱን የሚያደርሱባቸው፣ ከአማራ ክልል ተሻግረው የሚመጡ የፋኖ ታጣቂዎች እንደኾኑ ዋዜማ ሰምታለች።

ግንቦት 14 ቀን፣ እነዚሁ  “የደራ ማንነት አስመላሽ ኃይል” የሚል ስያሜ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በሰረርኩላ፣ ቱቲ፣ ብርጄ፣ ሰንቀሌ እና አባዶን በተባሉ ቀበሌዎች በተመሳሳይ ሰዓት በፈጸሙት ጥቃት፣ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸውን የዐይን እማኞች ተናግረዋል።

የፋኖ እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ሰላማዊ ሰዎችን አፍኖ በመውሰድ ገንዘብ እንደሚጠይቁም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በ1 ቢሊዮን ብር የተገነባው የራሱ ቢራ መጥመቂያ ያለው ሆቴል በቢሾፍቱ

አቶ አማኑኤል ሳይፈርት ይባላሉ፣ በአውሮፓ ጀርመን 22 አመት ኖሯል። መንግስት ለዲያስፖራው ባመቻቸው የኢንቨስትመንት እድል ተጠቅመው ወደ ሀገራቸው በመምጣት አቶ አማኑኤል በኮንስትራክሽን ሴክተሩ ላይ ከሰሩ በኋላ በሆቴሉ ዘርፍ ላይ ክፍተት በመመልከት የቱሪዝም ማዕከል በሆነችው በቢሾፍቱ ከተማ ሆቴል ለመክፈት እንቅስቃሴ ጀመሩ፣ እንቅስቃሴው ተሳክቶ ከ12 አመት ግንባታ በኋላ ተጠናቆ ለቢሾፍቱ ከተማ ተጨማሪ ድምቀት ሆኖ ሳይፈርት ሆቴል ተከፍቶ ስራ ጀምሯል።

ሳይፈርት ሆቴል የተለያየ ደረጃ ያላቸው 100 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን ለውጪ ሀገር ዜጎች ከ40 እስከ 100 ዶላር ክፍያ ይጠይቅባቸዋል፣ ለኢትዮጵያዊያን ክፍያው ከውጪ ሀገር ዜጎች እንደሚለይ ተነግሯል።

1900 ካሬ ላይ ያረፈው ሆቴሉ 9 የስብሰባ አዳራሾች፣ ስፓ፣ ጂም፣ ዋና ገንዳ እንዲሁም የራሱ የቢራ መጥመቂያ እንዳለው አቶ አማኑኤል ተናግሯል።

ሆቴሉን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ የጨረሰ ሲሆን ለ250 ዜጎች ቋሚ የስራ እድል ፈጥሯል።(FastMereja)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በኢትዮጵያ፣ በግጭቶችና ጦርነት ከደረሰው ጉዳት መልሶ ለማገገም 44 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከሌሎች የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ባደረገው አዲስ ጥናት ማመልከቱን ሪፖርተር ዘግቧል።

አገሪቱ በግጭቶችና ጦርነቶች ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከአጠቃላይ ምርቷ 7 ነጥብ 5 በመቶ የሚኾነውን እንዳጣች ጥናቱ ማረጋገጡን ዘገባው ጠቅሷል።

ኢትዮጵያ ጦርነትና ግጭቶች ካደረሱባት ጉዳት ለማገገም፣ የሰሜኑ ጦርነት ካለቀበት ጊዜ ጀምሮ አምስት ዓመታት ሊወስድባት እንደሚችልም ጥናቱ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል።

ገንዘብ ሚንስቴር ባለፈው ዓመት ባካሄደው ጥናት፣ ለመልሶ ግንባታ 29 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ አስታውቆ ነበር።

አዲሱ ጥናት በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ባለፉት ኹለት ዓመታት በተከሰቱ ግጭቶች የደረሱ ጉዳቶችን አያክትትም ተብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
ጥቆማ‼️

Hamster‼️

Guys ይህ ትልቅ ብር ማግኛ ኤርድሮፕ ነው እየተባለ ይገኛል

በርግጠኝነት እንገራቹ ይህ List መሆኑ አይቀሬ ነው ።

አሁንኑ በመጀመር ታፕ ታፕ አድርጉ

ያልጀመራቹ ጊዜው ሳይረፍድ  አሁንኑ በዚ ሊንክ ጀምሩት👇

ለመጀመር👇👇
https://www.tg-me.com/hamster_kombat_bot/start?startapp=kentId769729488


አጨዋወቱን ለከበዳቹ ዝርዝሩን በዚ ቻናል ያገኙታል👇👇
https://www.tg-me.com/sheger_crypto
አቶ የሽዋስ አሰፋ መታሰራቸው ተሰምቷል‼️

በአንድ ወቅት ሰማያዊ ፓርቲን አፍርሰው ወደ ኢዜማ ሲቀላቀሉ "ከትንንሽ ፓርቲ መሪነት ይልቅ የትልቅ ፓርቲ አባል መሆን ይሻላል" በሚል ንግግራቸው ስማቸው ጎልቶ የሚነሳው የሽዋስ አሰፋ ትናንት ግንቦት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት አንድ ሰዓት ካዛንቺስ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ ተይዘው እንደተወሰዱ ከቤተሰቦቻቸው ተሰምቷል።

አሁን ላይ ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያ እንዲመገኙ ለማወቅ ተችሏል።ለእስር ያበቃቸው ጉዳይ በግልፅ አልታወቀም።

@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

Online ስራ መስራት ከፈለጉ ሸገር Crypto ቻናልንን ይቀላቀሉ።

በርግጠኝነት ይወዱታል👇

JOin 👉 https://www.tg-me.com/sheger_crypto
አመራሩ ተገደሉ‼️

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የኤፍራታና ግድም ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ አልብስ አደፍራሽ በቀን 24/9/2016 ዓ.ም ከለሊቱ 6:00 ሰዓት አካባቢ በቤታቸው እያሉ በተተኮሰባቸው ጥይት ህይወታቸው ማለፉን ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘሁት መረጃ ያመላክታል(አዩዘበሀሻ)።
ነፍስ ይማር

@sheger_press
@sheger_press
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና ፕሬዝደንት ኢሳያስ በደቡብ ኮሪያ ዋና ከተማ ሴኡል ይገኛሉ‼️

ሁለቱ መሪዎች በደቡብ ኮሪያ የአፍሪካ  የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ደቡብ ኮሪያ ሴኡል ይገኛሉ።

ኢሳያስ አፈውርቂ ትናንት ወደ ሴኡል ያቀኑ ሲሆን ጠ/ሚ አብይ አህመድ ዛሬ ጠዋት ደቡብ ኮሪያ ሴኡል መድረሳቸው ታውቋል። በደቡብ ኮሪያ የሚካሄደው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ነገ ይጀመራል።

@ethio_mereja_news
" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ረቂቁ ከባለፈው መጠነኛ ማሻሻያዎች ተደርጎበት መቅረቡን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

በመጀመሪያው ረቂቅ አዋጅ ያልነበረና የመንግሥትንና የክልሎችን ግዴታና ኃላፊነት በመዘርዘር የተቀመጠው ክፍል አንዱ ነው።

በዚህ ክፍል ላይ መንግሥት በሃይማኖት አስተምህሮና የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት እንደማይችል ተደንግጓል፡፡

በተጨማሪ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት ተደንግጎ የነበረው የረቂቅ አዋጁ ክፍል ከተሻሻለው ረቂቅ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

ነገር ግን ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ፦

የሃይማኖት ተቋሙን ኦዲት ሪፖርት ለሰላም ሚኒስቴር እንዲያቀርብ፣

የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ #በ3_ወራት የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር እንደሚኖርበት የተቀመጠው የረቂቁ ክፍል በተሻሻለው ላይ #ተካቷል፡፡

ሌላኛው ተሻሽሎ የቀረበው የረቂቅ ክፍል አለባበስን እና የተማሪዎች አመጋገብን ጨምሮ በማንኛውም የትምህርት ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚደረግ ሃይማኖታዊ ተግባር የመንግሥትና ሃይማኖት መለያየት መርህንና የሃይማኖት ነፃነትንም በጠበቀ መንገድ መከናወን አለበት የሚለው ነው፡፡


የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረኩ የመጨረሻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በመንግሥት እና በሃይማኖት መካከል ያለው ልዩነት ምን ድረስ እንደሆነ ሳይታወቅ ቆይቷል ብለዋል።

አዋጁን ማዘጋጀትም ያስፈለገው ይህን ጉዳይ በግልጽ ለማስቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

(Reporter Newspaper)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በምስራቅ ሃረርጌ ዞን ከእድሜ እኩያው ጋር በተፈጠረ ፀብ የግድያ ወንጀል የፈፀመዉ ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን በደኖ ወረዳ ጎሮ ቀበሌ ውስጥ ከእድሜ እኩያው ጋር በተፈጠረ ፀብ ቅራኔ ውስጥ ገብቶ የተጣላውን ልጅ አባት በመግደል የተከሰሰ ግለሰብ በፅኑ እስራት መቀጣቱን የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታውቋል ።

የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ሃላፊ አ/ቶ  ሳሊም ሙክታር ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ተከሳሽ አልኸዲን ሃማዝ የእድሜ እኩያውን ወላጅ አባት ላይ የግድያ ወንጀል መፈፀሙን ገልፀዋል ።ተከሰሹ ግንቦት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ የተጣላውን የእድሜ እኩያውን ለማጥቃት ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲሄድ በማጣቱ በያዘው ስለታማ መሣሪያ አ/ቶ ሙሃመድ አብዱልመጅድ ጭንቅላታቸውን በመምታት ከፍተኛ ጥቃት አድርሶባቸዋል ።

ተከሳሹ በወቅቱ ጉዳቱን በማድረስ ተሰውሮ የነበረ ሲሆን ጉዳት የደረሰባቸው አ/ቶ ሙሃመድ በአካባቢው ማህበረሰብ ትብብር ህክምና ቢያገኙም ህይወታቸው ማለፉ ተጠቁሟል ። ፖሊስ በበኩሉ ተጠርጣሪውን ክትትል በማድረግ በቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በህክምና ማስረጃ በማጠናከር ለዓቃቤ ህግ ይልካል ።

ዓቃቤ ህግም የደረሰውን የምርመራ መዝገብ ተንተርሶ በተከሳሹ ላይ ክስ መስርቶበታል ። ዓቃቤ ህግ የመሠረተውን ክስ ሲመለከት የቆየው የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ ሲል ብይን ሰጥቷል ። 

ፍርድ ቤቱ ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎችም ያስጠነቅቃል በማለት ተከሳሽ አልኸዲን ሃማዝ በ15 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል ።

@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

Hamster‼️

Guys ይህ ትልቅ ብር ማግኛ ኤርድሮፕ ነው እየተባለ ይገኛል

በርግጠኝነት እንገራቹ ይህ List መሆኑ አይቀሬ ነው ።

አሁንኑ በመጀመር ታፕ ታፕ አድርጉ

ያልጀመራቹ ጊዜው ሳይረፍድ  አሁንኑ በዚ ሊንክ ጀምሩት👇

ለመጀመር👇👇
https://www.tg-me.com/hamsTer_kombat_bot/start?startapp=kentId1204288009


አጨዋወቱን ለከበዳቹ ዝርዝሩን በዚ ቻናል ያገኙታል👇👇
https://www.tg-me.com/sheger_crypto
"እባካችሁ ወጣቶች አትቀመጡ፣ስራ ለመፍጠር ሞክሩ፣እኛ ነፃ ስልጠናና ሌሎች እገዛዎችን እናደርጋለን"EDI

ኢዲአይ ከሰሞኑ ከወዳጆቼ ጋር ለትውውቅና አጭር ስልጠና ጋብዞንን ነበር። በቅድሚ ትውልድን ወደ ስራ ፈጣሪነት ለማስገባት የተቋቋመ በመሆኑ ለተቋሙ የስራ ኃላፊዎች ትልቅ አክብሮት አለኝ።

የኢትዮጵያ ኢንተርፕርነርሺፕ ኢንስትቲዩት(EDI) ይባላል።ከፊል-ራስ-ገዝ የምርምር አስተሳሰብ በኢኮኖሚ ጥናት እና የፖሊሲ ትንተና ፣ ምርምር እና ፖሊሲ ማጠናቀር ፣ አቅም መፍጠር፣ የእውቀት ሽግግር እንዲካሄድ በስራ ፈጠራ ላይ የሚያሰለጥን እና የሚያማክር ተቋም ነው።

በኢትዮጵያ የሚዲያ ኢንድስትሪ ውስጥ ለሚመጣው አዲስ የኢንተርፕርኒያል ሚዲያ አስተሳሰብ የድርሻውን ለመወጣት ነበር ያሰባሰበን።የሚዲያ አንቀሳቃሾቹ በኢኮሲስተም ውስጥ ዋና ተዋናይ መሆን እንዲችሉ ባላቸው ላይ ጥሩ ግንዛቤን ያስጨበጠ ቆይታ ነበር።
"እባካችሁ ወጣቶች አትቀመጡ፣ስራ ለመፍጠር ሞክሩ፣እኛ ነፃ ስልጠናና ሌሎች እገዛዎችን እናደርጋለን" ከተቋሚ የስራ ሃላፊዎች በተደጋጋሚ ሲነገር የነበረ ሃሳብ ነው።የEDI ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀሰንን ጨምሮ አሰልጣኞችና አስተባባሪዎች እነ ዳኒ ትውልድ ላይ እየሰራችሁት ያለው መልካም ስራ ለሌሎችም ምሳሌ ነውና በርቱልን።(wasumohammed)

@ethio_mereja_news
መረጃ‼️

እስክንድር ነጋ ከመንግስት ሰዎች የሰላም ድርድር ሂደት መጀመሩ ታውቋል

እስክንድር ነጋ የፋኖ ታጣቂዎችን ወክሎ ከመንግስት ድርድር መጀመሩ ተገልጿል። በ3ኛ ወገን አመቻችነት እስክንድር ነጋ ከመንግስት ሰዎች ጋር ቀጥተኛ ያልሆነ የድርድር ሂደት መጀመሩ ተጠቁሟል።

መንግስት ከእስክንድር ጋር እያደረገ ያለው ድርድር የሚሳከ ከሆነ ከእስክንድር ቡድን ጋር ከሸዋ የሻለቃ መከታው ቡድን፣ ከወሎ የምሬ ወዳጆ እና የኮ/ል ፈንታሁን ቡድኖች፣ ከጎጃም የማስረሻ ሰጤ እና የማንችሎት ቡድኖች፤ ከጎንደር በሻለቃ ሀብተ ወልድ የሚመራ ቡድን ወደ በድርድርሩ እንዲሳቱፉ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።

ከሰላም ውጪ ሌላ አማራጭ መንገድ የለም! ሰላም ለኢትዮጵያ(natnael)

@ethio_mereja_news
2024/10/01 22:35:27
Back to Top
HTML Embed Code: