Telegram Web Link
ተፈታለች‼️
ደራሲ እና አርቲስት አዜብ ወርቁ መታሰሯ ከሰዓታት በፊት ተዘግቦ ነበር‼️
ዛሬ በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው አዜብ ወርቁ ለግማሽ ቀን ያህል በእስር ከቆየች በኋላ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ተለቃለች።
አርቲስቷ ሰሞኑን "ልማት የሰውን ልጅ ሲያፈርስ በዓይኔ አየሁት!" የሚል ጽሁፍ በማህበራዊ ሚዲያዎች ካጋራች በኋላ ጽሁፉ ብዙዎች ተጋርተውት እንደነበርና በኋላም ከማህበራዊ ገጿ ጽሁፉን ማንሳቷን ማስታወቋ አይዘነጋም።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ፕሪሚየር ሊጉ መቐለ 70 እንደርታ እና ሀዲያ ሆሳዕና በሚያደርጉት ጨዋታ ዛሬ ይጀመራል

የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቐለ 70 እንደርታ እና ሀዲያ ሆሳዕና በሚያደርጉት ጨዋታ ዛሬ ይጀመራል፡፡

በሊጉ የመክፈቻ ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች የሚያደርጉት መርኃ ግብር 10 ሰዓት ላይ በድሬዳዋ ስታዲየም ይካሄዳል።

በዛሬው የጨዋታ መርኃ ግብር ከምሽቱ 1 ሰዓት አርባ ምንጭ ከተማ ከድሬዳዋ ከተማ የሚከናውኑት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።

በዘንድሮው ፕሪሚየር ሊግ መቐለ 70 እንደርታ፣ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ እና ስሑል ሽረ ዳግም ወደ ውድድር መመለሳቸውን ተከትሎ በዚህ የውድድር ዘመን በ19 ክለቦች መካከል ውድድር ተደርጎ 5 ክለቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ እንደሚወርዱ ተጠቅሷል።

ፕሪሚየር ሊጉ በቀጣይ ዓመት ወደነበረው ፎርማት የሚመለስ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት ግን በየሳምንቱ አንድ አራፊ ቡድን ኖሮ ውድድሩ በ19 ክለቦች መካከል እንደሚከናወን የሊጉ አክሲዮን ማህበር መረጃ ያመለክታል።

@sheger_press
@sheger_press
ንግድ ባንክ ቪዛ ካርድን በአለም አቀፍ ደረጃ መጠቀም የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ!!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞቹ ካርዶችን በአለም አቀፍ ደረጃ መጠቀም የሚያስችላቸዉን ስምምነት ከቪዛ ኢንተርናሽናል ጋር ተፈራረመ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳት አቤ ሳኖ እንደገለጹት ፤ባንኩ ከቪዛ ኢንተርናሽናል ጋር ለረጅም አመታት የዘለቀ አጋርነት ያለዉ ሲሆን የሚጠቀምባቸዉ ካርዶችም የቪዛ ኢንተርናሽናል ናቸው።

በዛሬዉ ዕለት ባንኩ ያደረገው ስምምነት ወደ ዉጭ የሚጓዙ ደንበኞች በውጭ ምንዛሬ በአለም አቀፍ ደረጃ መጠቀም የሚያስችላቸው ነው ብለዋል። ስምምነቱ ለአምስት አመት የሚቆይ ሲሆን ቪዛ ለባንኩ ድጋፍ እንደሚያደርግም ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press
News‼️

ኢትዮጵያ ወደ ሶማሊያ ፑንትላንድ ግዛት የምታጓጉዘው ያልተፈቀደ የጦር መሳሪያ ዝውውርን በጽኑ አወግዛለሁ አለ

ይህ ድርጊት በሶማሊያ ሉዓላዊነት ላይ ከፍተኛ ጥሰትን የሚፈጥር እና ከባድ የብሄራዊ እና ክልላዊ ደህንነት አንድምታዎችን ይፈጥራል ብሏል።
ከኢትዮጵያ ወደ ፑንትላንድ የጦር መሳሪያ ሁለት መኪናዎች ያለምንም ዲፕሎማሲያዊ ተሳትፎ እና ፍቃድ የጦር መሳሪያ ሲያጓጉዙ በሰነድ የተገኙ መረጃዎች ያረጋግጣሉ፣ ይህም የሶማሊያን የግዛት ሉዓላዊነት በግልፅ መጣሱን ያሳያል ብሏል። የሶማሊያ መንግስት ኢትዮጵያ ለአለም አቀፍ ህግጋት የምታደርገውን ጥረት እና ለቀጣናው መረጋጋት ያላትን ቁርጠኝነት በእጅጉ እንዳሳሰበው ገልጿል። አሁን በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈጠረው ውጥረት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈቱ ቁሮጠኛ ነን ብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
የፍቅር እስከመቃብር ፊልም በፍርድ ቤት እግድ ወጣበት።

ወደ ፊልም ተቀይሮ በኢቢሲ እየታየ የነበረው የክቡር ዶክተር ሐዲስ አለማየሁ «ፍቅር እስከ መቃብር» ልብወለድ እንዳይታይ ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ መስጠቱ ተሰምቷል።

"የቀረበው ክርክር ተመርምሮ ውሳኔ ለመስጠት እስከተያዘው ተጠሮ ማለትም እስከ ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወይም ከወዲሁ ትእዛዙ መነሳቱ እስከሚገልጽ ድረስ ወደ ፊልም የተቀየረው ተጠቃሹ የድርሰት ስራ በማናቸውም መንገድ ለህዝብ እይታ እንዳይቀርብ እንዳይሰራጭ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ/ ቁጥር 154 መሰረት ታግዷል።" ያሳገዱትም የደራሲው ቤተሰቦች ናቸው ተብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
ኤክስፐርት ለመሆን እና ከፍተኛ ተፈላጊነት ባላቸው ሙያዎች የምስክር ወረቀት ማግኘት ይፈልጋሉ? የ Safaricom Talent Cloud ትክክለኛው ቦታ ነው፡ https://bit.ly/3Re7G22

በመረጡት የትምህርት ዘርፍ እውቀትን ለመገንባት በጥሩ ሁኔታ ከተዘጋጁ ኮርሶች በተጨማሪ የሚከተሉትን ያገኛሉ፡-

- በመረጡት የሙያ መስክ የላቀ ለመሆን እንዲረዳዎ በባለሙያዎች የተመረጡ የትምህርት ካሪኩለሞች
- እጅግ ታዋቂ ከሆነው Pluralsight የonline መማሪያ ድህረገጽ ሰርተፍኬት
ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚመሩ የስልጠና ቡድኖችን
- በየወሩ ነጻ የ6 GB የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ

እነዚህን ተጨማሪ ጥቅማጥቅሞችና ግልጋሎቶች በማግኘት በፍጥነት ያሎትን እዉቀትና ክህሎት በማሳደግ በስራ ዘርፎ ዉጤታማ መሆን ይችላሉ። https://bit.ly/3Re7G22 ይጎብኙ!

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራሞ ቻናላችንን ይቀላቀሉ https://www.tg-me.com/+3nNaOCMHiXgyMTA0
ዛሬ መስከረም 11 2017 ባንኮች 1 ዶላርን በስንት ብር እየመነዘሩ ነው?

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1 ዶላር በ112 ብር እየገዛ፤ በ123 እየሸጠ ይገኛል

ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኗን ተከትሎ ባንኮች አዲሱን የምንዛሬ ተመን ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

የ2017 አዲስ ዓመት አስመልክቶም ባንኮች በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያውን በባንኮች አማካኝነት ገንዘብ እንዲልኩ የሚያበረርታታ ተመን እያወጡ ነው።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች በኩል የሚላክን ገንዘብ ከባንኩ ለሚቀበሉ ደንበኞቹ ተጨማሪ የ6.82 በመቶ የበዓል ስጦታ እንደሚሰጥ አስታውቋል።

ባንኩ ዛሬ መስከረም 11 2017 ዓ.ም መደበኛ የውጭ ሀገር ገንዘቦችን የሚገዛበትን እና የሚሸጥበትን ዋጋ ይፋ ሲያደርግ የመግዣ ዋጋውን የትናንቱን አስቀጥሏል። በዚህም አንድ የአሜሪካ ዶላርን በ112.3957 ብር እየገዛ በ123.6353 ብር እየሸጠ ይገኛል።

እስከ መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ የሚላክን አንድ የአሜሪካ ዶላር በ125 ብር እንደሚመነዝር ያስታወቀው ንብ ባንክም መደበኛውን (እለታዊ የምንዛሬ ተመን) ይፋ አድርጓል።

ባንኩ በእለታዊ መደበኛ የመንዛሬ ዋጋ አንድ የአሜሪካ ዶላር በ109.7209 ብር እየገዛ በ122.8874 ብር እየተሸጠ መሆኑን ገልጿል።

ኦሮሚያ ባንክም በዓልን ምክንያት በማድረግ ከውጪ በሃዋላ የተላከ አንድ የአሜሪካ ዶላርን ከእለታዊ ተመን በተጨማሪ 17 በመቶ ጉርሻ እንደሚሰጥ እና በዚህም 1 ዶላርን በ126+ ብር እንደሚመነዝር ማስታወቁ ይታወሳል።
ባንኩ የዛሬ የመስከረም 11 2017 መደበኛ የምንዛሬ ተመኑን ይፋ ሲያደርግ 1 የአሜሪካ ዶላር በ109.2120 ብር እየገዛ በ125.4096 ብር እየሸጠ መሆኑን ነው የጠቆመው።[አል አይን]
Forwarded from Sheger Press️️
Want to become an expert and get certified in skills that are in high demand? The Safaricom Talent Cloud is the right place: https://bit.ly/3Re7G22

Besides well-designed courses to build expertise in the area you pick, you also get:

• Personalized learning paths to help you master your chosen field
• Certificates from the popular online learning site Pluralsight
• Coaching groups led by experienced professionals to guide you
• Free 6GB internet data every month for learning

With these benefits and resources, you can quickly develop valuable expertise and advance your career. Visit: https://bit.ly/3Re7G22
Join our Telegram channel https://www.tg-me.com/+3nNaOCMHiXgyMTA0
መቀሌ

በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ህውሃት በመቀሌ ከተማ ህዝባዊ ውይይት እየተካሄደ ነው።

መድረኩን የህወሓት ሊቀ መንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ አማኑኤል አሰፋ እና የመቀሌ ከተማ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና ከንቲባ ይትባረክ አምሃ እየመሩት ይገኛሉ።

ውይይቱ ከመስከረም 11 እስከ 16 በሁሉም ከተሞችና ወረዳዎች ይካሄዳል።

በውይይት መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሕወሃት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብፅዮን ገብረሚካኤል መድረኩ በዚህ ፈታኝ ጊዜ ውስጥም ቢሆን ከህዝቡ ጋር በመመካከር መካሄድ አለበት ብለዋል።

እነዶ/ር ደብረፅዮን ከሠሞኑ በጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር ውጥረት ውስጥ መግባታቸው ይታወሳል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ15 ዓመት ታዳጊን ለአራት በመሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ

በኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ኦፓላሼ ቀበሌ ለአራት በመሆን የ15 ዓመት ታዳጊን አስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ።

ተከሳሾች በቁጥር አራት ሲሆን አስፋቸው አለሙ፣ አሻግሬ አበራ፤  ማቲዎስ ደዋና እና አስማማው አሉላ የተባሉ ግለሰቦች ናቸው።

ግለሰቦቹ በአመያ ዙሪያ ወረዳ በግምት 8:00 አካባቢ  ጫሬ ዶቄ ቀበሌ ቤተሰብ ለመጠየቅ ወደ ኦፓላሼ ቀበሌ እየሄደች የምትገኝ የ15 አመት ታዳጊ አስገድደው መድፈራቸውን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች  ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ክስ የቀረበባቸው ወንጀለኞች ጳግሜ 5 ቀን 2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው 7 ዓመት ፅኑ እስራት  ተቀጥተዋል።

አራተኛ ተከሳሽ ዕድሜው ከ10 እስከ 13 ዓመት በመሆኑ ተከሳሹ  መታሰር የማይችልና እንደዚህ ዓይነት ታዳጊ እስረኞችን ተቀብሎ   በማረምያ ተቋም በዞኑ ባለመኖሩ ምክንያት ቤተሰቡ ፈርሞ ወስዶት ክትትልና በቁጥጥር እንዲያደርግ በማለት ውሳኔ መሰጠቱን ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ  እና  ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

#ዳጉ_ጆርናል

@sheger_press
@sheger_press
በእሳት አቃጠሉት ‼️

በብራዚል የአንድ አመት እና የሰባት ወር ህፃናትን በደፈረ ግለሰብ የተቆጡ ሰዎች ፖሊስ ጣብያውን ሰብረው በመግባት ደፋሪውን ከነ ህይወቱ አቃጥለውታል።

@sheger_press
@sheger_press
2024/10/03 13:17:33
Back to Top
HTML Embed Code: