Telegram Web Link
በኮሬ ዞን በእገታ ላይ የነበሩ አራት አርሶ አደሮች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን በታጣቂዎች ታግተው የነበሩ አራት አርሶ አደሮች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች ለዶቼ ቬለ ገለጹ ፡፡ ታጣቂዎቹ ግድያውን ትናንት ሐሙስ የፈጸሙት አርሶ አደሮቹን ለመልቀቅ በመያዣነት የጠየቁትን አንድ መቶ ሺህ ብር እና አንድ ካርቶን የትምባሆ ሲጋራ ከተቀበሉ በኋላ ነው ተብሏል ፡፡

አርሶ አደሮቹ የታገቱት ትናንት ሐሙስ ማለዳ ከብት እያሠማሩ ባሉበት ወቅት መሆኑን ለዶቼ ቬለ የተናገሩት ሦስት የሟች የቅርብ ዘመዶች «ታጣቂዎቹ ወደ ቀበሌው የገቡት ከአጎራባች የኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በመነሳት ነው ፡፡ ታጋቾቹን ከያዙ በኋላ ካሊያ ተብሎ ወደ ሚጠራው ጫካ ውስጥ ነው ይዘው የሄዱት ፡፡ አንድ መቶ ሺህ ብር እና አንድ ካርቶን የትምባሆ ሲጋራ ከተሰጣቸው እንደሚለቋቸው መልዕክት ልከውብን ነበር ፡፡ በተጠየቅነው መሠረት የተባልነውን ብንልክም ገንዘቡን እና ትምባሆውን ከተቀበሉ በኋላ ገድለዋቸው ሄደዋል ፡፡ ቀብራቸውም ዛሬ ዓርብ እየተፈፀመ ይገኛል» ብለዋል ፡፡

ዶቼ ቬለ በአርሶ አደሮቹ ግድያ ላይ የኮሬ ዞን አስተዳዳሪንም ሆነ የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎችን አስተያየት ለማካተት ያደረገው ጥረት አመራሮቹ ስብሰባ ላይ ናቸው በመባሉ ሊሳካ አልቻለም ፡፡ ያም ሆኖ የአርሶ አደሮቹን መገደል በተረጋገጠ የፌስ ቡክ ገጹ የገለጸው የዞኑ መስተዳድር የድርጊቱ ፈጻሚዎች በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ቡድኖች ናቸው ሲል ዐሳውቋል ፡፡

@sheger_press
@sheger_press
🛑 "ሀገርን ለማስቀጣት የሚደረገው እንቅስቃሴ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል!"

"ከሳሾች በውሸት ቃለ መሀላ ፍርድ ቤቱን ያሳሳቱ በመሆናቸው ራሳቸው በሕግ የሚጠየቁበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም!" 

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ለከሰሱት ጠበቆችና ለአራቱ ከሳሾች ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እንኳን ለ2017 አዲስ አመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ በማለት መግለጫ ይጀምራል

#Ethiopia  | የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በተሰጠው ስልጣን እና ተግባር መሰረት ኃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ ይገኛል ። ይሁን እንጂ በተቋሙ አሰራር የሚረካ እንዳለ ሁሉ ደስተኛ ያልሆነ ወይም ቅሬታ ያለው አካል ሊኖር ይችላል። ይህ በየትኛውም ድርጅት ያለና የሚኖር ነው።

ተቋሙ በስፖርት መድረክ አለመግባባቶች እና ቅራኔዎች ሲኖሩ የሚስተናገዱበት መንገድ  በመተዳደሪያ ደንቡ በግልፅ አስቀምጧል። አንቀፅ 38 ላይ " በኢትዮጵያ ብሔራዊ የኦሎምፒክ ኮሚቴ ውስጥ ወይም በኢትዮጵያ ብሔራዊ የኦሎምፒክ ኮሚቴ እና በአባላቱ መካከል የሚነሱ ማናቸውም ከስፖርት ጋር የተያያዙ ወይም ተቋማዊ ቅራኔዎች በሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ  የኦሊምፒክ ኮሚቴ የአስተዳደር አባላት ( በሜኔጅመንት በቦርድ ወይም በጠቅላላ ጉባኤ ወይም ለዚሁ ችግር አፈታት በሚቋቋም የፍትህ አካል ይፈታል ።

[ ከስፖርት ጋር የተያያዙ ያለመግባባቶችና ቅሬታዎች ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች ውጭ ይፈታሉ ።]

ጉዳዩ ለስራ አስፈፃሚ ቦርድ እና / ወይም የኢትዮጵያ ብሔራዊ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ከፍተኛ የስልጣን አካል ለሆነው ለጠቅላላ ጉባኤው ይመራል። ጠቅላላ ጉባኤው በቀረበው ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ወይም ቅራኔውን ለመፍታት የእርቅ ፣ የግልግል ወይም የሽምግልና አካል እንዲሰየም ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል ።

በቀረበው ቅራኔ ላይ የተሰጠ ማንኛውም የመጨረሻ ውሳኔ በአቤቱታ መልክ ብቻ ሉዛን ስዊዘርላንድ ለሚገኘው የስፖርት ዳኝነት ፍርድ ቤት ሊቀርብ ይችላል ።

አቤቱታውን ማቅረብ የሚቻለው የሚመለከተው ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በ21 ቀናት ቀነ ገደብ ውስጥ ነው። " ይላል ።

📌 በዚህ መሰረት :-

1ኛ / የስፖርት ነክ ጉዳዮች በመደበኛ ፍርድ ቤት እንደማይታዩ እና መደበኛ ፍርድ ቤት ስልጣን እንደሌላቸው እየታወቀ ህግና ስርአትን ተከትሎ ጥያቄ ማንሳት ሲገባ  የውሸት ቃለ መሀላ በማቅረብ እና ተረኛ ችሎቱን በማሳሳት እግድ ያወጡበት መንገድ ከሳሽ ነን የሚሉት ግለሰቦች ተከራክረው ማሸነፍ የሚችሉበት የእውነተኛ የሕግ መሰረት የሌላቸው መሆኑን ያሳያል።

በተጨማሪም በውሸት ቃለ መሀላ ያገኙትን እግድ ልክ ተከራክረው እንዳሸነፉ መግለጫ መስጠታቸው የቱን ያህል በኃላፊነት እና በተጠያቂነት ስሜት እንደማይሰሩ በግልፅ የሚያሳይ ነው።

ሀገርን ለማስቀጣት የሚደረገው እንቅስቃሴ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል።

2ኛ/ በአለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (IOC) ሙሉ በሙሉ የታገደው እና  እውቅና በግልፅ የተከለከለው እንዲሁም  የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አባል ያልሆነው በአቶ እያሱ ወሰን የሚመራው የቀድሞው የቦክስ ፌዴሬሽን ከሳሽ ሆኖ መምጣቱ " እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል! "  እንዳለችው እንስሳ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ይዤ ልውደቅ ከሚል ክፉ መንፈስ የመነጨ በመሆኑ ይህንን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲገነዘበው ለመግለፅ እንወዳለን።

3ኛ/ ሻለቃ ሀይሌ ገብረሥላሴ የባለፉትን አራት አመታት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝደንት ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል። ነገር ግን ራሱን 'ከደሙ ንፁህ ነኝ' በሚል እና ከዚህ ቀደምም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት በነበረበት ወቅት ለማናጀሮች እና ለስፖርት ትጥቅ አምራች ካምፓኒዎች  አሳልፎ በመስጠት ብሄራዊ ቡድን ያፈረሰው ራሱ ሆኖ እያለ የስፖርቱ ተቆርቋሪ ሆኖ መምጣቱ እጅግ አሳዝኖናል።

ለመሆኑ ሻለቃ ሀይሌ ገብረሥላሴ የባለፉትን አመታት የት ነበር ?

4ኛ/ ጀግናው አትሌት ገዛኸኝ አበራ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት እንደሆነ ይታወቃል። በፌዴሬሽኑ ውስጥ ያለበትን የማኔጅመንት ክፍተት ወደ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ይዞ መምጣቱ " ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ! " የሚባለው ብሂል ዓይነት ነው።

5ኛ/ ከዚህ ቀደም በኦሊምፒክ ኮሚቴ ውስጥ የስፖርት ትጥቆችን መርካቶ ድረስ ሄደው  በመቸብቸብ በፈፀሙት ሕገ ወጥ ተግባር በኮሚቴው የታገዱ አካላት ይህንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር ስልጣን በሌለው መደበኛ ፍርድ ቤት ከሳሽ ሆነው መቅረባቸው እጅግ አሳፋሪ ነው ።

6ኛ/ አንዳንድ የሚዲያ ባለሙያዎች ከግለሰቦች ጋር በግልፅ በገንዘብ በመደለል እና በጥቅም በመተሳሰር (ለዚህም በቂ ማስረጃዎች አሉ ) ለህብረተሰቡ የተዛቡ እና ሚዛናዊ ያልሆኑ የአንድ ወገንን መረጃ ብቻ በማቅረብ የስፖርት ቤተሰቡን እያሳሳቱት ይገኛሉ።

እስካሁን በሆደ ሰፊነት ሁሉንም ችለን አልፈነው የነበረ ቢሆንም ከዚህ በላይ መጓዝ ተቋሙን እና አገርን አደጋ ውስጥ ሊከት ስለሚችል እያንዳንዱን ድርጊታቸውን በማጋለጥ በሕግ የምንጠይቃቸው መሆኑን እንገልፃለን።

[  ከህገ ወጥ ድርጊታቸውም እንዲቆጠቡ ስንል በዚሁ አጋጣሚ እናሳስባለን።]

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ እየተካሄደ ያለውን ግልፅ ሕገወጥ ተግባር የስፖርት ቤተሰቡ ግራ ቀኙን አገናዝቦ እንዲመለከተው ጥሪውን ያስተላልፋል። የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምርጫ ታገደ ለሚባለው የደረሰን ነገር ባይኖርም በውሸት ቃለመሀላቸው የተሳሳተ ዳኛ ካለ በሕግ አግባብ እናስቀለብሳለን።

ከሁሉም በላይ እነዚህ ከሳሾች በውሸት ቃለ መሀላ ፍርድ ቤት ያሳሳቱ በመሆናቸው ራሳቸው በሕግ የሚጠየቁበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን እንረዳለን ።
ዳጉ_ጆርናል

@sheger_press
@sheger_press
በእነ ዳንኤል ዮሐንስ ላይ አቃቤ ህግ ክስ መሰረተ

የፍትህ ሚኒስቴር አቃቤ ህግ ዳንኤል ዮሐንስን ጨምሮ በስድስት ግለሰቦች ላይ ሦሥት ክሶችን መሰረተ፡፡

አቃቤ ህግ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ግለሰቦቹ ላይ የመሰረተው ክስ አውሮፕላንን አላግባብ በመያዝ፣ በማህበራዊ ሚደያ አማካኝነት በቀጥታ በማስተላለፍ መልካም ስም የሚያጎድፍ ተንቀሳቃሽ ምስል በኮምፒዩተር ስርአት አማካኝነት በማሰራጨት እና የመንግስት ሰራተኛ ኦፊሻላዊ የስራ ግዴታውን እንዳይፈፅም መቃወም እና አለመታዘዝ የሚሉ ናቸው፡፡

በሁለቱ ወንጀሎች ሁሉም ሲከሰሱ የመዝገቡ መጠሪያ የሆነው በቲክክቶክ የሚታወቀው ዮሀንስ ዳንኤል በሶስቱም ተከሷል፡፡

ለሁለት ሰአታት ሙሉ ከአውሮፕላን አንወርድም፤ ይከስከስ በማለት ሌሎችም እንዳይወርዱ በማሳደም በቲክቶክ ቀጥታ በማሰራጨት ሳይታገት ታግቻለሁ በማለት በቲክቶክ ስሙ ዮኒ ማኛን ቀጥታ በማስገባት የአየር መንገዱ ስም እንዲጎድፍ አድርጓል የሚለውንም አቃቤ ህግ ዘርዝሮበታል፡፡

@sheger_press
@sheger_press
በአፋሮችና ሶማሌዎች መካከል ሲካሄድ የቆየው የጎሳ ግጭት እንደቆመ ለግጭቱ መፍትሄ ለመስጠት የተቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ መግለጡን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል።

ብሄራዊ ኮሚቴው፣ በግጭት አካባቢዎች በመከላከያና ፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ሥር የኾነ ነጻ ቀጠና እንደተቋቋመና ግጭቶችን ማስቆ እንደተቻለ ኮሚቴው መናገሩን ዘገባው አመልክቷል።

የሰላም ሚንስትር ብናልፍ አንዷለም፣ ከነጻ ቀጣናው ያልወጡ ቀሪ ታጣቂ ኃይሎች ባስቸኳይ እንዲወጡ ማድረግና በአወዛጋቢ አካባቢዎች ሠፈራዎችን ማቆም እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል ተብሏል።

@sheger_press
@sheger_press
#በኦሮሚያ ክልል መቂ ከተማ‼️

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን በመቂ ከተማ ጳጉሜ 2/2016 ዓ.ም በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ የ4 አሽከርካሪዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ30 በላይ ተሸከርካሪዎች ደግሞ ጉዳት ማስተናገዳቸውን ከጥቃቱ ያመለጡ እማኞች ተናገሩ፡፡

ጥቃት አድራሾቹ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ታጣቂዎች እንደሆኑ ቢገለፅም ጥቃት ያደረሱት የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሀይል መለዮ የለበሱ ናቸው ሲሉ ከጥቃቱ ያመለጡ አሽከርካሪዎች ተናግረዋል።

@sheger_press
@sheger_press
ሚድሮክ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 400 ሰራተኞቹ ለእያንዳንዳቸው ከ100 እስከ 500 ሺህ ብር ስጦታ አበረከተ

👉 ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሰራተኞችና አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል



ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሰራተኞች እና አመራሮች ላከናወኑት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ አመራሮችና ሰራተኞቹ እውቅና ሰጥቷል።

በዚሁ ወቅት ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በዙም ባስተላለፉት መልዕክት፤ የተቋሙ ሰራተኞች እና አመራሮች ላከናወኑት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡም ገልፀዋል።

በመድረኩ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2016 በጀት ዓመት የዕቅዱን 90 በመቶ ማሳካቱ ተጠቅሷል፡፡

ተቋሙ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 400 ሰራተኞቹ ለእያንዳንዳቸው ከ100 እስከ 500 ሺህ ብር ስጦታም አበርክቷል።

#ዳጉ_ጆርናል

@sheger_press
@sheger_press
በመዲናዋ የ2017 የትምህርት ዘመን በመጪው ሰኞ ይጀመራል

በአዲስ አበባ ከተማ የ2017 የትምህርት ዘመን የፊታችን ሰኞ መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚጀመር የከተማው ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የ2017 የትምህርት ዘመን በመጪው ሰኞ በሁሉም ት/ቤቶች የሚጀመር መሆኑንም የቢሮው መረጃ ያመላክታል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሸኽ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን ለ400 ሠራተኞቹ ከ100 ሺ ብር እስከ 500 ሺ ብር ሰጥተዋል!

ሸኽ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን ለሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሰራተኞች እና አመራሮች ላከናወኑት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል።

የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ የላቀ አፈጻጸም ላሳዩ አመራሮችና ሰራተኞቹ እውቅና ሰጥቷል።

በዚሁ ወቅት ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በዙም ባስተላለፉት መልዕክት፤ የተቋሙ ሰራተኞች እና አመራሮች ላከናወኑት ተግባር ምስጋና አቅርበዋል። ሼህ መሀመድ ሁሴን አላሙዲን በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡም ገልፀዋል።

በመድረኩ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2016 በጀት ዓመት የዕቅዱን 90 በመቶ ማሳካቱ ተጠቅሷል፡፡ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 400 ሠራተኞቹ ለእያንዳንዳቸው ከ100 ሺ ብር እስከ 500 ሺ ብር ስጦታ ተበርክቷል።

@sheger_press
@sheger_press
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1 ሺህ 499ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ነገ ጀምሮ በቱርክ አንካራ ከተማ በሶማሊያ መንግስት እና ኢትዮጵያ ሊያደርጉት የነበረው ውይይት ሊራዘም እንደሚችል መረጃዎች እየወጡ ነው::

ይህ ስብሰባ ለሌላ ጊዜ የተራዘመበት ምክንያት ሁለቱም ወገኖች በአቋማቸው ላይ እስካሁን ምንም አይነት ለውጥ ባለማሳየታቸው ነው ተብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በካዛንችስ እና አዋሬ ፥ ከህንፃዎች እና አንዳንድ በደንብ ከተያዙ መኖርያ ቤቶች በቀር ሁሉም ፈራሽ ናቸው መባሉ ተሰማ

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር አመራሮች ባሳለፍነው ሳምንት ካዛንችስ ተገኝተው ነዋሪዎችን ባነጋገሩበት ወቅት ካዛንችስ እና አዋሬ ውስጥ ከህንፃዎች እና አንዳንድ በደንብ ከተያዙ መኖርያ ቤቶች በቀር ሁሉም ፈራሽ መሆናቸው እንደተነገራቸው ዳጉ ጆርናል ከመሠረት ሚዲያ ሰምቷል። ይህን የሚያስረዳ የድምፅ ሪከርድ ደርሶኛል ሲልም የዜና ምንጩ ዘግቧል።

ከበርካታ ነዋሪዎች የደረሰን መረጃ እንደሚጠቁመው በቅርብ ቀናት ካዛንችስ ከስድስተኛ ፖሊስ ጣብያ ጀርባ ያለው አካባቢ ሙሉ በሙሉ ሊፈርስ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

"መቼ እንደሚፈርስ ግን ትክክለኛው ግዜ አልተነገረንም" ያሉት ነዋሪዎቹ ይህም "እንቅልፍ ነስቶናል፣ ከዛሬ ነገ መጥተው ውጡ ሊሉን ይችላል" ብለው ከፍተኛ ስጋት እንዳደረባቸው ተናግረዋል።

Via መሠረት ሚዲያ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ዶናልድ ትራምፕ በነበሩበት አካባቢ የተኩስ እሩምታ እንደተሰማ ተገለፀ

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፍሎሪዳ በሚገኘው የትራምፕ አለም አቀፍ የጎልፍ ክለብ ውስጥ ጎልፍ እየተጫወቱ በነበረበት ወቅት በአካባቢው ድንገተኛ የተኩስ እሩምታ እንደተሰማ ተገልጿል፡፡

የዶናልድ ትራምፕ የምርጫ ዘመቻ ግንኙነት ኃላፊ ስቴቨን ቼዌነግ፤ ትራምፕ በቅርበት በነበሩበት አካባቢ የተኩስ ድምፅ እንደተሰማ አረጋግጠዋል፡፡

ከክስተቱ በኋላ ዶናልድ ትራምፕ ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የገለፁት ኃላፊው፤ አሁን በጉዳዩ ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ማቅረብ እንደማይቻል ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካ የሚስጥራዊ ደህንነት ተቋም (ሰክሬት ሰርቪስ) ጉዳዩን ከምዕራብ ፓልም ቢች ከተማ ፖሊስ ጋር በመሆን እየመረመረ መሆኑን ገልፆ፤ አሁን ላይ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ደህና መሆናቸውን ማስታወቁን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡

ከሁለት ወራት ገደማ በፊት በዶናልድ ትራምፕ ላይ የግድያ ሙከራ ከተደረገ በኋላ ለሊት ያጋጠመው ክስተት በትራምፕ ላይ ያነጣጠረ ይሁን አይሁን እስካሁን ግልጽ አለመሆኑም ነው የተገለፀው፡፡

ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ ህዳር ወር ለሚደረገው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በፔንሲልቬንያ የምረጡኝ ቅስቀሳ እያደረጉ በነበሩበት ወቅት የግድያ ሙከራ እንደተሰነዘረባቸው የሚታወስ ነው፡፡

የBernstein ተንታኞች ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ የ bitcoin ዋጋ በአመቱ መጨረሻ ላይ 90,000 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ተንብየዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
“በጦርነቱ ከአንድ ሚልዮን በላይ ትግራዋይ አለቀ  ተብሎ የሚወራው ማስረጃም ሆነ ጥናት የለውም።ለፖለቲካ ፉጆታ የተፈበረከ ነው።
ከተኩስ ማቆም ውጭ ያለውን የፕሪቶሪያ ስምምነት አንቀበለውም ብሏል። ትጥቅ መፍታትም ሆነ ሌላው በስምምነቱ ላይ መቀመጡንና መፈረማቸውን ቢያምንም  ከተኩስ ማቆም ውጭ ያለውን "እንታገለዋለን" ብሏል። " መጀመሪያ ስንሰማ ሁሉንም ያስደነገጠ ነው" ብሏል።
- ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለሆራይዘን ሚዲያ ከተናገሩት የተወሰደ

@sheger_press
@sheger_press
የኢትዮጵያ አየር መንገድን በፑንትላንድ እንዳያርፍ ተከለከለ‼️
👉ይህ ክልከላ ሌሎች አውሮፕላንችንም ያካትታል።
ይህንን ክልከላ የጣለው የሱማሊያ ፌዴራል መንግስት ሲሆን ምክንያቱ ደግሞ በመንግስትና በፑንትላንድ አስተዳደር መካከል በተፈጠረው ውዝግብ የተነሳ ነው፡፡ ውዝግቡን ተከትሎ የሱማሊያ ሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን ከዛሬ ጀምሮ በፑንትላንድ የሚገኘው የቦሳሶ አየር ማረፊያ ዝግ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የፑንትላንድ የፀጥታ አካላት የቦሳሶ አየር ማረፊያ አስተዳደርና ደህንነት ከቁጥጥራቸው ውጭ መሆኑን በመግለፅ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ በዚያ ለሚጠቀሙ አውሮፕላኖች ማስጠንቀቂያ ሰጥተው እንደነበር ተዘግቧል፡፡ ይሁንና ይህንን ማስጠንቀቂያ ቸል በማለት በረራቸውን የቀጠሉት የኢትዮጵያ አየር መንገድና የዳሎ አየር መንገድ ብቻ የነበሩ ሲሆን ዛሬ እነዚህም ቦሳሶ እንዳያርፉ ከሱማሊያ ሲቪል አቪየሽን እገዳ ተጥሎባቸዋል፡፡

ይህ የዛሬው እገዳ በሱማሊያና በፑንትላንድ መካከል ያለውን የፖለቲካ ሽኩቻ አንድ ደረጃ ከፍ ያደረገ መሆኑን የፖለቲካ ታዛቢዎች ተናግረዋል፡፡ የአየር ማረፊያው በመዘጋቱ በርካታ መንገደኞች ለእንግልት የተዳረጉ ሲሆን ሲቪል አቪየሽኑ ሌላ ማስታወቂያ እስከሚያወጣ ድረስ ዝግ ሆኖ እንደሚቆይ አስታውቋል፡፡

@sheger_press
@sheger_press
በአዲሱ ዓመት በአዲስ ክህሎቶች ራሳችሁን ብቁ አድርጉ። በሳፋሪኮም ታለንት ክላውድ ላይ የ 20% ቅናሽ ለወንዶች : 5,706 ብር የነበረው አሁን በ 1,141 ብር ብቻ ያግኙ።

- 6000+ tech and non tech ኮርሶች
- በ ቀጣሪዎች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ሰርተፍኬቶች
- በተለያዩ ፕሮጀክቶቻችሁ ላይ ከአቻ ባልደረቦቻችሁ ጋር አብራችሁ የምትሰሩበት እድል
- ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የሚመሩ የስልጠና ቡድኖችን
- በየወሩ ነጻ የ6 GB የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚም ይሆናሉ

በዚህ አዲስ ዓመት ግቦችን ብቻ አታስቀምጡ፣ ግቦቹን አሳኩት። አሁኑኑ ይመዝገቡ : https://bit.ly/4cQrem2

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ: https://www.tg-me.com/+3nNaOCMHiXgyMTA0
Forwarded from Sheger Press️️
Make the most of the New Year with New Skills. Invest in your future with Safaricom Talent Cloud’s exclusive 80% scholarship for women, originally 5,706 birr, now just 1,141 birr.

Build your future with:
- 6,000+ tech and non tech courses
- Certifications recognized by top employers
- A supportive learning community
- Expert coaching at every step
- 6 GB free internet monthly

Don’t just set goals this New Year, achieve them. Register now at https://bit.ly/4cQrem2 and make 2017 your year of success!

For more information, join our Telegram channel: https://www.tg-me.com/+3nNaOCMHiXgyMTA0
2024/10/02 20:32:19
Back to Top
HTML Embed Code: