Telegram Web Link
ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው ከትግራይ ክልል መሆኑ መግለፃችን ይታወሳል።

እውነት ለመናገር ከጦርነት ማግስት ከትምህርት ለረጅም ጊዜ ተርቆ ከፍተኛ ነጥብ ከኢትዮጵያ ማስመዝገብ በውነት በጣም የሚያስደንቅ ውጤት ነው።

@sheger_press
@sheger_press
ግብጽ በተደጋጋሚ የምታቀርባቸው ዛቻዎች እና አቤቱታዎች “መሠረተ-ቢሶች” ናቸው ስትል እንደማትቀበለው ኢትዮጵያ አስታወቀች!

ኢትዮጵያ ግብጽ በተደጋጋሚ የምታቀርባቸው ዛቻዎች እና አቤቱታዎች “መሠረተ-ቢሶች” ናቸው ስትል እንደማትቀበለው ለጸጥታው ምክር ቤት በጻፈችው ደብዳቤ አስታወቀች፤ የመንግስታቱ ድርጅትን ቻርተር በሚጻረር መልኩ እየሰነዘረችብኝ ያለችውን ተደጋጋሚ ዛቻ ምክር ቤቱ እንዲያጤንልኝ ስትል አሳስባለች።

አዲስ ስታንዳርድ የተመለከተው እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ፊርማ ያረፈበት ይህ ደብዳቤ እንደሚያሳየው “ኢትዮጵያ በፍትሐዊ የናይል ወንዝ አጠቃቀም ላይ ያላትን ቁርጠኝነት ገልፆ ግብጽ የአባይ ውሃን በብቸኝነት የመጠቀም ፍላጎቷን” ኮንኗል።

ኢትዮጵያ ለጸጥታው ምክር ቤት በላከችው በዚህ ደብዳቤ በቅርቡ የግብጹ ጠቅላይ ሚንስትር “በየትኛውም አገር የሚከናወን የልማት ፕሮጀክት: ግብጽ በናይል ወንዝ ላይ ያላትን ታሪካዊ ድርሻ በማይቀንስ ሁኔታ መካሄድ አለበት” ሲሉ መናገራቸው ጠቅሳ “ግብፅ አሁንም በቅኝ-ግዛት ህጎች እና አስተሳሰቦች በመመርኮዝ በአባይ ውሃ ላይ በብቸኝነት የመጠቀም ፍላጎቷን ያንጸባረቀ ነው” ስትል ኮንናለች።

በተጨማሪ ደብዳቤው ግብጽ “አዋጭነታቸው ያልተረጋገጡ” የልማት ፕሮጀክቶችን የወንዙን ተፋሰስ ሀገራት ሳታሳውቅ ስትገነባ መቆየቷን ኢትዮጵያ ስታሳውቅ እንደነበረ አስታውሶ: ይህም የሌሎቹን የተፋሰስ ሃገራት ጥቅም እና ፍላጎት ያገለለ መሆኑን አመላክቷል።

@sheger_press
@sheger_press
እንደሚታወቀው ለሊት ስድስት ሰዓት ዉጤት ማየት ይጀመራል።

እናም በተለያየ ምክንያት ውጤት ማየት የማትችሉ ተፈታኝ ቤተሰቦቻችን በተቻለን አቅም በማየት እናግዛለን

ውጤት ሲለቀቅ በዚ ቻናል እናሳያለን አሁንኑ ተቀላቅላቹ ጠብቁን👇👇

Join us 👇👇
https://www.tg-me.com/+XUeXEA4uaCM3YmVk
https://www.tg-me.com/+XUeXEA4uaCM3YmVk
https://www.tg-me.com/+XUeXEA4uaCM3YmVk
🚨 ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ:

"ሪሜዲያል ዘንድሮም አለ ነገርግን መጠኑን እንቀንሳለን ፤ በየአመቱ መጠኑ እየቀነሰ ነው የሚሄደው።"

@sheger_press
@sheger_press
ውጤት ማያ አማራጮች

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ከዛሬ ጳጉሜን 4/2016 ዓ.ም ለሊት 6:00 ጀምሮ ማየት እንደሚችሉ መገለፁ ይታወቃል።

በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን ተመልከቱ፦

በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot

ከውጤት መግለጫ ፖርታል እና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማተም እንደምትችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላቸው ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መሔድ ሳያስፈልጋችሁ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ Compliant የሚለውን በመጫን የቅሬታቸውን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

አገልግሎቱ በቅሬታችሁ ላይ ምላሽ ቅሬታቸውን ባቀረቡበት ተመሳሳይ አድራሻ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
#አኃዛዊ_መረጃ

674,823
በ2016 ዓ.ም ለ12ኛ ክፍል ፈተና የተቀመጡ

36,409 (5.4%)
ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች

1,363
አንድም ተማሪ ያላሳለፉ ትምህርት ቤቶች

9%
ፈተናውን ከወሰዱ 321,536 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ውስጥ ማለፍ የቻሉት

2%
ፈተናውን ከወሰዱ 353,287 የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ውስጥ ማለፍ የቻሉት

26.6%
በኦንላይን ለፈተናው ከተቀመጡ ማለፍ የቻሉ

29.76%
ዘንድሮ የተመዘገበው አማካይ ውጤት (Mean)

575 (ከ600)
በተፈጥሮ ሳይንስ የተመዘገበው ከፍተኛው ውጤት (በአዲስ አበባ ካቴድራል ት/ቤት)

538 (ከ600)
በማኅበራዊ ሳይንስ የተመዘገበው ከፍተኛው ውጤት (በአዲስ አበባ ኢትዮ ፓረንትስ ት/ቤት)

675 (ከ700)
በትግራይ ክልል የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት
(ከቓላሚኖ ልዩ ትምህርት ቤት)

2 ትምህርት ቤቶች
ሙሉ በሙሉ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ያሳለፉ
(እቴጌ መነን የሴት ተማሪዎች አዳሪ ት/ቤት እና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ት/ቤት)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Blum‼️

በዚ ሰአት ከBlum የተሻለ ኤርድሮፕ የለም

እኔ በግሌ ከኖትኮይንም ከዶግስም የተሻለ ይሆናል ብዬ የማስበው Blum ብቻ ነው

በተለያየ በብዙ አካውንት ስሩት ፤ በእርግጠኝነት ብዙ ነው የምታተርፉበት 😊

Blum ላልጀመራቹ  በዚ ጀምሩ👇👇👇

https://www.tg-me.com/blum/app?startapp=ref_JhjvJ1zEys

https://www.tg-me.com/blum/app?startapp=ref_JhjvJ1zEys‌‌
#Newsflash‼️

የኢትዮጵያ ጦር ካሁን በፊት ተቆጣጥሯቸው ከነበሩት ከዶሎ እና ከጋባሃሬይ ኤርፖርት በተጨማሪ የጌዲዎ ግዛት አየር ማረፊያን መያዙ ተነግሯል።

ይህ ጉዳይ የሶማሊያ መንግስት የግብፅ ወታደሮችን ወደ ድንበር አካባቢ ለመውሰድ መሰማቱን ተከትሎ መሆኑን ከጋርዌ ኦላይን ዘገባ ይጠቁማሉ።

@sheger_press
@sheger_press
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ከ6 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይቻላል።

ልክ እንዳለፉት ዓመታት ሁሉ በኔትዎርክ መጨናነቅ ምክንያት ውጤት ማየት ለማይችሉ ወንድም እህቶቻችሁ ውጤት በማየት የተለመደው ትብብራችሁን አድርጉ።

የአድሚሽን ቁጥር እና ስም በመላክ ተረዳዱ።

በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot

@sheger_press
@sheger_press
6:00 ሆኗል። ግን እየሰራ አይደለም።

ሁሉም የተማሪ ቤተሰቦች እና ተፈታኞች ተረጋግታቹ ጠብቁ።

መልካም ምኞት ለሁላችሁም

@sheger_press
እስካሁን አልተለቀቀም‼️

ውጤት በመጠባበቅ ላይ ያላቹህ ተማሪዎች ተረጋጉ 🙏

ማየት ከተጀመረ በኋላም ከፍተኛ የሲይስተም መጨናነቅ ስለሚኖር ብዙዎቻቹህ ምናልባት እስከ ነገ ጥዋት ድረስ ውጤት ላታውቁ ትችላላችሁ።

@sheger_crypto_tech
@sheger_crypto_tech
ውጤት እየታየ ነው

ደጋግማቹ ሞክሩት

ውጤት ማሳያ ግሩኘ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታችሁን ለማየት

የአድሚሽን ቁጥር እና ስም በመላክ ተረዳዱ።

በፖርታል 👉 https://result.eaes.et

በአጭር የፅሑፍ መልዕክት 👉 6284

በቴሌግራም ቦት 👉 https://www.tg-me.com/EAESbot

@sheger_press
@sheger_press
የገቢዎች ቢሮ ሁሉም የንግድ ተቋማት በአስገዳጅነት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት በሚታይ ቦታ እንዲሰቅሉ አዘዘ!

ግብር ከፋዮች ከዚህ ቀደም ንግድ ፍቃድ እንዲሰቅሉ እና " ደረሰኝ ሳይቀበሉ አይክፈሉ " የሚል ፅሁፎች በተቋማቸው ላይ እንዲለጥፉ አስገዳጅ የነበረ ቢሆንም አሁን ደግሞ በተጨማሪነት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ( ቲን) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ( ቫት) ሰርተፊኬት ቅጅ በሚታይ ቦታ እንዲለጥፉ ትዕዛዝ ተሰጥቷል።

መንግስት የታክስ አሰባሰብ ሂደትን በይበልጥ ለማሳለጥ ይረዳኛል ያለዉን አዳዲስ ስትራቴጂዎች እየወሰደ እንደሚገኝ ይታወቃል።በዚህም ሁሉም የንግድ ተቋማት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ( ቲን) እና የቫት ምዝገባ በተጨማሪነት ለጥፉ መባላቸው ካፒታል ያገኘችወው መረጃ ያሳያል።

ከአዲሱ የዉጪ ምንዛሪ ለዉጥ ጋር ተያይዞ መንግስት ከያዛቸው ስር ነቀል ለዉጦች መካከል የታክስ ዘርፉ አንደኛው መሆኑ ይታዉቃል። በዚህ በበጀት ዓመት በታክስ 1.15 ትሪሊየን ብር ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን ይህ ደግሞ የበጀት ዓመቱ ሲጀመር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከነበረው 502 ቢሊየን ብር አንፃር ከእጥፍ በላይ የጨመረ እንዲሆን አድርጓታል።

Via Capital

@sheger_press
@sheger_press
የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሹመት እንዳይሰጥ በትግራይ የፀጥታ ሀይሎች ምክር ቤት ታገደ

የትግራይ ፀጥታ ሃይሎች፥ ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ አዲስ ሹመት መስጠትም ሆነ ማውረድ እንዳይችል መታገዱን ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ ተናግረዋል።

ይህ እንዲሆን የተወሰነው በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር እና በደብረፂዮን ገ/ሚካኤል በሚመራው የህወሓት ቡድን መካከል የተፈጠረው ልዩነት እየሰፋ በመሄዱ እንደሆነ ተመላክቷል::

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ይህ ድርጊት የተፈፀመው ከሳምንት በፊት በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ጋሰራ ወረዳ ሲሆን፣አንድ የፖሊስ አባል አንድትን ኒቃብ የለበሰች እህት ላይ ከባድ የሆነ የበትር ድብደባ ሲያደርስባት ያሳያል‼️

ሴትየዋ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከተወሰደች በኋላ በዚህ መልኩ ደብድበዋት ከእስር ለቀዋታል።

በስርቆት ወንጀል ተሳትፋለች የሚሉ መረጃዎችም እየወጡ ነው።

ይህ አሰቃቂ ድርጊት ብዙ ወንድሞችና እህቶችን ያሳዘነ ድርጊት ነው።

የሰራችው ነገር ምንም ይሁን ምንም መጠየቅ ያለባት በህግና በህግ ብቻ ነው።

ጥፋቱ👉አንድ ሰው በህግ ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ወደ ህግ ማቅረብ እንጂ ድብደባ መፈፀም ወንጀል ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
እንኳን አደረሳቹ

ለመላያው ኢትዮጲያዊያን በሙሉ እንኳን ለአዲሱ አመት በሠላም አደረሳቹ አዲሱ አመት የሰላም፣ የፍቅር፤ የመተሳሰብ የአብሮነት፥ የደስታ እንዲሆንልሆ ኢትዮ መረጃ ከወዲሁ ምኞቱን ይገልፃል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ የሚመራው ኦሎምፒክ ኮሚቴ በ11 ባንኮች ያለውን ሂሳብ እንዳያንቀሳቅስ በፍ/ቤት ታገደ‼️

የኦሎምፒክ ተሳታፊ ብሄራዊ ፌዴሬሽኖችና በታዋቂ ግለሠቦች የተወከሉ የህግ ባለሙያዎች(ህጋዊ ጠበቆች) 
  ትናንት(ሐሙስ) በኢ.ፊ.ድ.ሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር፣በዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ እና በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ሥ/አ ቦርድ አባላት ላይ ክስ መመስረታቸው ተከትሎ፣በትናንትናው ዕለት በተጠቀሱት አካላት ላይ የቀረበውን የክስ አቤቱታ የመረመረውና የተመለከተው ፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ላይ የዕግድ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ገንዘብ ያንቀሳቅስባቸዋል ተብለው የተለዩ በሀገሪቱ የሚገኙ 11 ባንኮች ላይ ያለውን ገንዘብ(አካውንት) ከዛሬ ጳጉሜን 5/13/2016 ዓ.ም ጀምሮ ሌላ ውሳኔ እስኪተላለፍ ድረስ እንዳያንቀሳቅስ የዕግድ ትዕዛዝ ተላልፎበታል።

ፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በቀን 4/13/16 በቁጥር 320687 ባስተላለፈው የዕግድ ትዕዛዝ መሠረት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣በወጋገን ባንክ፣በአዋሽ ባንክ፣ በአቢሲኒያ ባንክ፣በዳሽን ባንከ፣በህብረት ባንክ፣በንብ ባንክ፣በአባይ ባንክ፣በግሎባል ባንክ፣በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ እና በዘመን ባንክ ያለው የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች(አካውንቶች)በከሳሽና በተከሳሾች መካከል ባለው ክርክር ላይ ፍ/ቤቱ ውሳኔ እስኪሠጥ ድረስ ሳይንቀሳቀሱ ታግደው እንዲቆዩ ትዕዛዝ ከመሠጠቱም ሌላ ውሳኔው ለሁሉም ባንኮች ዋና መ/ቤቶች ተልኮ እንዲያስፈፅሙ ያዛል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 19:31:52
Back to Top
HTML Embed Code: