Telegram Web Link
ከሸዋ አማራ የሚወጡ የአዉደ ግንባር መረጃዎችን በፍጥነት በታማኝነት የሚያደርስ ቻናል ላስተዋዉቃችሁ👇👇👇👇

https://www.tg-me.com/SNN_merja
https://www.tg-me.com/SNN_merja
ማይክ ሀመር በአፍሪካ ቀንደ ወቅታዊ ሁኔታ ለመምከር ወደ #ኢትዮጵያ እና #ኬንያ እንደሚመጡ ተጠቆመ፣ በብራሰልስ ከአውሮፓ ህብረት ጋርም እየመከሩ መሆኑ ተገልጿል
#
#የአሜሪካ መንግስት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ማይክ ሀመር በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ለመምከር ወደ ኢትዮጵያ እና ኬንያ እንደሚመጡ ተገለጸ።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ማይክ ሀመር በብራሰልስ፣ አዲስ አበባ እና ኬንያ ለአስር ቀናት ይቆያሉ።

ትላንት ነሃሴ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ሀመር #ብራስልስ የገቡ ሲሆን ዋነኛ አጀንዳቸውም በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ ከአውሮፓ ህብረት እና የአሜሪካ አጋር ከሆኑ ተቋማት ጋር መምከር ነው ተብሏል።

ሀመር #በናይሮቢ በሚኖራቸው ቆይታ ከኬንያ ባለስልጣናት ጋር በቀጠናው የጸጥታ ሁኔታ እንደሚመክሩ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው አትቷል።

ሀመር በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከአፍሪካ ህብረት እና ኢጋድ ባለስልጣናት ጋር በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ እንደሚመክሩ መስሪያቤቱ በመግለጫው አመላክቷል።

ኢትዮጵያን በተመለከተ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በመግለጫው እንዳስታወቀው ሀመር በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት ዙሪያ ከሁለቱ ተፈራራሚ አካላት ጋር ይመክራሉ ብሏል።

በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማስቻል አሜሪካ የፌደራል መንግስቱን እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለማገዝ አሁንም ቁርጠኛ ናት ያለው መስሪያቤቱ በመግለጫው #በአማራ እና #በኦሮምያ ክልል ግጭቶች ዙሪያ ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር እንደሚመክሩ ጠቁሟል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በጎንደር ከተማ የቀጠለው እገታ‼️

በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በአዘዞ ማርያምበር ቀበሌ ትናንት ከምሽቱ 1:30 ገደማ 4 ሰዎች ታግተው ተወሰደዋል‼️

ሁለቱ በመጠጥ ሽያጭ የሚተዳደሩ ሴቶች ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ ወንዶች ናቸው።

አንደኛው ከዚህ በፊት ፖሊስ የነበረና ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚሰራ ሰው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ባለቤቱ ገቢዎች የምትሰራ ግለሰብ መሆናቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press
የኢትዮጵያ አየር ሀይል የምስራቁን የአየር ክልል በንቃት እየጠበቀ እንደሚገኝ አስታወቀ‼️

- የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር ደግሞ የምስራቅ ዕዝ በተሟላ ወታደራዊ ዝግጁነት ላይ ይገኛል ብሏል‼️

ከሰሞኑ ግብፅ እና ሶማልያ በቀጠናው እያረጉት ያለውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር ሀይል የምስራቁን የአየር ክልል በንቃት እየጠበቀ እንደሚገኝ አስታውቋል።

በኢትዮጵያ አየር ሃይል የ3ኛው አየር ምድብ የተሰጠውን ሃገራዊ ግዳጅና ተልዕኮ ለመወጣት በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የአየር ምድቡ አዛዥ ኮሎኔል ደረጀ ቡሽሬ ገልፀዋል፡፡

አዛዡ የ3ኛው አየር ምድብ የሃገራችንን ብሎም የምስራቁን የአየር ክልል በንቃት እየጠበቀ የሚገኝ የሃገር መከታና መመኪያ የሆነ ምድብ ነው ያሉ ሲሆን "ወደፊትም ኢትዮጵያን ከውስጥም ይሁን ከውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ለመጠበቅ በላቀ የዝግጁት ደረጃ ላይ ይገኛል" ብለዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር የምስራቅ ዕዝ በተሟላ ወታደራዊ ዝግጁነት ላይ ይገኛል ብሏል።

"በተለያዩ ዘመናት ሀገራችንን ለመውረርና የሽብር ጥቃት ለመፈፀም የሚሞክሩ ሀይሎችን በመከላከል በመስዋዕትነት የተረከቡትን አደራ ለማስቀጠል እስከ ህይወት መስዋዕትነት ለመክፈል በተሟላ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ" ሲል መከላከያ አሳውቋል።

@sheger_press
@sheger_press
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለመቀጠር እስከ 1 ሚሊዮን ብር ጉቦ መጠየቁን ፥ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት "የሐሰት እና የስም ማጥፋት" ሲል አጣጣለ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መጋቢ ሐዲስ ዘለዓለም ምሕረቴ በዛሬው ዕለት በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫውም "ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም በዋዜማ ራዲዮ የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ላይ የተገለፀው መረጃ ማለትም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በተለያዩ አብያተክርስቲያናት ላይ ለመቀጠር የእጅ መንሻ ወይም ጉቦ እየጠየቀ ነው በማለት ያሰራጨው እና በውስጥ ደላሎች የቅጥር አገልግሎት እንደሚሰጥ እንዲሁም  ከሦስት መቶ ሺ ብር ጀምሮ እንደሚጠየቅ እና በአጠቃላይ የመልካም አገልግሎት ችግር እንዳለበት አድርጎ ያቀረበው መረጃ የሐሰት ስም ማጥፋት ነው " ማለታቸዉን  ከተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል።

አክለውም "ዋዜማ ራዲዮ ከላይ የተጠቀሰውን የሐሰት መረጃ በማስተላለፉ ለተቋሙ ያለውን ግልፅ ጥላቻ ነው ያሳየው ይህንን መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት ማለትም ከአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ ወይም  የሀገረስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅን ስለ ጉዳዩ ሳይጠይቅ ከላይ የተጠቀሱትን ብልሹ አሠራሮች ሊቀ ጳጳሱ እንደሚያውቁ አድርጎ መዘገቡ እራሱ ሆን ተብሎ ሀገረ ስብከቱን እና በጠቅላላው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ለመኮነን የተደረገ ነው።"በማለት በመግለጫው አስታውቀዋል።

በተጨማሪም ዋዜማ ራዲዮ ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም የሠራውን ዘገባ እርማት እንዲሰጥበት እንጠይቃለን ያሉ ሲሆን እርማት የማይሰጥበት ከሆነ ግን በሕግ መሰረት አስተዳደራዊ ፍትሕን ከመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን እንዲሁም ፍትሕን ከፍርድ ቤት እንደምንጠይቅ እንገልፃለን ብለዋል።

በመጨረሻም "በተሰጠው የሐሰት እና የተዛባ መረጃ ምክንያት የተሳሳተ ግንዛቤ የያዛችሁ መላው የሀገረ ስብከታችን አገልጋዮች እና ምእመናን እንዲሁም የቤተክርስቲያናችን የበላይ አመራር አካላት ሀገረስብከቱ እንደማንኛውም ተቋም ያሉበትን የአሠራር ክፍተቶችን ለማሟላት በርካታ የአሠራር ማሻሻያዎችን እያደረገ እንዲሁም ተጨማሪ ማሻሻያዎችን ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ላይ ስለሚገኝ ይህንን እውነታ እንድትረዱን በታላቅ አክብሮት ለመግለፅ እንወዳለን" በማለት በመግለጫቸው አሳውቀዋል።

ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል

ዳጉ ጆርናል

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሳሮን በቱርክ በድጋሚ ታስራለች!
በአካባቢው ያላችሁ እና ማገዝ የምትችሉ አግዟት ፣ ሌሎቻችሁ በፀሎታችሁ አስቧት 👏

@merkato_media
ጎንደር‼️

በጎንደር ከተማ የሚገኙ ከቀበሌ እስከ ክፍለ ከተማ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የመንግሥት የፀጥታ አካላት በከተማዋ ግጭት በማባባስ ሰዎችን በማሳገት ገንዘብ በመቀበል እና በህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ውስጥ  እጃችሁ አለበት ተብለው ከየቤታቸው እና መስሪያቤታቸው ዛሬ ጠዋት ታስረዋል። በተመረጡ ቦታዎችም የቤት ለቤት ፍተሻ ተካሂዷል።

@sheger_press
@sheger_press
ጃዋር መሀመድ እንዲህ ይላል 👇

ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ በፍትሃዊነት የመጠቀም መብታችንን ለምግታት እንደምትዝተው ሁሉ፣ ቀጥተኛ ወታደራዊ እርምጃን መውሰድ አትችልምም፤ አትፈልግም።

ይልቁንም ውሃዉን ለማልማት አቅም የሚነሱን እና ትኩርታችንን የሚበታትኑ ሶስት መሰረታዊ ስልቶችን ተጠቀማለች፡፡

እነዚህም፣ በውስጣዊ ግጭቶች መወጠር፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ማጋጨትና አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለአባይ ልማት የሚውል ገንዘብ እንዳይሰጡን ማግባባት።

አሁን ላይ በራሳችን ተነሳሽነት በውስጣዊ ጦርነት እየታመስን እንዲሁም ከጎረቤት ሀገራት ጋርም አምባጓሮ ውስጥ ስለገባን ለግብጽ ሰርግና ምላሽ ሆኖላታል ማለት ይቻላል። ሰሞኑን የምታደርገው ዛቻም ከዚሁ የኢትዮጲያ ተጋላጭነት የመነጨ ነው።

መፍትሄውም ዛቻውን ለማስተንፈስ ውስጣዊ ግጭቶችን በሰላም መፍታት እና ከጎረቤቶቻችን ጋር የተፈጠረውን እሰጣገባም ማርገብ ወሳኝ ይሆናል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ባለፉት አመታት በተደጋጋሚ ስጽፍና፣ ስናገር እና ምክረ-ሀሳብ ስለግስ ቆይቻለሁ።

@sheger_press
@sheger_press
በጎንደር ከተማ በታጣቂዎች ለተፈፀመው አስነዋሪ ድርጊት የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል፡- የአማራ ክልል የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ
***

በጎንደር ከተማ በታጣቂዎች ለተፈፀመው አስነዋሪ ድርጊት የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ የአማራ ክልል የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል።

በጎንደር ከተማ የተፈፀመው አስነዋሪ እና አሳዛኝ ድርጊት ሆን ተብሎ እና ታቅዶ የተፈጸመ የጠላት አጀንዳ መሆኑን በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ደሳለኝ ጣሰው ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው ከቀናት በፊት በጎንደር ከተማ በአንዲት ህፃን ልጅ የተከሰተውን አሳዛኝ ታሪክ አስታውሰው፤ ገንዘብ ለመቀበል ባለው ሂደት ሕይወቷ ማለፉ ማህበረሰቡን ብሎም የክልሉን መንግስት ያሳዘነ ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ከፖለቲካ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ሆኖም ግን የኢኮኖሚ አቅም አላቸው ተብለው የሚታሰቡ ነዋሪዎችን ዒላማ በማድረግ፣ ከህፃን እስከ አረጋዊ ባሉ ነዋሪዎች ላይ የሚፈፀሙ የዕገታ ድርጊቶች የማህረሰቡን አብሮ የመኖር መስጋብር እያሳሱት መሆኑን አንስተዋል፡፡

የአማራ ክልል እሴት ባልሆነ መልኩ የኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘት እንደዚህ አይነት እኩይ ተግባር እየተፈጸመ ነው ብለዋል፡፡

በክልሉ የሚፈፀሙ ዘረፋ፣ እገታ እና ግድያ በታጣቂ ኃይሉ እንደሚፈፀሙ ማስረጃ እና መረጃዎች እንዳሉ የገለፁት ኃላፊው፤ የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ የኦፕሬሽን ዕቅድ እያዘጋጀ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ህዝቡም አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ የቢሮ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

ቴሌግራምን በመጠቀም ብቻ በርካቶች በርካታ ብር በማግኘት ላይ ናቸው።

እናንተም ይህን ቻናል በመቀላቀል ሙሉ ትምህርት ማግኘት ትችላላቹ።

Join us👇👇👇👍
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
https://www.tg-me.com/+fzeZ2gn56UE3NTI0
ደብረጺዮን ገ/ሚካዔል የሚመሩት የሕወሓት ቡድን የፕሪቶሪያውን የግጭት ማቆም ስምምነት ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ከፌደራሉ መንግሥት ጋር ለመስራት ተቸግሬያለሁ ሲል ትናንት ማምሻውን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስታውቋል።

ባሁኑ ወቅት ያለው ዋናው ልዩነት፣ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ የሚያጠነጥን እንደኾነ ሕወሓት ገልጧል።

በፌደራል መንግሥቱ ዘንድ የሚታየው አካሄድ፣ ትግራይን የመከፋፈል ወይም ወደተመቸው አቅጣጫ የመውሰድ ሁኔታ ነው በማለት ሕወሓት ከሷል።

ሕወሓት፣ በትግራይ እና አማራ ክልል ድንበሮች ላይ የሕዝብ ስብጥር የመቀየር ሙከራዎች እየተደረጉ ነው በማለትም በመግለጫው ላይ ወቀሳ አቅርቧል።

@sheger_press
@sheger_press
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ እንደገና መቀስቀሱን ከዋሪዎች መስማቱን ጠቅሶ ዶቼቬለ ዘግቧል።

ትናንት ከቀኑ 11 ሰዓት  ጀምሮ በመተማ ከተማ በተለያዩ አቅጣጫዎች በሁለቱ ወገኖች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ነዋሪዎች መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።

በመተማ ከተማ  ዙሪያ ውጊያ የተጀመረው ሰኞ'ለት ሲኾን፣ የፋኖ ታጣቂዎችም ከተማዋን ለሁለት ቀናት ከተቆጣጠሩ በኋላ ያለተኩስ ልውውጥ ለቀው መውጣታቸው ይታወሳል።

የፋኖ ታጣቂዎች ከማክሰኞ ጀምሮ ሽንፋ የተባለችውን ሌላ የወረዳ ከተማ ይዘው እንደሚገኙ ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል።

@sheger_press
@sheger_press
የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ሽንኩርት ከታንዛንያ ማስገባቱን አስታወቀ‼️

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮሽች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት መጪው ዘመን መለወጫ በዓል ገበያው ላይ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር ከክሎች ባለፈም ከታንዛኒያ ሽንኩርት ማስገባታቸውን ተናግረዋል፡፡
በተለይ የእሁድ ገበያ ላይ ከሸማች ህብረት ስራ ማህበራት ጋር በተያያዘ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን እና ታንዛኒያን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት ሽንኩርት ወደ ከተማዋ ማስገባት መቻላቸውን አንስተዋል።
በቅርቡ ለተፈጠረው የሽንኩርት መወደድ ምክያትም በሽንኩርት ማሳዎች ውስጥ ውሃ ተኝቶበት እንደሆነ ተናግረው ከኦሮሚያ ከሶማሌ እንዲሁም ከሌሎች ክልሎችም ጭምር ምርት መግባቱን ተናግረዋል፡፡
ቢሮው ሽንኩርትን ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እና ለሸማቾች ህብረት ስራ ማህበራት በጋራ ስራዎችን መሰራቱንም ገልጧል፡፡

ዳይሬክተሩ አላስፈላጊ የገበያ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎችን የመከታተል ስራዎች መሰራታቸውን እና በተለይ ደግሞ ንግድ ፍቃድ ኖሯቸው እየሰሩ ባሉ አካላት ላይ ከፈቃድ ማስጠንቀቂያ እስከ ፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ድረስ እየተሰጠ መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

በዚህም ለበዓሉ የሽንኩርት፣ የእንቁላል፣ የዘይት፣ የዱቄት፣ የቁም እንሰሳት ፣ የቅቤ፣ የጤፍ ምርቶች ላይ ከኦሮሚያ ክልል እንዲሁም ከአዲስ አበባ የንግድ ስራዎች ድርጅትና ከህብረት ስራ ኮምሽን ጋር በመቀናጀት ተመጣጣን በሆነ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸው ገልጸዋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አሜሪካ የኦነግ ከፍተኛ አመራሮች ከዕስር መፈታትን እንደምትደግፍ ገለጸች

አሜሪካ የኢትዮጵያ መንግስት የ #ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራሮችን ከዕስር መፍታቱን እንደምትደግፍ አስታወቀች።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍርካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል በወጣው መግለቻ አሜሪካ፤ “" ግጭት ለማስቆም እና ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚደረጉ ድርድሮችን ለመደገፍ ዝግጁ" መሆኗን አረጋግጣለች።

ትላንት አመሻሹን የኦነግ ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት አብዲ ረጋሳ፣ ለሚ ቤኛ፣ ዳዊት አብደታ፣ ሚካኤል በረን፣ ኬነሳ አያና፣ ገዳ ኦልጂራ እና ገዳ ገቢሳ ከእስር ተፈተዋል። የፓርቲው አመራሮች ከ2012 እና 2013 ዓ/ም ጀምሮ በኦሮሚያ ፖሊስ ተይዘው በዕስር ላይ ቆይተዋል።

አመራሮቹ በፌደራል ፍርድ ቤት በተደጋጋሚ እንዲፈቱ ትዕዛዝ ቢሰጥም ተፈጻሚ ሳይሆን ለአራት አመታት በዕስር ላይ መቆየታቸው ይታወቃል። አዲስ ስታንዳርድ በሐምሌ ወር ርዕሰ አንቀጽ የአመራሮቹ ከህግ አግባብ ውጭ ታስሮ መቆየትን በማውገዝ እስሩ በ #ኢትዮጵያ የፍትህ ስርዓት ላይ አደጋ ነው ሲል ገልጾታል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰኞ ይፋ ይደረጋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ሰኞ ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ/ም እንደሚገለጽ አሳውቋል።

የዘንድሮው ብሔራዊ ፈተና በቅይጥ ማለትም በወረቀት እና በኦንላይን መሰጠቱ ይታወሳል።

Via Tikvah

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ትግበራ መስከረም 1 ሊጀምር ነው

- ለደሞዝ ጭማሪው ከ91.4 ቢልዮን ብር በላይ ተመድቧል

(መሠረት ሚድያ)- የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን መምጣት ተከትሎ በመንግስት ቃል ከተገቡት ጉዳዮች አንዱ የሆነው የደሞዝ ጭማሪ ከመስከረም 1/2017 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና ትክክለኛነቱ በኢትዮጵያ ቼክ የተረጋገጠ አንድ የፋይናንስ ሚኒስቴር ደብዳቤ ጠቁሟል።

ባለፉት ሰአታት ውስጥ በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ይህ የፋይናንስ ሚኒስቴር ደብዳቤ ነው የተባለ ምስል እንዲሁም አዲሱን የደሞዝ ስኬል ያሳያል ተብሎ የተገለፀ ስሌት በስፋት ሲያጋሩ ቆይተዋል።

ደብዳቤው በሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ የተፈረመ እንደሆነ የሚያሳይ ሲሆን ለጠ/ሚር ቢሮ ተልኮ ሲቪል ሰርቪስ ደግሞ ኮፒ እንደተደረገ ይገልፃል።

ኢትዮጵያ ቼክ የደብዳቤውን እና የደሞዝ ስኬሉን ትክክለኛነት ያረጋገጠ ሲሆን ለታሰበው የደሞዝ ጭማሪ ከ91.4 ቢልዮን ብር በላይ እንደተመደበ እና ጭማሬው ከመስከረም 1 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን ይገልፃል።

ይህ በፋይናንስ ሚኒስቴር እና በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ተጠንቶ የቀረበው የደሞዝ ጭማሪ በሚኒስትሮች ምክር ቤት እንዲፀድቅ መቅረቡም ተመላክቷል።

በአዲሱ ስሌት መሠረት ነባር ደሞዛቸው በጣም ዝቅተኛ የነበረው እና 1,100 ብር ያገኙ የነበሩ መጠኑ በ332 ፐርሰንት ጨምሮ 3,660 ብር እንደሚሆን ያሳያል።

በሌላ በኩል ደሞዛቸው ከፍተኛ የነበረው እና 20,468 ብር ያገኙ የነበሩ መጠኑ በ5 ፐርሰንት ጨምሮ 2,1491 ብር እንደሚሆን ይጠቁማል።

Via ኢትዮጵያ ቼክ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 23:44:10
Back to Top
HTML Embed Code: