Telegram Web Link
Forwarded from Sheger Press️️
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዋን ራይድን ያልተገደበ ዕለታዊ፣ ሳምንታዊ ወይም ወርሃዊ ጥቅሎችን በቴሌ ብር በመግዛት ወጪ ቆጣቢ በሆኑ አማራጮች ተጠቃሚ ይሁኑ።

መተግበሪያውን ያውርዱ | ይመዝገቡ| ቤተሰብ ይሁኑ!

𝐃𝐫𝐢𝐯𝐞𝐫 𝐀𝐩𝐩https://shorturl.at/bdyFO

𝐏𝐚𝐬𝐬𝐞𝐧𝐠𝐞𝐫 𝐀𝐩𝐩https://shorturl.at/lJLZ6

የማኅበራዊ ትስስር ድኅረ ገጾቻችንን ይቀላቀሉ

Facebook: https://www.facebook.com/rideinone

Instagram: https://www.instagram.com/rideinone

Telegram Group: http://www.tg-me.com/rideinone9744

TikTok: https://www.tiktok.com/@rideinone

የናንተ የሆነውን ዋን ራይድን ምርጫዎ ያደርጉ በአንድ ይጓዙ! ዋን ራይድ
ባንክ ተዘርፏል ተባለ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሬማ ቅርንጫፍ በታጠቁ ሃይሎች ከ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ዝርፊያ እንደተፈጸመበት ተገለጸ

በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን ሚዳ ወረሞ ወረዳ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሬማ ቅርንጫፍ ትናንት ሰኔ 06 ቀን 2016 ዓ.ም በአካባቢዉ ይንቀሳቀሳሉ በተባሉ የታጠቁ ሀይሎች ዝርፊያ መፈፀሙን የሚዳ ወረሞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሠይድ ኢብራሂም ገልፀዋል ፡፡

የታጠቁት ሃይሎች ከዚህ በፊት ለአጎራባች መርሃቤቴ ወረዳ የተላከዉን ሰዉ ሰራሽ የአፈር ማዳበሪያ አስገድደዉ በሚል ክስ የቀረበባቸው ሲሆን አሁን ደግሞ ከኢትዮጽያ ንግድ ባንክ ሬማ ቅርንጫፍ ከ 2 ሚሊዮን ብር በላይ መዘረፉን ተናግረዋል ሲል የዘገበው የወረዳው ኮሙኒኬሽን ነው፡፡

በሌላ በኩል ታጣቂዎቹ ብሩን የወሰዱት አካውንታችን ለምን ታገደ በሚል ቁጣ እንደሆነም ከአካባቢ ምንጮች ተሰምቷል።(wasumohammed)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ሱዳን ውስጥ ከነበሩ ቀሪ የጉሙዝ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉሕዴን) ታጣቂዎች እና ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ነጻነት ንቅናቄ (ቤሕነን) አመራሮች ጋራ በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መግባባት ላይ እንደደረሰ የክልሉ ዜና አውታር ዘግቧል።

የክልሉ መንግሥት ካኹን ቀደም በአገር ውስጥና በውጭ ይንቀስቀሱ ከነበሩ ከቤንሻንጉል ሕዝብ ነጻነት ንቅናቄ እና ከጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ አመራሮች ጋር የጋራ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረሙ ይታወሳል።

ሱዳን ውስጥ ይኖሩ ነበር የተባሉትና ክልሉ መንግሥት ጋር ስምምነት የተፈራረሙት የጉሙዝ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ታጣቂዎች ብዛት ስንት እንደኾነ ዘገባው አላመለከተም።

@ethio_mereja_news
ተቃዋሚው ኦብነግ በተያዘው ወር አጋማሽ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በድጋሚ በሚካሄደው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የምርጫ ቅስቀሳ እያደረገ መኾኑን አስታውቋል።

ኾኖም ደጋፊዎቹ መታወቂያ ለማግኘት ወይም ለማደስ አኹንም ችግሮች እየገጠሟቸው እንደኾነ ፓርቲው ገልጧል።

ተቃዋሚ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች ለሚያነሷቸው ቅሬታዎች ምርጫ ቦርድ ምላሽ እየሰጠ መኾኑን የገለጠው ፓርቲው፣ ቦርዱ በጅግጅጋ ፍትሃዊ ምርጫ ለማካሄድ ቁርጠኛ መኾኑን አሳይቷል በማለት መስክሯል።

በጅግጅጋ በድጋሚ ምርጫ የሚካሄደው፣ ቦርዱ በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተገኘውን የምርጫ ውጤት በመሰረዙ ነው። ኦብነግ፣ በክልሉ የተካሄደው የድምጽ ሰጪዎች ምዝገባ ከፍተኛ ችግር ታይቶበታል በማለት ከምርጫው ራሱን ማግለሉ አይዘነጋም።

@sheger_press
በፋኖ ታጣቂዎች ውስጥ የመሪነት ቦታ አላቸው የሚባሉት እስክንድር ነጋ፣ የፋኖ ታጣቂዎች ከመንግሥት ጋር ለመደራደር ከውሳኔ አልተደረሰም በማለት ለቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ፕሮግራም ተናግረዋል።

በአማራ ክልል በተለያዩ ዞኖች የሚንቀሳቀሱ የፋኖ ቡድኖችን ለማዋሃድ እንቅስቃሴ እየተደረገ እንደኾነና የውህደቱ ሂደት ሲጠናቀቅ ከመንግሥት ጋር ድርድር የማድረግና ያለማድረግ ጉዳይ ውሳኔ እንደሚያገኝ እስክንድር ገልጸዋል።

@ethio_mereja_news
ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው አማጺ ቡድን በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ ግንቦት 25 ፈጸመው በተባለ "ማንነት ተኮር" ጥቃት ከ20 በላይ ንጹሃን እንደተገደሉ ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል።

በክልሉ የተለያዩ ዞኖች ሰሞኑን በመንግሥት ወታደሮችና አማጺው ቡድን መካከል ተከታታይ ውጊያዎች እየተካሄዱ ስለመኾኑ ዋዜማ ከምንጮቿ ተረድታለች።

በቄለም ወለጋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከፍተኛ ውጊያ እየተካሄደ መኾኑን፣ ነዋሪዎችም ከቤት ለመውጣት እንደተቸገሩና ውጊያው በተለይ የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ በሚገኝበት ሰዮ ወረዳ እየተካሄደ እንደኾነ ተናግረዋል።

በምስራቅ ወለጋ ዞን ቢሎ ቦሼ፣ ሌቃ ዱለቻ እና ኑኑ ቁምባስን ወረዳዎችም በተለይ የመከላከያ ሠራዊት ካምፖች በሚገኙባቸው ጅማቴ እና አዳሚን በተባሉ አካባቢዎች ከባድ ውጊያዎች እየተካሄዱ እንደኾነ ተሰምቷል።

በምዕራብ ሸዋ ዞን ግንደበረትና ጀልዱ ወረዳዎች እንዲኹም በሰሜን ሸዋ፣ በጉጂ፣ በምሥራቅ ሸዋና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞኖች የተለያዩ ወረዳዎች ግጭት ሲካሄድ መሰንበቱ ታውቋል።

@ethio_mereja_news
News‼️

ላለፉት በርካታ አመታት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ከመንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተበድረው ያልከፈሉት 900 ቢሊየን የሚሆን ብርን የገንዘብ ሚኒስቴር እንዲወርስ መወሰኑን ሸገር ከዋዜማ ሁነኛ ምንጮቿ ሰምታለች።(wazema)

@sheger_press
#NEWSALERT

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 37 ቢሊየን ብር የካፒታል ማሳደጊያ እንዲሰጠው ተወሰነ‼️

የካፒታል ማሳደጊያ ገንዘቡ ከአለም ባንክ ይገኛል ተብሏል

ዋዜማ- መንግስታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሁን ካለው 43 ቢሊየን ብር ካፒታል በተጨማሪ ከ37.1 ቢሊየን ብር በላይ(650 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር) የካፒታል ማሳደጊያ ገንዘብ እንዲሰጠው ተወሰነ።

ውሳኔውም የንግድ ባንኩን አጠቃላይ ካፒታል ከ80 ቢሊየን ብር በላይ የሚያደርገው ሲሆን፣ይህም ከሌሎች ከግል ባንኮች አንፃር ያለውን የበላይነት እጅግ ያገዝፈዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካፒታል እንዲያድግ የተወሰነው ትላንት ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ/ም የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባደረገው ስብሰባ ሲሆን ፣ በዚህም ምክር ቤቱ ፣ በባንኩ የሪፎርም እና የካፒታል ማሳደጊያ ዕቅድ ላይ መምከሩን ገልጾ ፣ የባንኩን ካፒታል ለማሳደግ በሙሉ ድምጽ መወሰኑም ታውቋል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በመግለጫው ለባንኩ የሚሰጠውን የካፒታል ማሳደጊያ ገንዘብን ያልገለጸ ሲሆን ፣ ዋዜማ የካፒታል ገንዘቡ ከሚተላለፍበት ከገንዘብ ሚኒስቴር ምንጮቿ ባገኘችው መረጃ ለመንግስታዊው ባንክ የሚሰጠው የካፒታል ማሳደጊያ ገንዘብ ከ37 ቢሊየን ብር በላይ መሆኑን አረጋግጣለች።

የዋዜማ ምንጮች አክለው እንደገለጹትም የመንግስታዊውን ባንክ ካፒታል በዚህ ደረጃ ለማሳደግ የተፈለገበት አንዱ ምክንያት ኢትዮጵያ የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ገበያ እየከፈተች በመሆኑ መንግስታዊውን ባንክ ጠንካራና ተወዳዳሪ አድርጎ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖም በመገኘቱ ነው።

የካፒታል ማሳደጊያው ገንዘብም ከአለም ባንክ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮቻችን ነግረውናል።

የኢትዮጵያ መንግስት ከአለም ባንክ እና ከአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም(አይ ኤም ኤፍ) ጋር እያደረገ ባለው ድርድር የሀገሪቱን የፋይናንስ ተቋማት ማጠናከር የሚለው አንዱ አጀንዳ በመሆኑ ፣ ለንግድ ባንክ የሚገኘው የካፒታል ማሳደጊያ ገንዘብም ኢትዮጵያ ከአለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር የምትፈራረማቸውስምምነት አካል መሆኑንም ተገንዝበናል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ከሰሞኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2017 ዓ/ ም በጀትን በንባብ ባቀረቡበት ወቅት : አለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ከኢትዮጵያ የሚፈልጓቸውን ብር ማዳከም አይነት ፖሊሲዎችን ሀገሪቱ በቅርቡ አትተገብርም ማለታቸው ከእነ አለም ባንክ ጋር እየተደረገ ያለውን ድርድር ያከተመለት ቢያስመስለውም ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከአለም ባንክ በሚገኝ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የካፒታል ማሳደጊያ ገንዘብ ላይ ከውሳኔ መድረሱ የሀገሪቱን እና የገንዘብ ተቋማቱን የድርድር አዝማሚያ አመላካች ሆኗል።

በከፍተኛ ደረጃ ካፒታሉ እንዲያድግ የተወሰነለት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኢትዮጵያ ውስጥ በሰጠው ብድርም በሰበሰበው ቁጠባም በእያንዳንዳቸው አንድ ትሪሊየን ብር ያለፈ ብቸኛ የኢትዮጵያ ባንክ ነው። [ዋዜማ]

@sheger_press
@sheger_press
ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

@ethio_mereja_news
ኑሮ የከበዳቸው የመንግሥት ሠራተኞች የምሳ ሰዓትን በቤተ እምነቶች እያሳለፉ መሆኑ ተነገረ‼️
👉የቤት ኪራይ መክፈል ያልቻሉ ተደብቀው ቢሮ ውስጥ ያድራሉ ተብሏል።

መንግሥት የሚከፍላቸው ወርኃዊ ደመወዝ አልበቃ ያላቸው የመንግሥት ሠራተኞች የምሳ ሰዓታቸውን ወደ ቤት እምነቶች በመሄድ፣ እንዲሁም ቤት ተከራይተው መኖር የማይችሉት ደግሞ ቢሮ ውስጥ ተደብቀው እንደሚያድሩ ተገለጸ፡፡

በ2010 ዓም ተሻሽሎ ወደ ሥራ ገበቶ የነበረው ባለ 106 አንቀጽ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅ፣ ከስድስት ዓመታት አገልግሎት በኋላ፣ በ160 አንቀጾች ተዋቅሮ በረቂቅ አዋጁ ላይ ውይይት እየተደረገበት ነው፡፡

ለመንግሥት መሥሪያ ቤት ኃላፊዎች የበዛ ሥልጣን የሚሰጥ፣ ለሠራተኞች ችግር ደግሞ መፍትሔ የማያመጣና ተቋማዊ አሠራርና አደረጃጀት ላይ ብቻ ያተኮረ ነው የሚል ትችት በረቂቅ አዋጁ ላይ ቀርቧል፡፡ የመንግሥት ሠራተኛውን ሕይወት የሚቀይር ሥራ እንጂ አዋጅ ማውጣት ብቻ አገርን አይቀይርም የሚሉ ድምፆችም ተሰምተዋል፡፡

ለመንግሥት ሠራተኞች የሚከፈለው ደመወዝ አነስተኛና ሊያኖር የማይችል ከመሆኑም በላይ፣ በበርካታ የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት ደመወዝ መክፈል ተስኗቸው ሠራተኞች ለወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው መቆየታቸውን፣ እንዲሁም በአንዳንድ ክልሎች ደግሞ ከሚቀጥሉት ዓመታት በጀት ተበድረው ደመወዝ እየከፈሉ መሆናቸው በተደጋጋሚ ሲነገር ይደመጣል፡፡

በረቂቅ አዋጁ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ የሰው ሀብት ሥራ አመራር ድጋፍና ክትትል ቡድን መሪ አቶ አብርሃም ደግፌ በሰጡት አስተያየት፣ በከተማ አስተዳደሩ 70 ያህል የመንግሥት ተቋማት ላይ ክትትል እንደሚያደርጉና ሥልጠና እንደሚሰጡ ጠቅሰው የሠራተኛው ሕይወት እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡

በከተማ አስተዳድሩ አንድ ከፍተኛ የሚባል ባለሙያ ያልተጣራ ደመወዙ 9,056 ብር መሆኑን ጠቅሰው፣ ‹‹ከዚህ ግብር ተከፍሎበት በእጁ የሚደርሰውን ገንዘብ አስልታችሁ ድረሱበት፤›› ሲሉ ተሳታፊዎችን ጠይቀዋል፡፡ በዚህ ደመወዝ የቤት ኪራይ የከተማዋ ጫፍ እንኳ ቢኬድ 10,000 ብር መድረሱን፣ ነገር ግን ይህ ከፍተኛ ባለሙያ ሙሉ ደመወዙን ለቤት ኪራይ ላድርግ ቢል ገንዘቡ እንደማይበቃው አስረድተዋል፡፡

በዚህ ሁኔታ ላይ ያለ አንድ ሠራተኛ የተሻለ አገልግሎት መስጠት ይቻላል ወይ?  ተፈጥሯዊ ሁኔታውስ በራሱ ይፈቅድለታል ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ይህ ችግር ደመወዝ በመጨመርም ይፈታል ብለው እንደማያስቡ ገልጸው፣ በሌሎች አማራጮች እንዲጠቀም ቢደረግ ችግሩ ሊቀል ይችላል እንጂ 2,000 ብር ቢጨመር እንኳን ሕይወቱ ላይ ለውጥ እንደማያመጣ ተናግረዋል፡፡ ‹‹በዚህም የተነሳ ሠራተኞች አንዳንዴ ቢሮ መጥተው ያለቅሱብናል፣ ምሳ  የምንበላበት የለም በማለት በግልጽ ይናገራሉ፤›› ብለዋል፡፡

ገንዘብ አልበቃቸው ያሉ የመንግሥት ሠራተኞች በምሳ ሰዓት ወደ ቤተ እምነቶች ሄደው እንደሚያሳልፉ አስረድተዋል፡፡ የመንግሥት ሠራተኛው ታማኝ ግብር ከፋይ ቢሆንም፣ ነገር ግን የሠራተኛውን ሕይወት የሚቀይር ነገር እስካልመጣ ድረስ በሚፈለገው ደረጃ አገልግሎት ሊሰጥ እንደማይችል ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሰሎሞን ይልማ፣ ‹‹የረቂቅ አዋጁን መዘጋጀት የሰማ የመንግሥት ሠራተኛ የደመወዝ ጭማሪ አለ የሚል አዝማሚያ እየሰማን ነው፤›› ብለዋል፡፡ የመንግሥት ሠራተኛው የረቂቅ አዋጁን ዝርዝር የማየትና የመስማት ፍላጎት እንደሌለው ጠቅሰው፣ ‹‹አዋጁ ቶሎ ተዘጋጅቶ ሠራተኛው የሚጠቀምበት አሠራር ካልተዘረጋ በቀጣይ ከሠራተኛው ጋር የምንጋፈጠው እኛው ነን፤›› ብለዋል፡፡ የመንግሥት ሠራተኛው ተስፋ መቁረጡንና ችግር ውስጥ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ሰሎሞን፣ ‹‹አሁን ስለአዋጁ ወይም ዝርዝር እንድናወራለት ፍላጎት የለውም?›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ውስጥ የሚሠሩና ደንብ የሚቆጣጠሩ ከ6,500 በላይ ኦፊሰሮች በወር 3,934 ብር እየተከፈላቸው ለአሥር ዓመታት በተመሳሳይ ደመወዝ እያገለገሉ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በዚህ የተነሳ መሄጃ እያጡ ቢሮ ምቹ ሁኔታ አለ በሚል እየተደበቁ የሚያድሩ አሉ ብለዋል፡፡ በመሆኑም የመንግሥት ሠራተኞች መነሻና መድረሻ ደመወዝ ሊስተካከል ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ዳይሬክተር አቶ ካሳየ አረጋ፣ ሠራተኞች በተደጋጋሚ እየለቀቁ ዓመቱን በሙሉ ቅጥር ሲፈጸሙ እንደሚውሉ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ነገር ግን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አገልግሎት ለመስጠት የተሻለ አደረጃጀትና ባለሙያ፣ ቢቻልም የሥራ አስፈጻሚው የመንግሥት አካል ውስጥ ያለውን ባለሙያ ሊገዳደሩና ሊጠይቁ የሚችሉ፣ ለቋሚ ኮሚቴዎች የተሻለ ድጋፍና ሙያ ያላቸው ሠራተኞች ቀጥረን ልንሠራ ይገባል፤›› ብለዋል፡፡

‹‹አልቻልንም ባለሙያም የለም፣ ጉዳዩ በደንብ መታየት አለበት፤›› ያሉት ዳይሬክተሩ፣ አዋጅ በወጣ ቁጥር ሠራተኛው ተስፋ የሚያደርግበት ድንጋጌ እየገባ ነገር ግን ለዓመታት ሳይተገበር ቆይቶ እንደገና እንዲሻሻል መምጣቱ በቅጡ ሊጤን ይገባል ብለዋል፡፡ 

የቤት ሠራተኛ ወርኃዊ ደመወዝ ከ2,500 ብር ላይ ባለፈበት በዚህ ጊዜ አንድ መንግሥት የፅዳት ሠራተኛ በ1,300 ብር መቅጠር የሰብዓዊ መብት ጥሰት አይሆንም ወይ ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ በመሆኑም አሁንም ወደፊት ታይቶ የሚባለው ነገር ቀርቶና ያለው ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ ገብቶ፣ ታች ያለው ሠራተኛ ዜጋ በመሆኑ ችግሩ ሊታይለት ይገባል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና የሕጎች ሕገ መንግሥታዊነት ዳይሬክተር አቶ ሙለዬ ወለላው፣ የመንግሥት ሠራተኛው ሀቀኛና ታማኝ ግብር ከፋይ ሆኖ እያለ ለተለያዩ ዓይነቶች የታክስ ግዴታዎች ተገዥ መደረጉን፣ ለአብነትም ሠራተኛውን እንዲጠቅም ተብሎ ለትራንስፖርትና ለቤት ኪራይ የሚከፈል ገንዘብ ጭምር ግብር እየተከፈለበት እየተበዘበዘ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ የሰው ሀብት ክትትል ድጋፍና ኦዲት ዳይሬክተር አቶ መላኩ ተመስገን በሰጡት አስተያየት፣ አዋጆች እየወጡ ቁልፍ ጉዳዮች በመመርያ ይታያሉ እየተባሉ ነገር ግን መመርያ ሳይወጣና በውስጡ ያለው ድንጋጌ ሳይፈጸም ጊዜው ደርሶ እንደገና እንደሚሻሻል አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ተወዳዳሪ ባለመሆኑ ሠራተኞችን መሳብና ማቆየት እንደማይቻልና አንዳንዶችም ‹‹መሄጃ አጣን ብለው የተቀመጡ መሆናቸውን›› የተናገሩት አቶ መላኩ፣ እነዚህ ሠራተኞች እንዴት አገልግሎት ማሻሻል ይችላሉ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በሰጡት ምላሽ፣ በአዲስ አበባ ያለው ክፍያ የፌዴራል ተቋማት ከሚከፍሉት ይሻላል ብለዋል፡፡ ነገር ግን በሁለቱም የሚከፈለው ግን የኑሮ ሁኔታን ለመቋቋም የሚያስችል አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ 

‹‹ብዙውን ጊዜ ትኩረት የሚሰጠው የመጨረሻ ውጤት ላይ እንጂ ደመወዝ እዚህ ደረጃ ድረስ እንዲወርድ ያደረገው ምንድነው የሚለው በሚገባ አይታይም፡፡ አሁን ኃላፊነት ላይ ያለን ሰዎች ነን ወይ በዚህ ጉዳይ ላይ መጠየቅ ያለብን?›› ሲሉ ተሳታፊዎችን ጠይቀዋል፡፡
#ሪፖርተር

@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ወደ ምትገኘው ነቀምቴ ከተማ በሣምንት ሦስት ቀናት በረራ መጀመሩን አስታወቀ።

ከነቀምቴ ከተማ በ35 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በ1.3 ቢሊዮን ብር የተገነባው የጉዲና ቱምሳ አየር ማረፊያ ዛሬ እሁድ ሲመረቅ ከአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በተጨማሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝ እና የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ ተገኝተዋል።

@ethio_mereja_news
ደረሰኝ ካልያዙ ንብረቶ ሊወረስ ነው🤔

መንግሥት ባለፈው ሳምንት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበው "የንብረት ማስመለስ" አዋጅ፣ ከውጭ በተላከላቸው ገንዘብ ሃብት ያፈሩ ዜጎች ገንዘቡን የተረከቡበትን ደረሰኝ ለፍርድ ቤት አቅርበው ካላረጋገጡ መንግሥት ንብረታቸው እንዲወረስ ሥልጣን የሚሰጥ እንደኾነ ሪፖርተር ዘግቧል።

ማንኛውም ሰው ሊታወቅ ከሚችል ገቢው በላይ ሃብት አፍርቶ የምንጩን ሕጋዊነት ማረጋገጥ ካልቻለ፣ መንግሥት ንብረቱን የመውረስ ሥልጣን እንዳለው ረቂቅ አዋጁ እንደሚደነግግ ዘገባው አመልክቷል። ዓቃቤ ሕግ ምንጩ አይታወቅም ብሎ ለሚጠረጥረው 5 ሚሊዮን ብር ለሚገመት ንብረት 10 ዓመት ወደኋላ ሂዶ ክስ ማቅረብ እንደሚችልም ረቂቅ አዋጁ ይፈቅዳል ተብሏል።

@ethio_mereja_news
ተፈቱ‼️

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ እና ቴዎድሮስ ዘርፉ ከእስር ተፈቱ

ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት “አካልን ነጻ የማውጣት” አቤቱታ ያቀረቡት ሶስት ጋዜጠኞች ከእስር ተፈቱ። ዛሬ እና ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኞች በቃሉ አላምረው፣ በላይ ማናዬ፣ ቴዎድሮስ ዘርፉ ናቸው።

ሶስቱ ጋዜጠኞች የፌደራል ፖሊስ “ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ በእስር እንዲቆዩ” ማድረጉን በመጥቀስ ለፍርድ ቤት አቤቱታ ያቀረቡት ባለፈው ሳምንት ነበር። ከአቤቱታ አቅራቢዎች አንዱ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ ከእስር የተፈታው፤ ዛሬ ሰኞ ሰኔ 10፤ 2016 ከሰዓት መሆኑን ባለቤቱ በላይነሽ ንጋቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግራለች።

“ኢትዮ ኒውስ” የተሰኘው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ በላይ፤ በህዳር 2016 በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለው በኋላ ለሰባት ወራት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ላይ ቆይቷል። ጋዜጠኛው ባለፈው ግንቦት ወር አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መዘዋወሩ ይታወሳል።

አስር ወራትን በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በእስር ያሳለፈው ሌላኛው ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ፤ ባለፈው አርብ ሰኔ 7፤ 2016 ወደ አዲስ አበባ እንዲመጣ ከተደረገ በኋላ በማግስቱ ከእስር መለቀቁን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጿል። “ምኒልክ” እና “ዓባይ”በተሰኙ የበይነ መረብ እና የሳተላይት ቴሌቪዥን ቻናሎች ላይ በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ፕሮግራም ያዘጋጅ የነበረው ቴዎድሮስ፤ በፖሊስ ቁጥር ስር የዋለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በፓርላማ ከጸደቀ ከአንድ ሳምንት በኋላ ነበር።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በኖኖ ወረዳ በሰርገኞች ላይ በተወረወረ ቦምብ ሙሽሮችን ጨምሮ  ሁሉም ሰርገኛ ህይወት አለፈ‼️

በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ ኖኖ ወረዳ ሰርገኞችን ዒላማ ባደረገ ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ኮማንድ ፖስት እና ነዋሪዎች ገለጹ።

የኖኖ ወረዳ ኮማንድ ፖስት ኃላፊ አቶ ተሾመ ሰቦቃ ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ በሰጡት ቃል ፥ ጥቃቱ ቅዳሜ ሰኔ 8 ንጋት ላይ ነው የተፈጸመው።

ጥቃት አድራሾቹ " ጽንፈኛ የአማራ ታጣቂዎች  ናቸው " ብለዋል።

ኃላፊው " ሰርገኞቹ ቤት ውስጥ እያሉ በር ዘግተውባቸው ቦምብ ወረወሩባቸው። ቤት ውስጥ ከነበሩት አንድም በሕይወት የወጣ የለም። እዚያው ተቃጥለው አልቀዋል "  ሲሉ ሁኔታውን አስረድተዋል።

አንድ የአካባቢው ነዋሪ ታጣቂዎቹ ሰርግ ቤቱ ላይ ከአንድ በላይ ቦምብ ወርውረው ሙሽሮቹን እና አብረዋቸው የነበሩ ሰዎችን መግደላቸውን ተናግረዋል።

የኮማንድ ፖስት ኃላፊን ጨምሮ የአካባቢው ነዋሪዎች በሰጡት ቃል ፥ በሰርግ ቤት ላይ የተነሳውን እሳት ለማጥፋት የመጡ የአካባቢው ነዋሪዎች በታጣቂዎቹ የተኩስ እሩምታ ተከፍቶባቸው በርካታ ሰዎች ተገድለዋል።

የአካባቢው ነዋሪ የሟቾች ቁጥር ከ30 እስከ 50 ሊደርስ እንደሚችል ተናግረዋል።

በጥቃቱ ሙሽሪት እና ሙሽራውን ጨምሮ የሰርጉ ታዳሚዎች የሆኑ ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን ነዋሪው ተናግረዋል።

የወረዳው የኮማንድ ፖስት ኃላፊ አቶ ተሾመ ሰቦቃ ፥ " በእሳት ተቃጥለው የሞቱ ሰዎችን ቁጥር መለየት አስቸጋሪ በመሆኑ ትክክለኛውን የሟቾች ቁጥር መለየት አልተቻለም " ሲሉ ለቢቢሲ ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ባለፈው ሚያዚያ ወር ላይ በዚህ ወረዳ በ5 ቀበሌዎች በተፈጸመ ጥቃት 12 ሰዎች መገደላቸውን ፤ ቤቶች መቃጠላቸውን ፣ ከብቶችም እየተነዱ መወሰዳቸውን ነዋሪዎች መግለጻቸው ይታወሳል።

ኢሰመኮም መረጃውን የማጣራት ስራ እየሰራ እንደነበር መግለጹ አይዘነጋም።

ከሟቾች አብዛኛዎቹ የአማራ ብሔር ተወላጆች እንደነበሩ ፤ ጥቃት ፈጻሚዎችም የ " ሸኔ (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት) ታጣቂዎች " እንደሆኑ ነዋሪዎች መናገራቸው ይታወሳል።

ዘገባው tikvahethiopia ነው።


@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መንግሥት ያቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ በሳዑዲ ዓረቢያ ባስቸጋሪ ኹኔታ ላይ የነበሩ 1 ሺህ 172 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ወደ አገራቸው እንደመለሰ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።

ከተመላሾቹ ስደተኞች መካከል፣ ኹለት ጨቅላ ሕጻናት እና ዕድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የኾኑ 29 ታዳጊዎች እንደሚገኙበት ሚንስቴሩ ገልጧል።

ብሄራዊ ኮሚቴው ከሚያዚያ 4 ጀምሮ እስከ ትናንት ድረስ ከ45 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን መመለስ ችሏል።

@ethio_mereja_news
16 የፌደራሉ መንግስት መስሪያ ቤቶች በስራ ገበታቸው ለሌሉና ለተሰናበቱ ሰራተኞች ግማሽ ሚሊዮን ብር ገደማ ክፍያ ከህግ ውጪ መፈፃማቸውን ዋና ኦዲተር አጋለጠ‼️

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከደንብና መመሪያ ውጪ 3 ሚሊዮን ብር ክፍያ በመፈጸም በቀዳሚነት ሲቀመጥ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር በሁለተኛነት ይከተላል፡፡
ይህ የተነገረው የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የ2015 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች የፋይናንስ ህጋዊነት ኦዲት እና የክዋኔ ኦዲት ሪፖርትን በዛሬው ዕለት ለህዝብ አንደራሴዎች ምክር ቤት ባቀረበበት ወቅት ነው፡

ዋና አዲተር መሠረት ዳምጤ በንባብ ባቀረቡት በዚህ ሪፖርት 30 የፌደራል መንግስት መስሪያ ቤቶች 16 ሚሊዮን 470ሺህ ብር ከደንብና መመሪያ ውጪ አላግባብ መክፈላቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ከእነዚህ ከህግ ውጪ ክፍያ ከፈጸሙ የመንግስት መስሪያ ቤቶች መካከል በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሊቀመንበር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) የሚመራው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር 3 ሚሊዮን ብር ከደንብና መመሪያ ውጪ በመፈጸም በቀዳሚነት ተቀምጧል፡፡

በለገሠ ቱሉ (ዶ/ር) የሚመራው የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር ደግሞ  ብር 2 ሚሊዮን 889ሺህ ክፍያዎችን አላግባብ ከደንብና መመሪያ ውጪ መፈጸማቸውን በኦዲት መረጋገጡን ዋና ኦዲተሯ ለአንደራሴዎቹ አስረድተዋል፡፡ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርስቲ፣ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሰቲዎች ከህግ ውጪ ክፍያዎችን ከፈጸሙ ተቋማት መካከል ዋናኞቹ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡

ዋና ኦዲተሯ ይህን ከደንብና መመሪያ ውጪ የተፈጸሙ ክፍያዎችን ከዘረዘሩ በኋላ ተቋማቱ ደንብና መመሪያ ተከትለው ክፍያ እንዲፈጽሙ፣ አላግባብ የከፈሉትንም ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡

በዋና ኦዲተሯ በኩል የቀረበው ሌላው የኦዲት ክዋኔ ሪፖርት በመስሪያ ቤቱ ውስጥ ለሌሉ እና ለተሰናበቱ ሰዎች የተከፈሉ ክፍያዎችን ይመለከታል፡፡ በዚህም በ16 መስሪያ ቤቶች በስራ ላይ ለሌሉና ለተሰናበቱ ሰራተኞች ከ485ሺህ ብር በላይ አላግባብ ክፍያ መፈጸሙ ተረጋግጧል፡፡

እንደ ሪፖርቱ ከሆነ በ2014 እና ከዚያ በፊት 92 መስሪያ ቤቶች ተመላሽ እንዲደርጉ በሚል አስተያየት ከተሰጠበት 443 ሚሊዮን ብር፣ ከ23 ሺህ ዶላር በላይ ገንዘብ ተመላሽ የሆነው 11 በመቶ ብቻ ወይም 48.2 ሚሊዮን ያህል መሆኑን መሠረት ዳምጤ በሪፖርታቸው አቅርበዋል፡፡
ይህም ማለት 89 በመቶ ወይም 394.8 ሚሊዮን ብሩ ተመላሽ አልተደረገም፡፡(አሻም)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት አራት ሰዎች ተገደሉ፣ የአከባቢው ባለስልጣናት እና ነዋሪዎች “የፋኖ ታጣቂዎችን” ተጠያቂ አድርገዋል!

ስለጥቃቱ አዲስ ስታንዳርድ የጠየቃቸው #የጨካ ከተማ ከንቲባ ሁኔታውን ሲያስረዱ ግጭቱ የተፈጠረው “በጽንፈኛው የፋኖ ሀይሎች” እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ሸኔ) መካከል መሆኑን ጠቁመው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ሸኔ) ሀይሎች የፋኖ ሀይሎችን ከከተማዋ በማስወጣት ተቆጣጥረዋት ነበር ብለዋል።

እንደ ከንቲባው ገለጻ ከሆነ የፋኖ ሀይሎች በተደጋጋሚ ይህንን ለመበቀል ወደ ከተማዋ በመዝለቅ በንጹሃን ላይ ጥቃት ይፈጽማሉ ብለዋል።

“የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ሸኔ) ታጣቂዎች በከተማዋ የገበያ ቦታ ላይ በቅርቡ በፈጸሙት ጥቃት የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉን እና በርካቶች መቁሰላቸውንም” ገልጸዋል።

በአከባቢው ያለው የጸጥታ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ነው ሲሉ ጠቁመዋል። በዚህም ሳቢያ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች አከባቢውን ለማረጋጋት መግባታቸውን አስታውቀዋል፤ አከባቢው በጣም ሰፊ በመሆኑ እና በረሃማ አየር ጸባይ ስላለው የጸጥታ ቁጥጥሩን አስቸጋሪ አድርጎታል ሲሉም ገልጸዋል።

የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊትን (ሸኔን) እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር ጥረት ሲደረግ የፋና ሀይሎች በሌላ አቅጣጫ ጥቃት እንደሚከፍት ጠቁመዋል፤ ይህም በወረዳዋ የጸጥታ እና መረጋጋት ስራውን እንዳወሳሰበት አስታውቀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
💥💥 የዋጋ ግሽበት ከመቼውም በላይ እየጨመረ ይገኛል

👉ብልህ ሰዉ ነገዉን ዛሬ ይወስናል !!ይፍጠኑ !!
DMC Real Estate Plc
በለቡ መብራት 65,395ካሬ ላይ ያረፈ ሰፊ እና እጅግ ዉብ መንደር

ቻድ ኢንባሲ እና CDC በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛል !
👉በምቹ አከፋፈል 10%  560.ሺ ቅድመ ክፋያ ጀምሮ
👉የንግድ ሱቆች G.floor -2rd floor ከ 24 ካሬ ጀምሮ
👉ከstudio 56ካሬ እስከ 4መኝታ 186ካሬ .በተለያየ የካሬ አማራጭ

👉በሚገርም ወብ Design የቀረበ
👌በዘመነ ፈጣን በተቀላጠፈ ቴክኖሎጂ አልሙንየም ፎርም ወርክ የሚሰራ

😄❗️ሰበር ዜና
❗️ዛሬ አዳዲስ 2ኛ floor ጀምሮ ዝቅተኛቤት floor ጥቂት ቤቶች  አዉተናል ይፋጠኑ,ይምረጡ  !!
🌀 ብርዎትን አሰሩት፤ በኢትዮጵያ ትልቁ አዋጭ የሆነው የሪል እስቴት ቢዝነስ ነው፡፡

ዲኤም ሲ ሪል እስቴት/Dmc Real Estate

ለበለጠ መረጃ /ለሳይት ጉብኝት
ይጀዉሉልን!
☎️ 0961478081
በትግራይ ክልል ከ122 ሺህ በላይ ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እየወሰዱ ነው‼️


በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዶክተር ታደሰ ካህሳይ እንደገለጹት፤ የስምንተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተናው እየተሰጠ ያለው በ1ሺህ 129 ትምህርት ቤቶች ነው።

ፈተናው ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት ቀናት እንደሚሰጥም ተናግረዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ ከተፈታኞች መካከል 62 ሺህ 732 የሚሆኑት ሴት ተማሪዎች ናቸው።

ተማሪዎቹ ፈተናውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲወስዱ አስቀድሞ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል።

የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ተቆጣጣሪዎች በበቂ ሁኔታ መመደባቸውን ጠቁመው፣ ለፈተናው ሰላማዊነትም የጸጥታ አካላት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን መግለጻቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ጥቆማ‼️

በቴሌግራም ገንዘብ መስራት ይቻላል ለሱም ምስክር NOTCOIN መመልከት በቂ ነው።

በኦንላይን ገንዘብ መስራት ከፈለጋቹ አሁንኑ ይህንን ቻናል መቀላቀል ግድ ነው👇👇
http://www.tg-me.com/sheger_crypto
http://www.tg-me.com/sheger_crypto
2024/09/29 23:16:04
Back to Top
HTML Embed Code: