Telegram Web Link
በ55,000 ብር ከገዛናው በሬ በ100,000 ብር የሚገመት ወርቅ ተገኘ።

በወላይታ ዞን በዳሞት ፑላሳ ወረዳ ሻንቶ ከተማ ለትንሳኤ በዓል ለእርድ በ55,000 ብር ከተገዛው በሬ የተገኘው ወርቅ በ100,000 ብር ተሽጧል።

ከዚህ በፊት በወላይታ ዞን ጠበላ ከተማ ለገና ከታረዱት በሬዎች በ235,000 ብር የሚገመት ወርቅ መገኘቱን መዘገባችን የሚታወስ ነው።

መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ።

Via:- Bonga Ethiopia

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ ሰራተኞች እየተከፈላቸው ባለዉ ደመወዝ ክፍያ ኑሮን መቋቋም ባለመቻላቸው ለችግር መጋለጣቸውን ኢሰማኮ አስታወቀ!

የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን የኢትዮጵያ ሰራተኞች እየተከፈላቸው ባለዉ ደመወዝ ክፍያ ኑሮን መቋቋም ባለመቻላቸው ለችግር መጋለጣቸውን በመግለፅ ይህን አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ያቀረብኩት ጥያቄ ትኩረት ሳይሰጠዉ ቀርቷል ብለዋል።

ማህበሩ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበው ምላሽ አላገኙም ካሏቸዉ ጥያቄዎች ዉስጥ "ሠራተኞች አሁን እየተከፈላቸው ባለው የደመወዝ ክፍያ የኑሮ ዉድነቱን በፍጹም መቋቋም ያልቻሉ በመሆኑ ደመወዝ የገቢ የሥራ ግብር እንዲቀነስ ላቀረብነዉ ጥያቄ መንግሥት ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ብሏል።

ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል የሚወስን የደመወዝ ቦርድ እንዲቋቋም በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ የተደነገገ ቢሆንም የደመወዝ ቦርድ ማቋቋሚያ ደንብ በሚንስትሮች ምክር ቤት ባለመውጣቱ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ያልተገባ መሆኑን ነዉ ማህበሩ ያስታወቀው።

በጦርነት ዘላቂ መፍትሒ ስለማይመጣ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ግጭትና ጦርነት ቆሞ በዉይይት ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ሁሉም ወገኖች በድርድር እንዲፈቱ የጠየቀው ኢሰማኮ ለጉዳዩ አፅንኦት ይሰጠዉ ብሏል በመግለጫው።

[Capital]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ሙዓለ ነዋይ ለማፍሰስ ማቀዱን በላከው መግለጫ መግለጡን ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል።

ኩባንያው በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ፣ አጠቃላይ የኔትዎርክ ማማዎችን ቁጥር ከ7 ሺህ በላይ ለማድረስ 5 ሺህ አዳዲስ የቴሌኮም ኔትዎርክ ማማዎችን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለመትከል አስቤያለሁ ማለቱን ዘገባው አመልክቷል። ኩባንያው ባኹኑ ወቅት 2 ሺህ 500 የቴሌኮም ኔትዎርክ ማማዎች በአገሪቱ ውስጥ አሉት።

1 ሺህ 500 ያህሉ የኔትዎርክ ማማዎች ኩባንያው ራሱ የተከላቸው እንደኾኑ ገልጧል ተብሏል። ቀሪዎቹ የኔትዎርክ ማማዎች፣ ኩባንያው ከኢትዮ ቴሌኮም በኪራይ የሚጠቀምባቸው ናቸው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የሕወሃት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር ወግነው እየተዋጉ ነው በማለት ያቀረበውን ውንጀላ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል።

የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ውንጀላ "በጥብቅ እንደሚያወግዝ" የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ይህን ውንጀላ ያሰማው ዓለማቀፍ ድጋፍ ለማግኘት ሲል ነው በማለት አጣጥሎታል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ሕወሃት የፖለቲካ ፓርቲ በመኾኑ "የታጠቀ ኃይል ወይም ሚሊሺያ የለውም" በማለትም ምላሽ ሰጥቷል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ አያይዞም፣ ሱዳን በትግራዩ ጦርነት ወቅት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉን ስደተኞች ያስጠለለች እንደመኾኗ ትግራይ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ የምትገባበት ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብሏል።

ኹለቱ ወገኖች ጦርነቱን ከሚያባብሱ ንግግሮች እንዲቆጠቡና ጦርነቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጠይቋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
“የህወሓት ወታደሮች” በሱዳን ግጭት ውስጥ ተቀጥረው እየተዋጉ ነው መባሉን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባበለ

በኮማንደር መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) የሚመራው የሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ታጣቂዎች ለጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን በማገዝ እየተዋጉ ነው ቢልም ህወሓት ሀሰተኛ ትችት ነው ብሏል።

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚያዝያ 26 ቀን 2016 ካወጣው መግለጫ አዲስ ማለዳ እንደተመለክተችው የጀነራል አል ቡርሃን የሱዳን ታጣቂ ኃይል የውጭ ቅጥረኞችን ይቀጥራል የተባለ ሲሆን “ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ውስጥ ጭካኔ ፈጽሟል” የተባለው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር (ህወሓት) ኃይሎች አሁን ከአል ቡርሃን እና አጋር ታጣቂዎቹ ወግነው እያጠቁን መሆኑን በማስረጃ አረጋግጠናል ብሏል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ትላንት ባሰራጩት መግለጫ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ወቀሳ “መሰረት ቢስ” ነው ያለ ሲሆን፤ ታጣቂ ኃይሉ በእርስ በእርስ ግጭት ውስጥ ዓለም አቀፍ ድጋፍ ለማግኘት አቅዶ ያዘጋጀው ትርክት ነው መባሉን አዲስ ማለዳ ከመግለጫው ተመልክታለች።

የትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር መግለጫ እንደጠቀሰው ህወሓት “አንድ የፖለቲካ ድርጅት እንጂ የትጥቅ አደረጃጀት በፍጹም የሌለው እና የሚያዛቸው ታጣቂዎችም የሌሉት ስብስብ” ነው። የትግራይ ሕዝብ ከሱዳን ሕዝብ ጋር ያለው የጠበቀ ወዳጅነትም ይህን እንድናደርግ አይገፋንም ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ መግለጹን አዲስ ማለዳ ተመልክታለች።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
#DV 2025
የኢትዮጵያ ፕሬስ ነፃነት ካለፈዉ ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ 11 ደረጃዎች በማሽቆልቆል 141ኛ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ

በየአመቱ የዓለም ፕሬስ ነፃነት ዝርዝር የሚያወጣዉ ድንበር የለሹ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (RSF) የኢትዮጵያ የፕሬስ ነፃነት ከ 180 ሀገራት ዉስጥ 141ኛ ደረጃ ላይ መመደቧን አስታዉቋል።

ይህ ድርጅት ትላንት ሚያዝያ 28 ፤ 2016 ዓ.ም. ባወጣዉ ሪፖርት "ከ 180 ሀገራት ዉስጥ ኢትዮጵያ 141ኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን ገልፆ ይህም ካለፈዉ የፈንጆቹ ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ 11 ደረጃዎች ማሽቆልቆሏን አመላክቷል ።

የአለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነትን ምክንያት በማድረግ ደረጃዎችን የሚያወጣዉ ተቋሙ "በየሀገራቱ ያሉት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ አውዶች፣ የህግ ማዕቀፍ እና የደህንነት ሁኔታ፤ ድርጅቱ ደረጃዎቹን ለማውጣት በጠቋሚነት የሚገለገልባቸው መመዘኛዎች" ናቸው።

በተያዘዉ ዓመት በሚዲያ ነፃነት ኤርትራ ባለፈዉ ዓመት ከነበነረችበት ደረጃ በስድስት በማሽቆልቆል 180 ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የጠቆመዉ ሪፖርቱ ሰሜን ኮሪያ ፣ አፍጋኒስታን እና ሲሪያ ከ 177 እስከ 179 ደረጃን መያዛቸውን አስታዉቋል።

እንደ ድርጅቱ ዝርዝር ከሆነ ኖርዌይ ፣ ዴንማርክ ፣ ስዊድን እና ኔዘርላንድ ከ 1 እስከ 4ኛ ደረጃን በመያዝ የሚዲያ ነፃነት ያለባቸው ሀገራት መሆናቸዉን አስመስክረዋል ።

(capital)
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ከሀዋሳ አዲስ አበባ በሚበር አውሮፕላን ጭስ ቢታይም መንገደኞች ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መውረዳቸውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታወቀ

የበረራ ቁጥር ኢቲ 154 ዛሬ ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ አውሮፕላኑ ውስጥ ጭስ ታይቷል።

ይሁን እንጂ አውሮፕላኑ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል በመቆም መንገደኞች ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መውረዳቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ያለ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ደንበኞቹን ይቅርታ መጠየቁን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያወጣው መረጃ ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት፣ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ራስ ገዝ የአገርነት እውቅና የመስጠት ሃሳብ እንደሌላት ለዲፕሎማቶች መግለጣቸውን ጠቅሰው የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የሶማሊላንድ ባለሥልጣናት፣ ከኢትዮጵያ ጋር የተደረሰው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ተግባራዊ ሊኾን እንደተቃረበና በኹለት ወራት ውስጥ የመጨረሻው ስምምነት ሊፈረም እንደሚችል በቅርቡ መግለጣቸው አይዘነጋም።

ኾኖም የኢትዮጵያ መንግሥት በሶማሌላንድ በኩል ለሚሰጡ መግለጫዎች በይፋ የሰጠው ማረጋገጫ ወይም ማስተባበያ የለም።
ዋዜማ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በኢትዮጲያ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ወስጥ የነበሩ ሱዳናዉያን በጥቃት ምክንያት መሰደዳቸዉ ተሰማ‼️

በሺዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን ስደተኞች በሰሜን ኢትዮጵያ በሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ካምፖች ዉስጥ የሚገኙ ሲሆን የጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡ሶስት ስደተኞች ለቢቢሲ እንደተናገሩት ከኮሜር እና ኦላላ ካምፖች የተሰደዱት ሰዎች ቁጥር 7,000 ሊደርስ ይችላል።

ሆኖም ግን ከካምፑ ተሰሰደዱ ስለተባሉት ሰዎች በገለልተኛ አካል አሃዙን ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኤጀንሲ ስለ ክስተተ መግለጫ አልሰጠም። ነገር ግን በጸጥታ እጦት ቅሬታ ሳቢያ ካምፑን ለቀው የወጡ ስደተኞችን መኖራቸዉን እንደሚያውቅ አስቀድሞ መናገሩ ይታወሳል፡›፡ካምፑ ካለፈው አመት ነሃሴ ወር ጀምሮ በአካባቢው ሚሊሻዎች ከሰራዊቱ ጋር እየተፋለሙ ባለበት የኢትዮጵያ ሰሜን ምዕራብ የአማራ ክልል ዉስጥ ይገኛል።

ክልሉ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር በመሆኑ የበይነመረብ ግንኙነት ተቋርጧል።ስደተኞቹ እንዳሉት ካምፖች ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በታጣቂዎች ጥቃት እየተፈጸመባቸው ሲሆን እገታ እየተለመደ መጥቷል።ከባለሥልጣናት ጥበቃ እጦት የተነሳ በዋናው መንገድ እና በአቅራቢያው ባለ ትንሽ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አጠገብ እንዳደሩ አንድ ስደተኛ ተናግሯል።

“በድንኳኔ ብቆይ ምናልባት መጥተው በጥይት ሊመቱን ይችላሉ። በአደጋ ላይ እንዳለዉ ስለተሰማኝ ጥሩ እንቅልፍ መተኛት አልቻልኩም” ፣ “በሌሊት በጣም አደገኛ ስለሆነ በዚያ ቦታ መቆየት አትችልም” ሲል አክሏል፡፡በሱዳን ጦር እና ተቀናቃኝ የፈጣን ደጋፊ ሃይሎች (RSF) ጦርነት ከጀመረበት ካለፈው ሚያዚያ ጀምሮ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሱዳን ዜጎች ከሀገር ተሰደዋል።

ወደ 33,000 የሚጠጉት ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸዉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታዉቋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ብዙ ዜጎቻቸውን በስቅላት የሚቀጡ ሀገራት እነማን ናቸው🤔

እንደ አምንስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ከሆነ የሞት ፍርድ ቁጥር እየጨመረ የመጣ ሲሆን ፍርዳቸው በስቅላት ወይም አንገታቸው ተቀልቶ የሚገደሉ እንዳሉም ተገልጿል፡፡

በ2022 ዓመት ብቻ 2 ሀገራት ዜጎቻቸውን በስቅላት ቀጥተዋል የተባለ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ መከሰት በሞት የሚቀጡ ዜጎች ቁጥር እንዲጨምር አድርጓልም ተብሏል፡፡

ቻይና ብዙ ዜጎቿን በስቅላትበመቅጣት ከዓለማችን ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን በዓመት በአማካኝ 1 ሺህ ዜጎችን በስቅላት ቀጥታለች፡፡

ሌላኛዋ ሀገር ኢራን ስትሆን ከ570 በላይ ዜጎችን በስቅላት ስትቀጣ አፍሪካዊቷ ግብጽም ዜጎቿን በስቅላት ከሚቀጡ ሀገራት መካከል ተጠቅሳለች፡፡
ሳውዲ አረቢያ፣ አሜሪካ እና ሲንጋፖር በተጨማሪነት የተጠቀሱ ሀገራት ሲሆኑ ሀገራቱ ዜጎቻቸውን በሞት እየቀጡ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በቤንዚን ላይ ጭማሪ ሲደረግ ሌሎች የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላሉ ተባለ!

ከግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከቤንዚን ውጪ የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዓለም ገበያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየታየ የመጣውን የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መነሻ በማድረግ በቤንዚን የችርቻሮ መሸጫ ላይ ብቻ መጠነኛ ማሻሻያ መደረጉን ሚኒስቴሩ አመልክቷል።

በመሆኑም ከግንቦት 1 ቀን 2016 ከምሽቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ ያለው የነጭ ናፍጣ፣ የኬሮሲን፣ የአይሮፕላን ነዳጅ፣ የቀላል ጥቁር ናፍጣ እና የከባድ ጥቁር ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል።

በዚህም መሰረት:-
ቤንዚን ……………………………………… ብር 78.67 በሊትር
ነጭ ናፍጣ………………………………… ብር 79.75 በሊትር
ኬሮሲን …………………………………... ብር 79.75 በሊትር
የአውሮፕላን ነዳጅ ………………... ብር 70.83 በሊትር
ቀላል ጥቁር ናፍጣ…………………… ብር 62.36 በሊትር
ከባድ ጥቁር ናፍጣ…………………. ብር 61.16 በሊትር ሆኗል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መንግሥት 12 ነጥብ 57 ቢሊዮን ብር የነዳጅ ድጓማ አድርጊያለሁ አለ

መንግሥት በ2016 በጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ለሕዝብ አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪዎች 12 ነጥብ 57 ቢሊዮን ብር የነዳጅ ድጓማ ማድረጉን ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ። 102 ሺህ 329 ተሽከርካሪዎች ከድጎማ ተጠቃሚነት በጊዜዊነት መታገዳቸውም ተጠቁሟል።

በትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ብሔራዊ የታለመለት ነዳጅ ድጎማ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሰልማን መሐመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በ2016 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ብቻ ለታለመለት የነዳጅ ድጎማ 12 ነጥብ 57 ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል።

የነዳጅ ድጎማ ከተጀመረ ጀምሮ 241 ሺህ 81 ተሽከርካሪዎች የድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተመዘገቡ ቢሆንም፤ ጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም በተደረገ ኦዲት በድጎማ ማስተግበሪያ ሥርዓቱ ውስጥ የድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተመዘገበው የሚገኙት የተሽከርካሪ ቁጥር 141 ሺህ 182 ናቸው ብለዋል።
(ኢ ፕ ድ)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር፣ በአማራ ክልል ከሚገኘው አውላላ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ 1 ሺህ የሚጠጉ ሱዳናዊያን ስደተኞች እንዲኹም ከኩመር መጠለያ ጣቢያ ከ300 እስከ 400 የሚገመቱ ስደተኞች ለቀው መውጣታቸውን መግለጡን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ስደተኞቹ፣ ከመተማ ወደ ጎንደር በሚወስደው መንገድ ላይ እንደሚገኙ ኮሚሽኑ መግለጡን ዘገባዎቹ አመልክተዋል፡፡

ስደተኞቹ ኹለቱን መጠለያ ጣቢያዎች ለቀው ለመውጣት የተገደዱት፣ በመጠለያዎቹ የግድያ፣ ሥርቆት፣ የተደራጀ ዝርፊያና የጠለፋ ወንጀሎች በመስፋፋታቸውና የአገልግሎት ችግሮች በመባባሳቸው እንደኾነ፣ ኮሚሽኑ ከስደተኞቹ መስማቱን ጠቅሷል ተብሏል። በመተማና በባንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩምሩክ በሚገኙ መጠለያ ጣቢያዎች ከ53 ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ስደተኞች እንደሚገኙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት፣ የስደተኞቹን "የደኅንነት ስጋቶች" እና "የአገልግሎት አቅርቦት ችግሮች" ለመፍታት ጥረት እያደረገ መኾኑን ትናንት ባወጣው መግለጫ ያስታወቀ ሲኾን፣ በቅርቡ በአውላላ እና ኩመር መጠለያ ጣቢያዎች የተፈጠረው "ክስተት እንዳሳሰበው" መግለጡም አይዘነጋም።

@ethio_mereja_news
በአዲስ አበባ ከተማ በትላንትናው እለት ባጋጠመ የእሳት አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወት አለፈ

በአዲስ አበባ ከተማ ግንቦት 1ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 5:17 ሰዓት ላይ በቦሌ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 2 ጃፓን ኤንባሲ አካባቢ ባጋጠመ የእሳት አደጋ የአንድ ሰዉ ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የእሳት አደጋዉ ያጋጠመዉ በአንድ መጋዘን ላይ ሲሆን ህይወታቸዉ ያለፈዉ ግለሰብ የመጋዘኑ የጥበቃ ሰራተኛ ናቸዉ።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቦታዉ ላይ ፈጥነዉ ቢደረሱም የጥበቃ ሰራተኛዉ ህይወት አስቀድሞ ያለፈ በመሆኑ የእሳት አደጋዉ ተዛምቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር ችለዋል።

መጋዘኑ ለመጋዘን አገልግሎት ስራ መዋል የማይገባዉ የመኖሪያ ቤት ቢሆንም ባለንብረቶቹ ቤቱን ለመጋዘን አገልግሎት ይጠቀሙት እንደነበር ኮሚሽኑ አስታውቋል።

ማናቸዉም ዕቃዎች የሚቀሙጡባቸዉ መጋዘኖች እሳትን ሊቋቋሙ ከሚችሉ ግብዓቶች የተገነቡና ለዚሁ ዓላማ ብቻ የተገነቡ መሆን ይኖርባቸዋል ሲል ኮሚሽኑ አሳስቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
#ኢትዮጵያ#አሜሪካ የሚገኙ ተፈላጊዎችን ሀገሪቱ አሳልፋ በመስጠት ትብብር እንድታደርግ ጠየቀች‼️
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል፤ በአሜሪካ ተቀምጠው “የኢትዮጵያን ሰላምና ደኅንነት የሚያውኩ ተፈላጊዎችን” አሳልፎ በመስጠት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋን ትብብር እንዲያደርጉ ጠየቁ፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአሜሪካው የፌዴራል የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር አምባሳደሩ የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱም ኮሚሽነር ጀነራል ጥሪ ማቅረባቸውን የፌደራል ፖሊስ መረጀ አመላክቷል፡፡

ኮሚሽናር ጀነራሉ ጥያቄውን ያቀረቡት አምባሳደሩን በቢሯቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው፡፡

አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው፤ በአሜሪካን መንግሥት የሚፈለጉ ወንጀለኞችን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አሳልፎ በመስጠት ላበረከተው አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ሀገራቸው ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ተመሳሳይ ድጋፎችን እንድታደርግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ መናገራቸውም ተገልጿል፡፡
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ፣ በኢትዮጵያ "የጸጥታ ችግሮች" እና "የሞባይል ዳታ ገደቦች" ማነቆ እንደኾኑበት ሃላፊዎቹ ትናንት ናይሮቢ ውስጥ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

ሃላፊዎቹ፣ በኢትዮጵያ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች የኩባንያው እንቅስቃሴና አገልግሎቶች የተገደቡ እንደኾኑ ገልጸዋል።

በተለይ ኩባንያው 500 የቴሌኮም ኔትዎርኮች በዘረጋበት አማራ ክልል ውስጥ፣ የሞባይል ዳታ አገልግሎት ገደብ እንደተጣለበት ሃላፊዎቹ ጠቅሰዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኦሮሞ ህዝብ ማንነቱን ተነፍጎ፣ በቋንቋው መጠቀም አንዳይችል ተደርጎ፣ የሀገር ባለቤትነቱ ተነፍጎ በሀገሩ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ለመቆጠር ተገዶ ቢቆይም አሁን ነጻ ወጥቷልም ብለዋል‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በትናንትናው እለት በነቀምቴ ከተማ በነበራቸዉ ቆይታ “ጦርት፣ እርስ በእርስ መገዳድልና መበላላት ይብቃን” ሲሉ ጥሪ አቅርበዉ ነበር።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በትናንትናው እለት በነቀምቴ ወለጋ ስታዲየም በተዘጋጀ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ሠላም፣ አንድነትና ልማት ላይ ያተኮሩ ሐሳቦችን አንስተዋል።

በዚህም “የኦሮሞ ህዝብ ከአንድ ክፍለ ዘመን በለይ ማንነቱን ተነፍጎ፣ በቋንቋው መጠቀም አንዳይችል ተደርጎ፣ የሀገር ባለቤትነቱ ተነፍጎ በሀገሩ እንደ ሁለተኛ ዜጋ ለመቆጠር ተገዶ ቆይቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒትር ዐቢይ ፤ አሁን ግን በከተፈለ መሰዋእትነት “ኦሮሞ ነጻ ወጥቷል” ህዝቡ ይህንን ሊረዳ ይገባል ብለዋል።

“ለኦሮሞ ህዝብ በሙሉ በነቀምት አዋጅ ማወጅ እፈልጋለሁ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በኦሮሚያ ምድር ውስጥ ጦርነት፣ የኦሮሞ ልጆች እርስ በእርስ በእርስ መገዳደል አንዲሁም የኦሮሞ ልጆች ተቀምጠው ስለ ችግሮቻቸው መወያየት አለመቻል ከዛሬ ጀምሮ መቆም ለአበት” ሲሉ ተናረዋል።

“በጠላት መታለል እና በጠላት አጀንዳ መከፋል ይብቃን” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ “ባህላችንን እና ማነታችንን የሚገልጸው በመወያት፣ በመደማመጥ እንዲሁም በጋራ የወሰኑትን ነገር ይዞ ወደ ስራ በመቀየር ነው” በማለት ገልጸዋል።“አብረን መወያት አቅቶን ከጠላት ጋራ መምከር አሳፋሪ ነው፤ ስለዚህ ከታሪክ ተምረን ለህዝባችን ሰላም ማምጣት አንድንችል ጦርት እና መገዳደል ይብቃ” ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።

“የኦሮሞ ህዝብ ከአንድ ከፍል ዘመን በላይ በማንም ሲገዛ እና የማንም መጫወቻ ሲሆን የቆየው አንድነት ስላጣ ነው” ብለዋል።  አዩዘሀበሻ በአልአይን ዘገባ ላይ ፤ የኦሮሞ ህዝብ በማን መጫወቻ እንደነበር እና በማን ሲገዛ እንደቆየ ጠ/ሚኒስትሩ ስለመናገራቸዉ በዘገባው አልተካተተም።

“የኦሮሞ ህዝብ በአንድንት መቆም ቢችል ኖሮ ላለፉት 50 ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ ትግል ወደኋላ እየተመለሰ አይኖርም ነበር” ሲሉም ተናግረዋል ሲል የዜና ምንጩ ዘግቧል ።“ለልማትም፣ ለጦርነትም፣ ራስን ለመጠበቅም እንዲሁም የተለያዩ ሃሳቦችን ለማመንጨት አንድነት ያስፈልገናል” ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ “የኦሮሞ ህዝብ አንድንት ከማንኛመው ጊዜ እስፈላጊ የሚሆንበት ጊዜ ላይ ነን” ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው ያነሱት ሶስተኛው ነጥብ ስለ ልማት ሲሆን በዚህም የለውጡ መንግስት ወደ ስልጣን ሲመጣ ሀገሪቱ ለሰራተኞቿ ደመወዘወ መከፍል የማትችልበትና የውጭ ሀገራት እዳዋ ከእቅሟ በላይ ነበር ሲሉ አስታውሰዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እንደ ምስራቅ አፍሪካ 2ኛ ነበር፤ እንደ አፍሪካም እኮኖሚያችን በጣም ወደ ኋላ የቀረ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ዛሬ ግን በጦርነት እና በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ሆነንመ ቢሆን በመስራቅ አፍሪካ 1ኛ፤ በአፍሪካ ውስጥም ከፍተኛ የኢኮኖሚ ለውጥ እየገነባን ነው” ብለዋል።

“የአፍሪካ ተምሳሌት የሚሆን ኢኮኖሚ እና ብልጽግናን የመገንባት ስራችንን የሚያቆምን ምንም ምድራዊ ኃይል የለም” ሲሉም ተናግርዋል። “ዛሬ ከነቀምት በማውጀው አዋጅ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ መረዳት ያለበት የኦሮሞ አንድነት የማይጠበቅ ከሆነ የኢትዮጵያ አንድነት ሊጠበቅ አይችልም። ኦሮሞ ሠላም ካልሆነ ኢትዮጵያ ሠላም አይኖራትም። ኦሮሞ ታላቅ ነው።ራሱን ለውጦ አገር ይለውጣል” በማለት ተናግረዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በድጋሜ እና ቀሪ ምርጫ አንሳተፍም ሲሉ እናት ፓርቲ እና መኢአድ አስታወቁ፡፡

የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት አንደኛዉ መገለጫ ሕዝብ በነፃ ምርጫ በመረጠዉ አካል እንዲተዳደር መቻሉ መሆኑ ነው የሚለው መግለጫው፡፡

በአገራችን ኢትዮጵያ በ6ተኛዉ ዙር አገር አቀፍ ምርጫ ወቅት ምርጫ ባልተከናወነባቸዉና ድጋሜ ምርጫ በሚደረግባቸዉ አካባቢዎች ምርጫ ለማካሄድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

የተጠቀሰዉን ምርጫ አስመልክቶ አገር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሥር ከመሆኗ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ሁኔታ አኳያ ምርጫ ለማካሄድ አስቻይ ኹኔታዎች እንደሌሉ በመጥቀስ አስቻይ ሁኔታዎች እስኪፈጠሩ ምርጫዉ እንዲዘገይ ቦርዱን በደብዳቤ መጠየቃችን ይታወሳል የሚለው የፓርቲዎቹ መግለጫ፡፡

ይሁን እንጂ ቦርዱ ያቀረብነዉን ጥያቄ ከግንዛቤ በማስገባት የተጠየቀዉን ማስተካከያ ማድረግ ባለመቻሉ በተጠቀሰዉ ቀሪና ድጋሜ ምርጫ የማንሳተፍ መሆናችንን ለሕዝባችን በይፋ እናደርጋለን ሲሉ ለጣብያችን በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/06/26 05:16:03
Back to Top
HTML Embed Code: