Telegram Web Link
🕊

[ † እንኳን ለእናታችን ቅድስት እሌኒ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! †


🕊  †   እሌኒ ንግሥት   †   🕊

† ቅድስት እሌኒ የታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ እናቱና እግዚአብሔር ለበጐ አገልግሎት የጠራት ቡርክት ሴት [ንግሥት] ናት::

ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-

የቅድስቲቱ ሃገረ ሙላዷ ሮሃ [ሶርያ] አካባቢ ነው:: ነገዷ ከእሥራኤል ዝርዋን እንደሆነም ይነገራል:: ጣልያኖች "Helena" : በእንግሊዝኛው "Helen" ይሏታል:: እኛ ደግሞ "እሌኒ" እንላታለን:: ትርጓሜው "ጥሩ ምንጭ" : አንድም "ውብና ደግ ሴት" ማለት ነው::

ቅድስት እሌኒ በመልካም ክርስትና አድጋ እንደ ቤተ ክርስቲያን መተርጉማን ተርቢኖስ የሚባል ነጋዴ አግብታ ነበር:: ወቅቱም ዘመነ ሰማዕታት ነበር:: በማይሆን ነገር ጠርጥሮ ባሕር ላይ ጥሏት ንጉሥ ቁንስጣ አግኝቷታል:: እርሱም የበራንጥያ [የኋላዋ ቁስጥንጥንያ] ንጉሥ ነበር::

ቅድስት እሌኒ ከቁንስጣ የተባረከ ልጅን ወለደች:: ቆስጠንጢኖስ አለችው:: በልቡናው ፍቅርን : ርሕራሄን : መልካምነትን እየዘራች አሳደገችው:: ቅዱሱ አባቱ በሞተ ጊዜ ተተክቶ ነገሠ::

ቅድስት እሌኒንም ንግሥት አደረጋት:: ያንን የአርባ ዓመት ግፍ በአዋጅ አስቀርቶ ለክርስቲያኖች ነፃነትን : ክብርን በይፋ ሰጠ:: አንድ : ሁለት ብለን የማንቆጥረውን ውለታ ለምዕመናን ዋለ:: ከነዚህ መልካም ምግባራቱ ጀርባ ታዲያ ቅድስት እናቱ ነበረች::

ቅድስት እሌኒ ጾምን : ጸሎትን ከማዘውተሯ ባሻገር አጽመ ሰማዕታትን ትሰበስብ : አብያተ ክርስቲያንን ታሳንጽ : ለነዳያንም ትራራ ነበር:: በኢየሩሳሌምና አካባቢው ብቻ ከሰማንያ በላይ አብያተ መቃድስ አሳንጻለች:: እነዚህንም በወርቅና በእንቁ ለብጣቸዋለች::

በዘመኗ መጨረሻም የጌታችንን ቅዱስ ዕፀ መስቀል ከተቀበረበት አውጥታ ለዓለም በረከትን አስገኝታለች::

እናታችን ቅድስት እሌኒ እንዲህ በቅድስና ተመላልሳ በሰማንያ ዓመቷ በ፫፻፴ [330] ዎቹ አካባቢ ዐርፋለች:: ቤተ ክርስቲያናችንም ስለ ቅድስናዋና ውለታዋ በዓል ሠርታ : ታቦት ቀርፃ ስታከብራት ትኖራለች::

† ከቅድስት እናታችን ምልጃና በረከት አምላካችን ያድለን::

🕊

[ †  ግንቦት ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. ቅድስት እሌኒ ንግሥት
፪. ቅዱስ ስልዋኖስ

[ † ወርኀዊ በዓላት ]

፩. አባ በርሱማ ሶርያዊ [ለሶርያ መነኮሳት ሁሉ አባት]
፪. አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ [ኢትዮጵያዊ]
፫. ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ቅዱሳን ሊቃውንት [ርቱዐነ ሃይማኖት ዘኒቅያ]
፬. የብሔረ ብፁዐን ጻድቃን
፭. አባ መልከ ጼዴቅ ዘሚዳ [ኢትዮጵያዊ]
፮. ቅዱስ ዞሲማስ ጻድቅ [ዓለመ ብፁዐንን ያየ አባት]

" ነገር ግን ለበጐ ነገር ጥበበኞች : ለክፉትም የዋሆች እንድትሆኑ እወዳለሁ:: የሰላምም አምላክ ሰይጣንን ከእግራችሁ በታች ፈጥኖ ይቀጠቅጠዋል:: የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን:: " † [ሮሜ. ፲፮፥፲፱]

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
#ቅዱስ_ያዕቆብ ዘሥሩግ እንዲህ አለ:-

#በቅድስና_ውበት ስለተሞላችው ንጽሕት ትሕት እናገር ዘንድ አንደበቴ ብቁ አይደለም፡፡ ... የተራ ቀለማት
መዋሐድ ለማይመጥኗት ለዚህች እጅግ ክብርት እንዴት ያለ ሥዕልን ልሣል? ውበትዋ ከእኔ መጠበብ በላይ ነው ፤ አእምሮዬም እንዲሥላት አልፈቅድለትም፡፡

#የድንግል_ማርያምን ክብርዋን ከመግለጥ ፀሐይን ከነብርሃንዋና ከነሙቀትዋ መሣል ይቀልላል፡፡ ምናልባት የፀሐይ ጨረር በሥዕል ሊቀመጥ ይችል ይሆናል፡፡ ስለ እርስዋ የሚነገረውን ነገር ግን አሟልቶ ለመስበክ አይቻልም፡፡

እርስዋን ከነማን ጋር መመደብ ይቻላል? ከደናግል ጋር? ከቅዱሳን ጋር? ከንጹሐን ጋር? ካገቡ ሴቶች ጋር? ከእናቶች ጋር? ከአገልጋዮች ጋር? እነሆ የድንግልናን ማኅተም ከወተት ጋር የያዘ ሰውነትዋን እዩ! መውለድዋንም ከታተመ ማኅፀንዋ ጋር እዩ! ከደናግል መካከል ናት ስል ሕፃን ይዛ ስታጠባ አያታለሁ! ከዮሴፍ ጋር ትኖራለች ስል በጋብቻ ቃልኪዳን እንዳልታሠረች አያለሁ!

#ስለ_እርስዋ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል ፤
የክብርዋ ከፍታ ግን ያስቸግረኛል፡፡ ከቶ ምን ባደርግ
ይሻለኛል? ስለ እርስዋ ለመናገር ብቁ እንዳልሆንሁ
በግልፅ እናገራለሁ፡፡ ከፍቅር የተነሣ ግን ተመልሼ
መናገር ያምረኛል፡፡...

ሱራፌል ከእሳቱ የሚሸሸጉለትን የእርሱን ከንፈሮች በቡሩካን ከነፈሮችዋ የሳመች እርስዋ የተባረከች ናት! ዓለማት ሕይወትን የጠጡበትን ምንጭ እርሱን ያጠባች እርስዋ የተባረከች ነች’

(የብርሃን እናት ገፅ 352)


             #_ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
🕊

[ † እንኳን ለቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †


🕊  † ቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ  †  🕊

† አናንያ : አዛርያና ሚሳኤልን እንዲያው በቀድሞው አጠራር ሠለስቱ ደቂቅ [ሦስቱ ሕጻናት] እንላቸዋለን እንጂ ለእኛስ በእድሜም : በጸጋም : በትሩፋትም አባቶቻችን ናቸው::

ቅዱሳኑ የወቅቱ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጆች ናቸው:: ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን አቃጥሎ ሕዝቡን ሲማርክ አብረው ተማርከው ባቢሎን ወርደዋል::

ንጉሡ ከምርኮ ወጣቶች ለቤተ መንግስት ሲመርጥ ሦስቱ ቅዱሳንና ዳንኤል ተመርጠው የምቾት ሕይወት ተዘጋጅቶላቸው ነበር:: ነገር ግን በምግብና በአምልኮ ከአሕዛብ ጋር መተባበርን አልፈለጉምና ምርጫቸው ጾምና ጸሎት ከቆሎ ጋር ሆነ:: ምንም እንኳ በቤተ መንግስት ውስጥ ቢኖሩ : ምንም የነገሥታት ልጆች ቢሆኑ ለእነርሱ ከእግዚአብሔር ፍቅር የተሻለ አልነበረምና በጥሬ ቆሎ ተወስነው ኖሩ::

አምላካቸው ከሃሊ ነውና በውበትም ሆነ በጥበብ በባቢሎን ምድር ከነርሱ የሚደርስ አልተገኘም:: ንጉሡም በባቢሎንና በአውራጃዋ ላይ ሾማቸው:: ስማቸውንም በአማልክቱ ስም ሲድራቅ : ሚሳቅና አብደናጐ አላቸው::

ከነገር ሁሉ በኋላ አሕዛብ ቀንተውባቸዋልና የክፋት አዋጅን አሳወጁ:: ናቡከደነጾር ፷ [60] ክንድ ቁመት ያለውን የወርቅ ምስል አቁሞ "ስገዱ" ቢላቸው አይሆንም በማለታቸው ተቃጥለው እንዲሞቱ እሳት ተፈረደባቸው:: ነበልባሉ ከጉድጓዱ ወደ ላይ ፵፱ [49] ክንድ ቢነድም ቅንጣት ያህል ፍርሃት አልጎበኛቸውም::

ወደ እሳቱም ሲጥሏቸው መልዐከ አድኅኖ ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ አዳናቸው:: ከሆነው ነገር የተነሳ አሕዛብ አፈሩ:: ናቡከደነጾር ግን ከዙፋኑ ተነስቶ የቅዱሳኑን አምላክ እግዚአብሔርን ባረከ::

ከዚያች ቀን በኋላ አናንያ : አዛርያና ሚሳኤል በአት አጽንተው : በጾምና በጸሎት ተወስነው ኑረዋል:: ነፍሳቸው ከሥጋቸው ስትለይ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆኗል:: ቅዱስ ዳንኤልና ናቡከደነጾር ተሯሩጠው ቢሄዱ ሦስቱም በአንድነት ዐርፈው ተገኝተዋል:: ንጉሡ በእጅጉ ይወዳቸው ነበርና በወርቅ በተለበጠ ሳጥን ቀብሯቸዋል:: ስሞት ከመካከላቸው ቅበሩኝ በማለቱ ዛሬ ድረስ ለበቁ አባቶች የአራቱ መቃብር ባቢሎን ውስጥ ይታያል::

ቅዱሳን አናንያ : አዛርያና ሚሳኤል [ሲድራቅ : ሚሳቅና አብደናጐ] ያረፉት ግንቦት ፲ [10] ቀን ሲሆን ዘመኑም ከክርስቶስ ፭፻ [500] ዓመት በፊት ነው::

† አምላካቸው ከእሳት ባወጣቸው ቀንም :-
"ይትባረክ እግዚአብሔር አምላከ አበዊነ::
ስቡሕኒ ውዕቱ ወልዑልኒ ውዕቱ ለዓለም::" የሚለውን ምስጋና ፈጣሪ ገልጾላቸው ደርሰውታል:: [በእሳቱ ውስጥ ሆነው ተናግረውታል::]

ድርሰታቸው ፪ [2] ወገን ሲሆን ባለ ስድስት አንቀጹ ምስጋናቸው ከ፮፻ [600] ዓመት በኋላ ክርስቶስ እንደሚወለድ የሚያሳይ ነው:: ሌላኛውና ፴፫ [33] አንቀጾች ያሉት ምስጋናቸው ደግሞ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ለ፴፫ [33] ዓመታት እንደሚመላለስ ያጠይቃል::

ቅዱሳን ሠለስቱ ደቂቅ ካረፉ ከ፱፻ [900] ዓመታት በኋላ [ማለትም ከክርስቶስ ልደት በ፬፻ [400] ዓመታት] ታላቁ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ቤተ ክርስቲያንን አንጾላቸው ነበርና አጽማቸውን ሊያገኝ ተመኘ::

ወዳጁን ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ጠርቶ "አባ! አጽመ ቅዱሳንን ባቢሎን ወርደህ አምጣልኝ?" አለው:: ቅዱሱ ሐጺር ዮሐንስም በደመና ተጭኖ ባቢሎን ገባ:: በቅዱሳኑ መቃብር ፊትም ሰግዶ አለቀሰ:: ሠለስቱ ደቂቅም "ወዳጃችን! ምን ሆንክ?" አሉት::

ቅዱሱም መልሶ "ወደ ግብጽ እንሒድ:: አባ ቴዎፍሎስ ይፈልጋቹሃል" አላቸው:: እነሱም "ለቅዱሱ ቴዎፍሎስ እንዲህ በለው:: እግዚአብሔር ዋጋህን ይክፈልህ:: ግን አጽማችን እስከ ዓለም ፍጻሜ ባቢሎንን አይለቅም:: ለክብርህ ግን እንመጣለን::"

"ለምልክትም ይሆን ዘንድ መብራት ሳታበራ በሌሊት ጠብቀን በለው" ብለው ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርን ባርከው ሸኙት:: ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርም መጥቶ መልእክቱን አደረሰ:: በዕለተ ቅዳሴ ቤታቸው ቅዱሳን:- ቴዎፍሎስ : ቄርሎስ : ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርና ሌሎችም ከምዕመናን ጋር በጨለማ ሳሉ ቤተ ክርስቲያኑ ቦግ ብሎ በራ::

እጅግ የሚደነቅ ብርሃንም ከበባቸው:: በብርሃኑ መካከል ሠለስቱ ደቂቅ ሲያልፉ በጐ መዓዛ ሸተተ:: ሕዝቡም በደስታና በዝማሬ የቅዱሳኑን ቅዳሴ ቤት አክብሯል::

† በረከታቸው ይደርብን::

🕊

[ † ግንቦት ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. ሠለስቱ ደቂቅ ቅዱሳን [አናንያ : አዛርያና ሚሳኤል]
፪. ቅዱስ አብርሃም ጸራቢ [ሰማዕት]
፫. አባ ሚካኤል ገዳማዊ
፬. አባ ይስሐቅ ግብጻዊ

[ †  ወርሐዊ በዓላት ]

፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
፫. ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ ጻድቅ ንጉሥ
፬. አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
፭. ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ]
፮. ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
፯. ቅዱስ ዕፀ መስቀል

† " ናቡከደነፆርም መልሶ:- መልአኩን የላከ : ከአምላካቸውም በቀር ማንንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን : የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን : በእርሱ የታመኑትን ባርያዎቹን ያዳነ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ:: " † [ዳን.፫፥፳፰] (3:28)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
#እንካ_ሰላምታ_

🙎‍♂ እንካ ሰላምታ፦
👉👨‍🔧ምን አይነት ሰላምታ?
🙎‍♂
#በፀሎት
👉👨‍🔧 ምን አለ በፀሎት?
🙎‍♂ምህረቱ በበዛ በእግዚአብሔር ቸርነት፣
ከሳጥናኤል ቀንበር ወጣን ከባርነት።

👨‍🔧አንካ ሰላታ
👉🙎‍♂ ምን አይነት ሰላምታ?
👨‍🔧
#በጦፍ
👉🙎‍♂ምን አለ በጦበጦፍ?
👨‍🔧 ንጹህ ደም ለማፍሰስ ጠላቴ ሲሰለፍ፣
ለራሱ ታዘዘ ለእኛ የመጣው ሰይፍ

🙎‍♂እንካ ሰላታ፦
👨‍🔧ምን አይነት ሰላምታ?
🙎‍♂
#በከበሮ
👨‍🔧ምን አለ በከበሮ?
🙎‍♂ ጥበበኛው ሰይጣን በጥበብ ተሽሮ፣
ሲኦል ስትማረክ ተመልሷል አፍሮ።

👨‍🔧እንካ ሰላምታ፦
🙎‍♂ምን አይነት ሰላምታ?
👨‍🔧
#በወይን
🙎‍♂ምን አለ በወይን?
👨‍🔧በቀራኒዮ መስቀል የፈሰሰለትን፣
የሰው ልጅ ካልበላ ስጋውን እና ደሙን፣
ያን! ሰማያዊ ቤት አይወርስም ርስቱን።

🙎‍♂ እንካ ሰላምታ፦
👨‍🔧ምን አይነት ሰላምታ?
🙎‍♂
#በስግደት
👨‍🔧ምን አለ በስግደት?
🙎‍♂ጉንብስ ቀና ስንል በመንፈስ በእምነት፣
እንደ ሰም ቀለጠ የሳጥናኤል ጉልበት።

👨‍🔧እንካ ሰላምታ፦
🙎‍♂ ምን አይነት ሰላምታ?
👨‍🔧
#በበገና
🙎‍♂ምን አለ በበገና?
👨‍🔧ለናዝሬቱ ኢየሱስ እናቅርብ ምስጋና፣
ከባርነት ቀንበር አውጥቶናልና።

እንኩ ሰላምታ
በምንታ
#በሰማይ_በምድር
ምን አለ በሰማይ በምድር
ከአለም ትሰፋለች የአምላክ እናት
#ድንግል_ማርያም

             #_ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
                        †                        

🕊  💖        ሰ ላ ም ታ        💖  🕊

❝ ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤
አሠሮ ለሰጣን
▸ አግዐዞ ለአዳም ፤
ሰላም
▸ እምይእዜሰ ፤
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም ❞

🕊

❝ ክርስቶስ በታላቅ ኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው ፤ አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ❞

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[ ❝ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ❞ ]

[ አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት ንጉሠ ነገሥት ወእግዚኣ አጋእዝት አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት… ኦ ትዕግሥት ወአርምሞ በፍቅረ ዚአነ በጽሐ እስከ ለሞት አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት ወንሕነኒ ንግበር በዓለነ ቅድስተ ፋሲካ በሐሴት አርአየ ሥልጣኖ ላዕለ ሞት ገባሬ ሕይወት ክርስቶስ ፤

ትርጉም ፦ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ፣ የነገሥታት ንጉሥ የጌቶች ጌታ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ፣ … ወዮ ትዕግሥትና ዝምታ ፣ እኛን ከመውደዱ የተነሣ እስከ መሞት ደረሰ ፣ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ ፣ እኛም የተቀደሰች በዐላችንን ፋሲካን [ ትንሣኤን ] በደስታ እናክብር ፣ ሕይወትን የሠራ [ የፈጠረ ] ክርስቶስ በሞት ላይ ሥልጣኑን አሳየ።

[ ድጓ ዘፋሲካ ]

🕊

❝ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን ከይዶ መቃብሪሁ ለአዳም ወበትንሣኤሁ ገብረ ለነ ሰላመ ለጻድቃን አብርሃ ፤

ትርጉም ፦ የአዳምን መቃብር ረጋግጦ ክርስቶስ ከሙታን ተነሣ ፣ በትንሣኤውም ለጻድቃን ብርሃን የሚሆንን ሰላምን ለእኛ አደረገልን። ❞

[ድጓ ዘፋሲካ]


†                       †                         †
💖                    🕊                     💖
                        †                        

🕊  💖  የኢትዮጵያ ብርሃን  💖  🕊

🕊

" ኢትዮጵያ ከመላእክት ጋር የሚዘምር ማሕሌታዊ ከካህናተ ሰማይ ጋር የሚያጥን ካህን የምታፈራ ሀገር ናት። ለሰማይ አገልጋዮችን ገና ሳይሞቱ የምትልክ፣ ከተዋጊዎች መካከል ወደ ድል ነሺዎች መልእክተኛ የምትልክ ቤተ ክርስቲያን እንዴት ያለች ናት ? !

ቅዱስ ያሬድ በትሕትናው ከትል ተማረ። ትሑታንን ከፍ የሚያደርግ ፈጣሪም ከፍ አደረገውና ከመላእክት ጋር ዘመረ። ትልዋን ከዛፍ አውርዶ ቢጨፈልቃት ኖሮ ለአንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመታት ያልነጠፈው የምስጋና ጅረት በሀገራችን ባልፈሰሰ ነበር። ኃይል አለኝ ብለህ የምትጨፈልቃቸው ትሎች ሰማይ የሚያደርሱህ መምህራኖችህ እንዳይሆኑ ተጠንቀቅ ይላል የታሪኩ ተግሣፅ።

ቅዱስ ያሬድ እግሩን በጦር እየተወጋ እንኩዋን ዝማሬው ሰማያት ወስዶት አልተሰማውም ነበር። የእኛው ሲላስ የእኛው ጳውሎስ ቅዱስ ያሬድ ሆይ በዘመርክባት ሀገርህ ዛሬ ብዙ ጦር ተሰክቶባታል። ከአንተ ዜማ በቀር ዛሬም መጽናኛ የለንምና በምልጃህ አስበን።

ጥዑመ ልሳን ያሬድ: ሊቀ ጠበብት ያሬድ: ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ የቤተ ክርስቲያን ጌጥ !! "

[ ዲ/ን ሔኖክ ሃይሌ ]


†                       †                         †
💖                    🕊                      💖
2024/09/29 07:26:40
Back to Top
HTML Embed Code: