Telegram Web Link
የወያኔ ሙርኮኛው ቄሮን መጨፍጨፍ አለብት በሚል እና ህውሃትን የድንጋይ ሥር እባብ ብሎ በመሳደብ የሚታወቀው ካሳዬ ጨመዳ ስለ ኢትዮኤርትራ ጦርነት ዛሬ ይሄንን ብሏል

" የኢትዮጲያ ትንሳኤ ደርሷል በቅርቡም ይፈፀማል ያውም በዚህ አመት በዙሪያችን ያሉ ጥጋበኛ ጠላቶቻችንን እናስወግዳልን ፈጣሪም ከኢትዮጲያ ጋር ነው ይረዳናል "

#ማስታወሻ

የኦሮሞ ህዝብ ከመቼውም በላይ ስላምን ልማትን እንጂ በየቦታው በጦርነት ስብስብ መማገድ አይደለም ኦሮምያ ላይ ያለው ጦርነት በድርድር ይጠናቀቅ የኦሮሞ ወጣት ወደ ትምህርት ወደ ልማት ፊቱን ያዙር።
ወለጋ በርሃብ አለንጋ ተገርፎ መንገድ ላይ የሚሞተው እና ፊንፊኔ ሴተኛ አዳሪ ሲጫረት የሚያድረውን እኩል ባለግዜ ማለት ነውረኝነት ነው የኦሮሞ ህዝብ በስላም እጦት እየተስቃየ ነው የኦሮሞ ወጣት ትምህርት እና ልማት ነው ሚያስፈልገው ከሌላ ህዝብ ጋር እየተበሻሸቁ ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ የኦሮሞ ህዝብ ጠላት ሽመታ ሊቆም ይገባል።
.
.
.
በመንግሥት እና በ WBO መካከል የተጀመረው ድርድር ዳግም ተጀምሮ በስላም እንዲጠናቀቀ ከሁሉም በላይ እኛ ግፊት ልናደርግ ይገባል ልዩነቶችን ማጥበብ ይቻላል የኦሮሞ ህዝብ ከመቼውም በላይ ስላም አግኝቶ የኦሮሞ ወጣት ወደ ሥራ ወደ ትምህርት እንዲመለስ እንፈልጋለን ለዚህ ደሞ ሁላችንም በአንድነት ለሁለቱ ሃይሎች ጥሪ ማድረግ አለብን ሁለቱ ከተስማሙ አትራፊው የኦሮሞ ህዝብ ነው
ለምዕራብ ወለጋ ቤጊ ቆንዳላ ወገኖቻችን አስቸኳይ የምግብና መድኃኒት እርዳታው አሁንም አጠናክረን እንቀጥል። ከ3.2 ሚሊዩን ብር ወጭ የተደረገባቸው አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ከመካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን አፋን ኦሮሞ ፊንፊኔ የተበረከታ ድጋፍ ተደርጓል ። ፈጣሪ ይባርካችሁ 🙏
አሁንም አነሰ በዛ ሳንል ድጋፋችን እንቀጥል!!
Negash Qemant
ኢሬቻ መልካ አሶሳ⚫️🔴⚪️
#Ethiopia: Local charities call for urgent malaria relief response in Western #Oromia

Two local charity organizations warn that the malaria epidemic in #Western_Oromia could worsen in the next two months if not promptly addressed.

More than 70% of the population in #West_Wollega and 60% in #Kellem_Wollega are at high risk.

Urgent funding and government action are needed.

https://addisstandard.com/asdailyscoop-local-charities-call-for-urgent-malaria-relief-response-in-western-oromia/
#አዛምተው

የኦሮሞ አባ ገዳዎች በኦሮሚያ ሰላም እንዲሰፍን ጠየቁ።

አባ ገዳዎቹ ከሆረ ፊንፊኔ ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች እየተከበረ ባለው የኢሬቻ ቀአል ላይ ሰላም እንዲሰፍን በመጠየቅ ላይ ናቸው።

በኦሮሚያ በኢትዮጵያ መንግሥትና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መካከል አየተደረገ ያለው ጦርነት አመታትን ዘልቋል።

በኦሮሚያ አመታትን ያስቆጠረው ጦርነት ህይወትን እየቀጠፈ፣ ሀብት ንብረት እያወደመ፣ በክልሉ ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስን እያስከተለ ዛሬም ቀጥሏል።

በአንድ በኩል በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እና በመንግስት ሃይሎች መካከል የሚደረገው ጦርነት የብዙ ንፁሃን ዜጎችን ህይወት እየቀጠፈ ይገኛል።

በሌላ በኩል ደግሞ የአማራ ፅንፈኛ ቡድን ፋኖ ታጣቂዎች የኦሮሚያን ወሰን ጥሰው በመግባት መሬት ለመውረር በሚያደርጉት ሙከራ ንፁሃንን እየገደሉ፣ እየዘረፉ እና እያፈናቀሉ ችግር ተባብሶ ቀጥሏል።

ከየአቅጣጫው አደጋ የተቃጣበት ህዝብ በጦርነት፣ በረሃብ እና በበሽታ ለከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ተዳርጓል።

እናም ይህንን ህዝቡ ያለበትን ሰቆቃ ማብቂያ ያገኝ ዘንድ የኦሮሞ አባ ገዳዎች ከሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ ጀምሮ አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች መከበረ በቀጠለው በኢሬቻ በአል ላይ ስለሰላም በማስተጋባት ላይ ይገኛሉ።

ትናንት በምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ በተከበረው የኢሬቻ በአል ልይም አባ ገዳዎች እና የሀገረ ሽማግሌዎች የሰላም ጥሪ መልክት አስተላልፈዋል።

ትናንት ጥቅምት 11/2016 በምስራቅ ሸዋ ዞን ፈንታሌ ወረዳ በተከበረው የሆራ በሰቃ የኢሬቻ በአል ላይ አባ ገዳዎች፣ ሃdha ሲቄዎች፣ ቄሮዎች እና ቀሬዎች ተገኝተው ነበር።

እናም በዚህ የኢሬቻ በአል ላይ አባ ገዳዎች መልክት ያስተላለፉ ስሆን ኢሬቻ የይቅርታ፣ የእርቅና የአንድነት በአል መሆኑን ተናግረዋል።

አባ ገዳዎቹ በኦሮሚያ በቀጠለው ጦርነት ውስጥ የሚጎዱት ንፁሃን መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ተፋላሚ ሃይሎቹ ይህን በማሰብ ይቅር በመባባል ሰላም የሰፈነባት ኦሮሚያን ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ ተገቢ ነው ብለዋል።

በተመሳሳይ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ በትናንትናው እለት በተከበረው የኢሬቻ በአል ስነስርዓት ላይ የተገኙ አባ ገዳዎች ኢሬቻ የአንድነት መገለጫ በመሆኑ "ያሉንን ልዩነቶች በመተው በመተሳሰብ እና በመፈቃቀር አንድ ሆነን በሀገራችን ሰላም እንዲሰፍን የበኩላችንን አስተዋጽኦ ማበርከት አለብን" በማለት ጥሪ አቅርበዋል።
OMN

https://www.tg-me.com/danny4677
ሽመልስ አብዲሳ እና ጃል መሮ ከሚያራርቃቸው ይልቅ ደማዊ ማነታቸው አንድ ያደርጋቸዋ ።
በድርድር ሰላም እንዲያመጡ ሁላችንም ጫና መፍጠር አለብን !
#UNICEF reports 7.6 million Ethiopian children unable to attend school amid disasters, conflicts
reliefweb.int/report/ethiopi
አስደሳች ዜና ለመላው የአገው ህዝብ 😊

የአገው ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር ህገ መንግስታዊ መብት ጥያቄ ላይ ህዝበ ውሳኔ እንዲሰጥበት በድጋሜ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ.ፌዴሬሽን ም/ቤት በዛሬው ዕለት በአስተባባሪው ኮሚቴ በደብዳቤ ተጠየቀ፦
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የአዊ ህዝብ ከሌሎች የሀገራችን ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ጋር በጋራ በመሆን በኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ የአንበሳውን ድረሻ የተወጣ መሆኑ የማይካድ ሀቅ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ራስን በራስ ለማስተዳደር መብት ተነፍጎ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ ዊንግስት በሚባለው ክልል ስር ተዋቅሮ ልዩ የብሔረሰብ ዞንነት ተሰጥቶት ይገኛል።

በመሆኑም በዛሬው ዕለት ማለትም ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ/ም የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ በለ98 ገፅ ሠነድ ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፌዴሬሽን ም/ቤት በአስቸኳይ የአገው ህዝብ ክልል የመሆን ህዝበ ውሳኔ እንዲሰጥበት በደብዳቤ ጠይቋል።

መላው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የአገው ህዝብ አሁን ላይ ህልውና በመኖርና በመጥፋት አዳጋ ላይ ያለ መሆኑን ተረድታችሁ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንድታደርጉልን የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ በአፅንዖት ይጠይቃል።

የአገው ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በህገ መንግስቱ መሠረት ዕውን ይሆናል!!!
https://www.tg-me.com/danny4677
ኦሮምያ ውስጥ ለሚደረገው እርስ በእርስ ጦርነት ማንም ጀግና ማንም አሸናፊ ማንም ተሸናፊ የለም ።ነገር ግን ዋጋ እየከፈለ ያለው ንፁኃኑ ብቻ ነው ።

መሶቡን ይዞ ለትሪ መጣላት ሞኝነት በድርድር. በንግግር የማይፈታ ነገር የለም
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የግዜ ጉዳይ ካልሆነ ኣሰብ የኢትዮጵያ መሆኑን ኣይቀርም፣ ያ ካልተደረገ ግን መፈንዳቱ ኣይቀርም
” ጀነራል ፃድቃን!
ኦሮምያ ውስጥ የሁለት ወንድማማቾች ደም አፋሳሽ ጦርነት ቆሞ በድርድር መፍታት አለበት የምለው በመሀል ምስኪኑ ንፁሀን እያለቀ እየተፈናቀለ ስለሆነ ነው ከታች ያለውን የአዲስ ማለዳ ዜና አንብቡት !!


በኦሮሚያ ክልል ግጭት በተቀሰቀሰባቸው አካባቢዎች 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ተፈናቅለዋል ተባለ

በኦሮሚያ ክልል ግጭት በተቀሰቀሰባቸው አካባቢዎች 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች መፈናቀላቸውን ሴንተር ፎር ዴቭሎፕመንት ኤንድ ካፓሲቲ ቢዩልዲንግ (CDCB) አስታወቀ።

ድርጅቱ በክልሉ ስላለው ኹኔታ አስመልክቶ ባወጣው ሪፖርት፤ “በክልሉ እየተካሄደ ያለው ግጭት ካስተለው መፈናቀል በተጨማሪ፤ የሰው ሕይወት ጠፍቷል፣ ንብረት ወድሟል እንዲሁም የልማት እንቅስቃሴዎች ተቀዛቅዘዋል” ያለ ሲሆን፤ የሕዝቡም ማህበራዊ ትስስር መሸርሸሩን ጠቁሟል፡፡

ድርጅቱ አደረኩት ባለው ጥናት መሰረት በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል 1 ሚሊየን 292 ሺሕ 323 ሰዎች ተፈናቅለዋል ያለ ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ 374 ሺሕ 400 ወይንም 29 በመቶ የሚሆኑት ብቻ በመጠለያ ጣቢያዎች ውስጥ ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ገልጿል፡፡

የተቀሩት 71 በመቶ የሚሆኑት ተፈናቃዮች ደግሞ በማህበረሰቡ ውስጥ ተበታትነው እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡

ድርጅቱ በዩኤስኤይዲ ትብብር ባዘጋጀው በዚህ ሪፖርት፤ በተለይም በምስራቅ ወለጋ እና ምዕራብ ወለጋ ያለው ኹኔታ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን፤ ከአጠቃላይ ተፈናቃዮች ውስጥ  859 ሺሕ ወይንም 66 በመቶ የሚሆኑት ከኹለት ዞኖች ብቻ የተፈናቀሉ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡

በተጨማሪም በክልሉ ያለው ግጭት በትምህርት ላይ ያመጣውን ተፅዕኖ በዝርዝር ያስቀመጠው ሪፖርቱ፤ በክልሉ 739  ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን እንዲሁም ከ210 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ መሆናቸውን ገልጿል።

1 ሺሕ 117 መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎች ከሥራቸው ገበታቸው ውጪ መሆናቸውንም ጨምሮ አመላክቷል፡፡

በተጨማሪም ድርጅቱ ከክልሉ ጤና ቢሮ አገኘሁት ባለው መረጃ መሰረት፤ ግጭት በተቀሰተባቸው አካባቢዎች የሚገኙ 208 ጤና ተቋማት ሙሉ በሙሉ፣ እንዲሁም 788 የሚሆኑት ደግሞ በከፊል መውደማቸው መገለጹን አዲስ ማለዳ ከሪፖርቱ ተመልክታለች፡፡

በዚህም 10 አምቡላንሶች መዘረፋቸውን፣ 45 የሚሆኑት መቃጠላቸውን እንዲሁም 25 ደግሞ ከአገልግሎት ውጭ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን፤ በተጨማሪም 2 ሞተር ሳይክሎች መዘረፋቸውን፣ 5 የሚሆኑት ከአገልግሎት ውጭ መሆናቸውን እንዲሁም፤ 80 የሚሆኑት ደግሞ መቃጠላቸውን ገልጿል፡፡

“በምዕራብ ኦሮሚያ ወረዳዎች እና መካከለኛው አካባቢዎች በመንግሥት እና በክልሉ በሚንቀሳቀሰው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ታጣቂዎች መካከል የሚስተዋለው ግጭት፤ እንዲሁም በተለይ በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን በፋኖ ታጣቂ ቡድን የሚደረሰው ጥቃት ውድመት አድርሷል” ሲልም ሪፖርቱ ገልጿል።

በተጨማሪም “ግጭት በተቀሰቀሰባቸው አካባቢዎች ማህበራዊ ደንቦች ተሽረዋል፣ ማህበራዊ ተቋማት ወድመዋል፤ ጭካኔ እና ሕገወጥነት የተለመደ ሆኗል።” ያለው ሪፖርቱ፤ "ለዚህም በጥቅምት ወር 2015 በምዕራብ ወለጋ ዞን ሳሲጋ ወረዳ በገሎ ቀበሌ በመካነ ኢየሱስ ቤተ ክርሰቲያን ውስጥ፤ፐለአምልኮ በተሰበሰቡ ሰዎች ላይ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት የ14 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ማረጋገጫ ነው።" ሲል ገልጿል።

ሴንተር ፎር ዴቭሎፕመንት ኤንድ ካፓሲቲ ቢዩልዲንግ (CDCB) በሪፖርቱ በክልሉ የሚስተዋሉት ግጭቶች በተለይ ሴቶች እና ሕጻናትን ለአደጋ የጣሉ መሆናቸውን የገለጸ ሲሆን፤ ቤተሰቦቻቸውን በድንገት የሚያጡ ሕጻናት ቁጥር እየጨመረ መሆኑን አስታውቋል። በተጨማሪም ባለቤቶቻቸው የሞቱባቸው ሴቶች ለዝርፊያ፣ ለአስገድዶ መድፈ እና ለተለያዩ አካላዊ ጥቃቶች እየተጋለጡ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

ስለሆነም በክልሉ የወደሙ መሰረተ ልማቶቸ እንዲስሩ ለአርሶ አደሮች ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ያለው ድርጅቱ፤ በተዋጊዎች መካከል በአስቸኳይ ሰላም እንዲወርድም በሪፖርቱ ጠይቋል።

ለደረሰውም ውድመት ከክልሉ፣ ከፌደራል መንግሥቱና ከግብ-ሰናይ ተቋማት አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
2024/09/28 23:19:55
Back to Top
HTML Embed Code: