Telegram Web Link
Forwarded from 💐🕍 አብዲ ቲዩብ๑ 💐۞๑๑۩ 💐 🕌abdi Tube ๑ 💐 (abdul jilal አቡዲ ቲዩብ)
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"እመነኝ/እመኚኝ ላለመስገድ ምንም ምክንያት የለህም/የለሽም!!!!
@abdu4321
@abdu4321
መጪው ረመዳን
በመልካም ስራ ወደ አላህ የምንቃረብበት፣ አላህ
ዘንድ የምንወደድበት ፣ወንጀላችን የሚሻርበት ፣ምንዳችን የሚበዛበት "የተወደደ"የኢባዳ ወር ይሁንልን !! 🙏🙏🙏 👉አሚን🤲🤲👇👇👀🍃@abdiiiii1
የፈቲ ባል ይቀጥላል👇👇👇👇👇👇🙏🙏
Forwarded from 💐🕍 አብዲ ቲዩብ๑ 💐۞๑๑۩ 💐 🕌abdi Tube ๑ 💐 (abdul jilal አቡዲ ቲዩብ)
Forwarded from 💐🕍 አብዲ ቲዩብ๑ 💐۞๑๑۩ 💐 🕌abdi Tube ๑ 💐 (abdul jilal አቡዲ ቲዩብ)
👆👆👆👆የፈቲ ባል የተሠኘው ፕሮግራም ላይ
ሀሣብ ካሎት
@abdiiiii1👀🍃ፃፉልን
Forwarded from 💐🕍 አብዲ ቲዩብ๑ 💐۞๑๑۩ 💐 🕌abdi Tube ๑ 💐 (abdul jilal አቡዲ ቲዩብ)
أهلاً يا رمضان شهر الإقبال على الله

ታላቁና ተወዳጁ ነቢያችን ﷺ ሶሐቦቻቸውን የረመዷንን መቃረብ አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ ብስራትን ሲገልጹ እንዲህ ይሏቸው ነበር፡-

عن أبي هريرة رضي الله عنه قال، قال رسول الله ﷺ ( أتاكم رمضان شهر مبارك فرض الله عز وجل عليكم صيامه تفتح فيه أبواب السماء وتغلق فيه أبواب الجحيم وتغل فيه مردة الشياطين لله فيه ليلة خير من ألف شهر من حرم خيرها فقد حرم )

(صحيح رواه أحمد 9/225 ( الفتح الرباني ) والنسائي 4/129 وصححه الألباني في الترغيب 1/490).

«የተባረከ ወር የሆነው ረመዷን መጣላችሁ!፡፡ አላህ ጾሙን በናንተ ላይ ግዳጅ አድርጓል፡፡ በዚህ ወር የሰማይ ደጃፎች ይከፈታሉ፡፡ የጀሀነም ደጃፎች ይዘጋሉ፡፡ አመጠኛ ሸይጣናት ይታሰራሉ፡፡ አላህ ከአንድ ሺህ ወር (ስራ) የምትበልጥ የሆነች አንድ ለሊት አለችው፡፡ የዚህን ወር መልካም ነገር የተነፈገ ሰው በርግጥም ከብዙ መልካም ነገራት የተነፈገ ነው፡፡»

قال تعالي { شهر رمضان الذي أنزل فيه القرآن هدي للناس وبينات من

الهدي والفرقان } ( البقرة / 185 )

@abdu4321
@abdu4321
Forwarded from 💐🕍 አብዲ ቲዩብ๑ 💐۞๑๑۩ 💐 🕌abdi Tube ๑ 💐 (abdul jilal አቡዲ ቲዩብ)
*ሱራህ 26, አያህ 78*
ٱلَّذِى خَلَقَنِى فَهُوَ يَهْدِينِ
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
وَٱلَّذِى هُوَ يُطْعِمُنِى وَيَسْقِينِ
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
وَإِذَا مَرِضْتُ فَهُوَ يَشْفِينِ
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡

وَٱلَّذِى يُمِيتُنِى ثُمَّ يُحْيِينِ
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
وَٱلَّذِىٓ أَطْمَعُ أَن يَغْفِرَ لِى خَطِيٓـَٔتِى يَوْمَ ٱلدِّينِ
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
رَبِّ هَبْ لِى حُكْمًۭا وَأَلْحِقْنِى بِٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
وَٱجْعَل لِّى لِسَانَ صِدْقٍۢ فِى ٱلْـَٔاخِرِينَ
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡

@abdu4321
@abdu4321
Forwarded from Deleted Account
በወርሃ ረመዳን በብዛት የሚያጋጥሙ ስህተቶች

1. ከመጠን በላይ መመገብ፡-
ይሄ ችግር በተለይም ረመዳን ላይ በሰፊው ይስተዋላል፡፡ ያለመጠን መመገብ ለብዙ ሸር መንሰኤ ነው፡፡ ሱፍያን አሥሠውሪ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “አካልህ ጤናማ እንዲሆን፣ እንቅልፍህ እንዲቀል ከፈለግክ ምግብህን አቅልል፡፡” ጌታችን እንዲህ ይላል፡-
وَكُلُوا وَاشْرَبُوا وَلَا تُسْرِفُوا ۚ إِنَّهُ لَا يُحِبُّ الْمُسْرِفِينَ
“ብሉ ጠጡ፡፡ አታባክኑ፡፡” [አልአዕራፍ፡ 31]
ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ቀይም አልጀውዚያ ረሒመሁላህ ከዚች አንቀፅ ቀጥለው እንዲህ ይላሉ፡- “ባራገፉት ፋንታ ሰውነታቸውን የሚያቆሙበት ምግብና መጠጥ እንዲያስገቡ ባሮቹን ጠቆማቸው፡፡ መጠኑም አይነቱም አካላቸው በሚጠቀምበት መጠን እንዲሆንም አሳሰባቸው፡፡ ይህንን ባለፈ ጊዜ ብክነት ይሆንበታል፡፡ ሁለቱም ጤናን ጎጅ፣ በሽታን ጎታች ነው፡፡ ማለትም አለመብላትና አለመጠጣት እንዲሁም በምግብና በመጠጥ ድንበር ማለፍ፡፡” [አጥጢቡ አንነበዊ፡ 181]
2. በስህተት የበላ ወይም የጠጣ ሰው ፆሙ ተበላሽቷል በሚል መቀጠል፡፡ በስህተት መመገብም ሆነ መጠጣት በምንም መልኩ ፆምን አያበላሽም፡፡ ነብዩ ﷺ “አንድ ሰው ረስቶ ከበላና ከጠጣ ፆሙን ይቀጥል፡፡ ያበላውና ያጠጣው አላህ ነው” ብለዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
3. የወር አበባ ከመጣ በኋላ ፆምን መቀጠል፡፡ አንዳንድ ሴቶች ፆም ይዘው ቀኑን ካጋመሱ በኋላ የወር አበባ ሲመጣባቸው ደክሜበታለሁ ብለው ይቀጥላሉ፡፡ ይሄ አጉል ልፋት ነው፡፡ የወር አበባ ላይ ያለች ሴት በኢጅማዕ ፆም አይፈቀድላትም፡፡ ይልቁንም በዚያው ልክ ቀዷ ታወጣለች፡፡
4. የተምር ፍሬዎችን በየመስጂዱና ካልሆነ ቦታ መጣል፣
5. ከእኩለ ቀን በኋላ መፋቂያ መጠቀም እንደማይፈቀድ ማሰብ፡- በርግጥ ይሄ እሳቤ ቀጥተኛ ማስረጃ ባይኖረውም ከአንዳንድ ዑለማዎች የተወሰደ ነው፡፡ ሆኖም ግን ከዚህ በተቃራኒ ከብዙ ዑለማዎች ተዘግቧል፡፡ በዚያ ላይ ነብዩ ﷺ “ከፆመኛ በላጭ ነገሮች ውስጥ አንዱ ሲዋክ ነው” ብለዋል፡፡ ኢብኑ ማጀህ ዘግበውታል፡፡ ሶሐብዩ ዓሚር ኢብኑ ረቢዐ ረዲየላሁ ዐንሁ “ነብዩን ﷺ ፆመኛ ሆነው እጅግ ብዙ ጊዜ ሲዋክ ሲጠቀሙ አይቻለሁ” ብለዋል፡፡ ቲርሚዚ ዘግበውታል፡፡
6. የወር አበባ እና የወሊድ ደም ላይ ያሉ ሴቶች “ፆም አልያዝንም” ብለው ከመልካም ስራ መዘናጋታቸው፡- የተከለከሉት ፆምና ሶላት ነው፡፡ ስለዚህ ዚያራ፣ ሶደቃ፣ ባጠቃላይ ሌሎች ኸይር ስራዎችን በመስራት በረመዳን በተለየ የሚገኘውን ምንዳ ለማግኘት ሊጥሩ ይገባል፡፡
7. አንዳንድ ሴቶች የወር አበባ ስሜት ስለተሰማቸው ብቻ ደም ሳያዩ ፆማቸውን ማፍረሳቸው፡- የወር አበባ በታወቀ ጊዜ የሚመጣ የታወቀ የደም አይነት ነው፡፡ ኢብኑ ጁረይጅ ረሒመሁላህ ዐጣእን “በወር አበባዋ ቀናት ከደሙ ቀደም ብሎ የምታየው ዳለቻ ወይም ውሃ ፈሳሽ የወር አበባ ነውን?” ብየ ጠየቅኳቸው ይላሉ፡፡ እሳቸውም “በጭራሽ! ደሙን እስከምታይ ድረስ ሶላት እንዳትተው፡፡ ከሶላት ሊያግዳት የሚያስብ ሸይጣን እንዳይሆን እፈራለሁ፡፡” [ሙሶነፍ ዐብዲርዛቅ፡ 1160]
8. መስጂድ ውስጥ ረጅም የውስጥ ሱሪ ሳይለብሱ መተኛት፡- ሃፍረተ ገላ ሲጋለጥ ያጋጥማል፡፡ ይሄ በኢዕቲካፍም ጊዜ ሆነ በሌላ ሰዓት መስጂድ ውስጥ ከሚተኙ ሰዎች ዘንድ በብዛት የሚያጋጥም ስህተት ነው፡፡ ስለዚህ ይሄ ችግር እንዳያጋጥምና ሌሎችም እንዳይቸጋገሩ ጥንቃቄ ሊኖረን ይገባል፡፡
9. አንዳንድ የወለዱ ሴቶች ደም ከቆመም በኋላ አርባ ቀን አልሞላንም ብለው አይፆሙም፡፡ ይሄ ስህተት ነው፡፡ ኢማም አትቲርሚዚ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “የነብዩ ﷺ ሶሐቦች፣ ታቢዕዮችና ከነሱም በኋላ ያሉ ምሁራን የወሊድ ደም ላይ ያሉ ሴቶች ለአርባ ቀናት እንደማይሰግዱ ተስማምተዋል፡፡ ከዚህ በፊት የጠራች ካልሆነች በስተቀር፤ በዚህን ጊዜ (ከአርባ በፊት ከጠራች) ታጥባ ትሰግዳለች፡፡” [ጃሚዑ አትቲርሚዚ፡ 1/258]
ከተለያዩ ኪታቦች የተሰበሰበ
(ኢብኑ ሙነወር፣
Forwarded from Deleted Account
ሀዲስ ቁድሲ


አቡ ሁረይራ [رضي الله عنه‌‎ ] እንዳስተላለፉት ነቢዩ [صلى الله عليه وسلم] እንዲህ ብለዋል፡-

“የቁርኣን እናትን (ፋቲሐን) ሳያነብ የሰገደ ሰው፣ ሶላቱ ጎደሎ ነው፡፡” (ቃሉን ሦስት ጊዜ ደጋግመውታል)፡፡ አንድ ሰው ለአቡ ሁረይራ “ከአሰጋጁ በኋላ ብንሆን እንኳ” አላቸው፡፡ እሳቸውም “ለራስህ አንብብ፤ ምክንያቱም ነቢዩ [صلى الله عليه وسلم] እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁና፤ “ኃያሉና የተከበረው አላህ እንዲህ ብሏል፡- ሶላትን በኔና በባሪያዬ መካከል ለሁለት ከፍየዋለሁ፤ እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል፡፡ ባሪያው ‹አልሐምዱ ሊልላሂ ረብቢል ዓለሚን› ሲል አላህ (ሱ.ወ) ‹ባሪያዬ አመሰገነኝ› ይላል፡፡ ‹አር-ረሕማኒ -ረሒም› ሲል ደግሞ አላህ (ሱ.ወ) ‹ባሪያዬ አሞገሠኝ› ይላል፡፡ ‹ማሊኪ የውሚዲ-ዲን› ሲል አላህ ‹ባሪያዬ አላቀኝ› ይላል፡፡ (ወይም ደግሞ) ‹ባሪያዬ ለኔ ኃይል ራሱን አስገዝቷል› ይላል፡፡ ‹ኢይያከ ነዕቡዱ ወኢያከ ነስተዒን› በሚል ጊዜ ‹ይህ በኔና በባሪያዬ መካከል ነው፤ እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል› ይላል፡፡ ‹ኢህዲነስ-ሲራጠ-ል-ሙስተቂም፣ ሲራጠል-ለዚነ አን ዐምተ ዐለይሂም፣ ገይሪ-ል-መግዱቢ ዐለይሂም ወለድ-ዷሊን› በሚል ጊዜ ደግሞ፣ ‹ይህ ለባሪያዬ ነው፣ እናም ባሪያዬ የጠየቀውን ያገኛል› ይላል፡፡

@abdiiiii1
Forwarded from Deleted Account
إِنَّ ٱلْمُسْلِمِينَ وَٱلْمُسْلِمَٰتِ وَٱلْمُؤْمِنِينَ وَٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْقَٰنِتِينَ وَٱلْقَٰنِتَٰتِ وَٱلصَّٰدِقِينَ وَٱلصَّٰدِقَٰتِ وَٱلصَّٰبِرِينَ وَٱلصَّٰبِرَٰتِ وَٱلْخَٰشِعِينَ وَٱلْخَٰشِعَٰتِ وَٱلْمُتَصَدِّقِينَ وَٱلْمُتَصَدِّقَٰتِ وَٱلصَّٰٓئِمِينَ وَٱلصَّٰٓئِمَٰتِ وَٱلْحَٰفِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَٱلْحَٰفِظَٰتِ وَٱلذَّٰكِرِينَ ٱللَّهَ كَثِيرًۭا وَٱلذَّٰكِرَٰتِ أَعَدَّ ٱللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةًۭ وَأَجْرًا عَظِيمًۭا

"ሙስሊሞች ወንዶችና ሙስሊሞች ሴቶች፣ ምእምናንና ምእምናትም፣ ታዛዦች ወንዶችና ታዛዦች ሴቶችም፣ እውነተኞች ወንዶችና እውነተኞች ሴቶችም፣ ታጋሾች ወንዶችና ታጋሾች ሴቶችም፣ አላህን ፈሪዎች ወንዶችና አላህን ፈሪዎች ሴቶችም፣ መጽዋቾች ወንዶችና መጽዋቾች ሴቶችም፣ ጿሚዎች ወንዶችና ጿሚዎች ሴቶችም፣ (ካልተፈቀደ ሥራ) ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶችና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶችና አውሺዎች ሴቶችም፣ አላህ ለእነርሱ ምሕረትንና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል፡፡"

@abdu4321👀🍃
.
🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨የፈቲ ባል የመጨረሻ ክፍል ነገ ብለን ነበር ነገር ገን ብዙ የቻናላችን ተከታታዩች በውስጥ መስመር ዛሬ ይሁን በማለታቸው እኛም ልንታዘዛቸው ወደድን አላህ ያክብርልን 🤲🤲ከስር ይለቀቃል
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
Forwarded from 💐🕍 አብዲ ቲዩብ๑ 💐۞๑๑۩ 💐 🕌abdi Tube ๑ 💐 (abdul jilal አቡዲ ቲዩብ)
ለምን ይጨነቃሉ ? ለምን ? እኮ ለምን ?
👉አይጨነቁ የምንሎት በዚህ ቻናል ሙሉ በሙሉ እምነት ስላለን ነው ይህ ቻናል አላህን እናስታውስ ዘንድ የተቋቋመ ነው ይፍጠኑና ይቀላቀሉ

🙏ሹክረን ለክ @astewul1
አሠላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ
ውድ የ ኢስላም ልጆች ይህ አዲስ ቻናል ነው
እውነተኛው የ ኢባዳ ወር ከኛ ጋር ሁነው ያሳልፉ ስንሎ በሙሉ እምነት ነው ይቀላቀሉን
2024/09/24 21:21:16
Back to Top
HTML Embed Code: