Telegram Web Link
#EthiopianCivilServiceUniversity

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ነባር ተማሪዎች የ2017 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 20 እና 21/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

የተከታታታይ (የማታ እና የቅዳሜና እሑድ) ትምህርት ፕሮግራሞች ነባር ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 22 እና 23/2017 ዓ.ም የሚካሔድ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በሁሉም ፕሮግራሞች የዘገዩ ተማሪዎች ምዝገባ በቅጣት መስከረም 24/2017 ዓ.ም የሚከናወን ሲሆን፤ የሁሉም ትምህርት መርሐግብሮች ትምህርት መስከረም 24/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

@tikvahuniversity
#AAU #UAT #Cutoff_Points

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ስፖንሰርነት እና በግል የቅድመ ምረቃ አመልካቾች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ይፋ አድርጓል።

በዚህም በመንግስት ስፖንሰር ለተደረጉ የቅድመ ምረቃ አመልካቾች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ለተፈጥሮ ሳይንስ 64 እና ለማኅበራዊ ሳይንስ 51 መሆኑ ታውቋል።

በግል ለመማር ያመለከቱ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ለ2017 ዓ.ም የ UAT መቁረጫ ነጥብ ከ54-79 (እንደየትምህርት ክፍሉ) መሆኑ ተገልጿል።

በግል ለመማር ያመለከቱ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ከፍተኛ የመቁረጫ ያስቀመጡ ት/ት ክፍሎች፦
► ህክምና ትምህርት ክፍል - 79
► ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ እና ኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ - 78
► ኮምፒውተር ሳይንስ ት/ት ክፍል - 77
► የጥርስ ህክምና ትምህርት ክፍል - 75
► ህግ ትምህርት ክፍል - 70

(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ይፋ ያደረገው ለመንግስት እና የግል የቅድመ ምረቃ UAT አመልካቾች የመቁረጫ ነጥብ ከላይ ተያይዟል።)

በመንግስት ስፖንሰርነት እና በግል የቅድመ ምረቃ ትምህርታችሁን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመከታተል የመግቢያ ፈተና (UAT) ወስዳችሁ ያለፋችሁ አመልካቾች፣ የምደባ ውጤታችሁን http://admission.aau.edu.et/login ላይ ገብታችሁ Username (email) እና Password በማስገባት መመልከት ትችላላችሁ።

@tikvahuniversity
ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) የ5 ወር የቅዳሜ እና እሑድ ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓሶች ምዝገባ ላይ ነን። 

👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️    0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1:
ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://www.tg-me.com/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ የድኅረ ምረቃ አመልካቾችን ለመቀበል ማስታወቂያ እያወጡ ይገኛሉ።

አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመግቢያ ፈተና (NGAT) ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡

(የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ያወጧቸው የጥሪ ማስታወቂያዎች ከላይ ተያይዘዋል፡፡)

@tikvahuniversity
#ክቡር_ኮሌጅ የአፍሪካ ቢዝነስ ስኩል አባልና ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው።

👉 በኢትዮጵያ ሙሉ ዕውቅና ያለው
👉 ከ18 ዓመት በላይ በትምህርት ኢንዱስትሪው የተሰማራ
👉 ምቹና ዘመናዊ በሆነ ስማርት የመማሪያ ክፍሎችና ግብዓቶች የተደራጀ

► በመጀመሪያ ዲግሪ
► በቴክኒክና ሙያ /TVET/ (level I-IV)
► የ12ኛ ክፍል የአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) በቀን እና በማታ ተማሪዎችን ለመቀበል በምዝገባ ላይ ነን!

Website: https://kibur.net

አድራሻ፦ ጀሞ ሚካኤል ከአፍሪካ ህንፃ አጠገብ
☎️       0113854042 / 0904848586

Telegram: https://www.tg-me.com/kiburcollege
Facebook:  https://www.facebook.com/kiburcollege
በአዲስ አበባ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ለአምስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚዲያ እና ተግባቦት መፅሐፍት ድጋፍ አድርጓል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ እና ወራቤ ዩኒቨርሲቲ የመፅሐፍት ድጋፍ የተደረገላቸው ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው።

ድጋፉ በሀገሪቱ የሚዲያ ተቋማትና ጋዜጠኝነት እንዲጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ኤምባሲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሙዚቃ ጥበባት ትምህርት ፕሮግራም በ2017 ዓ.ም በመደበኛው መርሐግብር የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚጀምር አሳውቋል፡፡

በመሆኑም የ12ኛ ክፍል አጠናቃችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁ፣ የሪሚዲያል ማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እና ከተለያዩ ተቋሞች በስፖንሰር የመማር ፍላጎትና ተሰጥኦ ያላችሁ ተማሪዎች ከመስከረም 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

የማመልከቻ ቦታ 👇
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፔዳ ግቢ፣ የሲኒማና ቴአትር ጥበባት ትምህርት ክፍል

ለተጨማሪ መረጃ፦ 0918424663

@tikvahuniversity
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ነባር የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት መስከረም 22 እና 23/2017 ዓ.ም ሲሆን፤ ምዝገባ መስከረም 27 እና 28/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል።

አዲስ በትምህርት ሚኒስቴር የምትመደቡ እና የሪሚዲያል ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ ይደረግላችኋል ተብሏል።

@tikvahuniversity
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
#Lorcan_Medical_College

የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ጀምሯል❗️

BSc fields of study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing

TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography

የ CPD ማዕከል አገልግሎት!

☎️ 0913398780 / 0911596059

አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ

📍 Addis Ababa, CMC Square, behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital

Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
Empowering educators to utilize culturally relevant EdTech tools is crucial for engaging students and enhancing their learning experiences. Let's make education accessible for everyone. Discover how we can integrate local languages and cultural narratives into educational technology to create learning experiences that resonate with all Ethiopian students.

Tune in to Fana FM 98.1 on Monday, September 30th at 8:10pm for insights.

#EdTechMondays #EdTechMondaysEthiopia #Ethiopia #Africa #Education #EdTech #Tech #AddisAbaba #ICT #CulturallyResponsive #Inclusivelearning #CulturalRespect #EmpowerStudents #Inclusivelearning #Shega #mastercardfoundation
በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ ወደ አርሲ ዩኒቨርሲቲ የምትመደቡ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ መረሐግብር ተማሪዎች፣ ዩኒቨርሲቲው የመግቢያ ቀናት ወደፊት እስከሚያሳውቅ በትዕግስት እንድትጠብቁ ጠይቋል።

@tikvahuniversity
አሶሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ለነበራችሁ እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ለምትመደቡ አዲስ የአቅም ማሻሻያ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው አስካሁን ጥሪ አለማድረጉን ገልጿል።

በቀጣይ ጥሪ አስከሚደረግ በትዕግስት እንድትጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል።

@tikvahuniversity
በ2017 የትምህርት ዘመን አዲስ የዩኒቨርሲቲዎች የቀን የምግብ በጀት ዋጋ ተመን ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር ባለፈው ሐምሌ መግለፁ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ የ2017 ትምህርት ዘመን መጀመርንም ተከትሎ ዩኒቨርሲቲዎች አሁንም ቀድሞ በነበረው የበጀት አሰራር ተማሪዎቻቸውን እየመገቡ ይገኛሉ።

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የሰጡት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሹኔ፣ የተሻሻለው አዲስ የበጀት አሰራር በቅርቡ ይለቀቃል ብለዋል።

"ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች አንድ አይነት የሜኑ በጀት ይሁን ወይስ በየአካባቢው የሚገኘውን ሀብት መሠረት ያደረገ በጀት ይሁን" በሚለው ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይሁን እንጂ የተሻሻለው አዲስ የሜኑ አሰራር በቅርቡ ይለቀቃል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በዚህም የአንድ ተማሪ የቀን ወጪ ከ100 ብር በላይ እንደሚሆን ገልፀዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች በቀን አንድ ተማሪ ቁርስ፣ ምሳ እና እራት ለመመገብ በመንግሥት የሚመድብላቸው 22 ብር በጀት በቂ አለመሆኑን በተደጋጋሚ ያነሳሉ፡፡

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ከተለያዩ በጀቶች በማዛወር በቀን እስከ 80 ብር በመመደብ ተማሪዎቻቸውን እየመገቡ እንደሚገኙ ይገልፃሉ፡፡

የዋጋ ትመናው ጊዜውን ያላገናዘበ በመሆኑ ማስተካከያ ሊደረግበት እንደሚገባ የተለያዩ አካላት ሲጠይቁ ይደመጣል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፣ ጥናቶች "እስከ ነሐሴ 2016 ዓ.ም ድረስ ሥራዎች ተጠናቀው በአዲሱ የትምህርት ዘመን አዲስ የቀን ዋጋ ተመን ይፋ ይደረጋል" ብለው እንደነበር አይዘነጋም፡፡

@tikvahuniversity
2024/09/28 15:24:57
Back to Top
HTML Embed Code: