Telegram Web Link
#BahirDarUniversity

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ተማሪዎች እያስመረቀ ነው።

ተመራቂዎቹ በመደበኛው፣ በክረምት፣ በተከታታይ እና በርቀት መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

አጠቃላይ ተመራቂዎች - 8,524
በፒኤችዲ - 82
በማስተርስ ዲግሪ - 1,119
በመጀመሪያ ዲግሪ - 2,589
በስፔሻሊቲ እና ሰብ-ስፔሻሊቲ - 62
በፒጂዲቲ - 4,334
በኤችዲፒ - 96
በአመራር ሰርተፊኬት - 6
በማሪታይም- 234

@tikvahuniversity
#ነፃ_የፌሎውሺፕ_ዕድል

ከዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ተመርቀዋል? የማኅበረሰብ ለውጥ ለማምጣት ፍላጎት አለዎት?

እንግዲያውስ ለዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ምላሽ የአመራር ፌሎውሺፕ ፕሮግራም ያመልክቱ።

ለሁለት ዓመት የሚቆየው ፌሎውሺፕ ፕሮግራሙ የአደጋ ተጋላጭነት አስተዳደር ክህሎትና ልምድ እንዲያጎለብቱ ያስችልዎታል።

በዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና የሚያገኙ ሲሆን፤ በፕሮጀክቶች ላይ በመስራት ከዘርፉ ሙያተኞች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩ ይደረጋል።

ስለፌሎውሺፕ ፕሮግራሙ መረጃ ለማግኘት 👇
https://drive.google.com/file/d/12fK_rTrR37tfEasG7tPd4Sm--4L2jkeu/view?usp=drive_link

ኦንላይን ለማመልከት 👇
https://docs.google.com/forms/d/1QJflHITYBmP_dxSQRTWhUsGZoHRQashTNqMsIOd2zZI/edit

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
ነሐሴ 5/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
#Infinix_Note40_Pro_Plus

ነሐሴ 4 ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በቃና ስቱዲዮ የተደገሰው ልዩ የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G የሙዚቃ እና የጌም ድግስ የትም ይሁኑ የት ማይቀርበት ነው፡፡ በተለያዩ የጌም ቶርናመንቶች አዲሱን የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G ስልክን ጨምሮ በሽልማቶች የሚንበሸበሹበት፤ እነ ዲጄ ሚላ፣ ዮን ዜማ፣ ፍላሽ ኪዶ፣ ዲጄ ፔርዱ፣ ሳጂ እና አብሌር በመድረኩ የሚነግሱበት ደማቅ ምሽት ተዘጋጅቷል፡፡

#Note40Et #Note40Pro #Note40 #Note40ProPlus #InfinixEt
ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሰቲ 544 ተማሪዎችን አስመረቀ።

ተመራቂዎቹ በድኅረ ምረቃ እና በቅድመ ምረቃ መርሐግብር በተለያዩ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

በዚህም 388 የድኅረ ምረቃ እና አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ያለፉ 156 የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች በድምሩ 544 ተማሪዎች ተመርቀዋል።

በዚህ ዓመት በጥር እና በሰኔ ወር የተሰጡ የመውጫ ፈተናዎች ያለፉ ተፈታኞች ቁጥር ከ60% በላይ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
Photo
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከ8,500 በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል።

በዩኒቨርሲቲው የመውጫ ፈተና ከሰጡ 78 የትምህርት ክፍሎች መካከል 38ቱ ያስፈተኗቸውን በሙሉ ማሳለፋቸውን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ገልፀዋል። 16 የትምህርት ክፍሎች ደግሞ እያንዳንዳቸው ከአንድ ተማሪ በስቀር ሁሉንም ማሳለፋቸውን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ዓለም አቀፋዊነቱን እያጎላ እንደሚገኝ የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፤ ከአፍሪካ ምርጥ 100 ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰዋል። የውጭ ሀገራት ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑንም ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
° " በጀት አጥሮናል ቤታችሁ ቆዩ በመባላችን አላግባብ ጊዜያችን እየተቃጠለብን ነው መፍትሔ እንሻለን " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ተማሪዎች

° " ከተወካዮቻቸው ጋር በቅርቡ እንነጋገራለን " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ት/ክፍል ተጠሪ


" ላለፉት ስምንት ዓመታት ትምህርት ላይ ብንሆንም አሁንም በተለያየ መልኩ ጊዜያችን እየተቃጠለ በመሆኑ የመመረቂያ ጊዜያችን አሳሳቢ ሆኗል " ሲሉ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

" ዩኒቨርሲቲው በበጀት እጥረት ምክንያት መግቢያችን ለሁለተኛ ጊዜ መራዘሙ ትክክል አይደለም " ብለዋል ተማሪዎቹ።

በኮቪድ-19 ለአስር ወራት እንዲሁም በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት የትምህርት ጊዚያቸው መቃጠሉንና የመመረቂያ ጊዚያቸው መራዘሙን ተማሪዎቹ ገልፀዋል።

በዚህ ዓመት ለ12ኛ ክፍል ፈተና እንዲወጡ ተደርገው ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም እንደተጠሩና በኋላም ወደ ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም እንደተገፋ፤ አሁን ደግሞ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ይገልፃሉ።

አሁን የምግብ በጀት በቂ ባለመሆኑ ኢንተርን ዶክተሮች ወደ የነን ካፌ ፎርም በመሙላት ከዶርም እንዲወጡና እየተመላለሱ እንዲጨርሱ እንዲሁም ወደቤተሰብ የሄዱ ተማሪዎች በዛው እንዲቆዩ  ዩኒቨርሲቲው ማስታወቂያ ማውጣቱ አሳሳቢ እንደሆነ አንስተዋል።

በመሆኑም የሚመለከተው አካል መፍትሔ ይስጠን ሲሉ ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ የጠየቃቸው በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ትምህርት ክፍል ተጠሪ ዶ/ር ጌታሰው ጥያቄውን በተመለከተ ከተማሪዎች ጋር በተለይም ከተማሪ ተወካዮች ጋር እንደሚነጋገሩ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
Tikvah-University
° " በጀት አጥሮናል ቤታችሁ ቆዩ በመባላችን አላግባብ ጊዜያችን እየተቃጠለብን ነው መፍትሔ እንሻለን " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ተማሪዎች ° " ከተወካዮቻቸው ጋር በቅርቡ እንነጋገራለን " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ት/ክፍል ተጠሪ " ላለፉት ስምንት ዓመታት ትምህርት ላይ ብንሆንም አሁንም በተለያየ መልኩ ጊዜያችን እየተቃጠለ በመሆኑ የመመረቂያ ጊዜያችን አሳሳቢ ሆኗል " ሲሉ የሀዋሳ…
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምላሽ !

" ማስታወቂያዉ ከኮሌጁ እውቅና ውጭ የተለጠፈ በመሆኑ በለጠፈዉ አካል ላይ አጣርተን እርምጃ የምንወስድ ይሆናል " - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በኑሮ ዉድነቱ ምክኒያት ተማሪዎችን መመገብ ባለመቻሉ ተማሪዎች የተመደበላቸዉን 22 ብር ወስደዉ እንዲጠቀሙ የሚገልጽ ማስታወቂያ ማዉጣቱን እንዲሁም ለ12ኛ ክፍል ፈተና ሲባል ግቢዉን ለቀዉ የወጡ ተማሪዎች ጥሪ እንዳልተደረገላቸዉ መናገራቸዉን ገልጸን የተማሪዎችን ቅሬታ አቅበን ነበር።

ይህን ተከትሎ " የቀረበዉ መረጃ ትክክል አይደለም " ያሉን የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ተባባሪ ፕሮፌሰር አለሙ ጣሚሶ ኢንተርን ሀኪሞች ከግቢ እንደማይወጡና ዶርማቸዉን እንደማይለቁ ይልቁንም ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርስቲው የምግብ አገልግሎት በመቋረጡ በጀታቸዉን እንዲጠቀሙ ስለመገለጹ ነግረዉናል።

ይህ የሆነበት ምክኒያት አሁን ላይ ለሶስት አመት ዉል የገቡ ነጋዴዎች በእቃ መወደድ ምክኒያት ምንም አይነት የምግብ ግብአት ሊያቀርቡልን ባለመቻላቸዉና ይህን ችግር ተወያይተን መፍትሄ እስክንሰጠዉ ነው ሲሉ ይገልፃሉ።

ሌሎች ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት ከተጠናቀቀ በቅርቡ ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሳሉ ትክክለኛ ቀኑንም ለተማሪዎች በይፋ የሚነገራቸው ይሆናል የሚሉት ሀላፊዉ ተማሪዎችን አሁን ላይ መቀበል ያልቻሉት ከምግብ አቅርቦትና አንዳንድ ማስተካከያ የሚፈልጉ ጉዳዮች ስላሉ ነዉ ብለዋል።

ከዚህ ዉጭ በየጊዜዉ ለ12ኛ ክፍል ፈተና ሲባል መዉጣታቸዉም ሆነ አሁን ላይ በቶሎ አለመግባታቸዉ የሚወስድባቸዉን ጊዜ ለማካካስም ዩኒቨርሲቲዉ መፍትሄዎችን ማስቀመጡን ገልጸዉልናል።

ይሁንና ተማሪዉን የሚያደናግር ማስታወቂያ ያወጣዉ አካል ከኛ እዉቅና ዉጭ በመሆኑ ማንነቱን አጣርተን እርምጃ የምንወስድ ይሆናል ብለዉናል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ሳይንስ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝደንቱ ተማሪ ደረጀ መንገሻ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፤ ምንም እንኳን ኢንተርን ዶክተሮች ከግቢ ባለመዉጣታቸዉ እስካሁን መጉላላት እንዳልደረሰባቸዉ ቢገልጽም ማስታወቂያዉ ያለነሱ እዉቅና መለጠፉም ሆነ ተማሪዉን ሳይፈልግ ወደነን ካፌ መቀየር አግባብ ስላልሆነ ለዩኒቨርሲቲዉ አመራሮች ዉሳኔዉ ልክ አለመሆኑን የሚገልጽ ደብዳቤ አስገብተን ምላሽ እየጠበቅን ነዉ ብሏል።

ተማሪዎች ሀምሌ 25 ያልገቡበት ምክኒያት ዩኒቨርሲቲዉ ከበጀት ማስተካከያና ካምፓስ ዉስጥ ከሚያስተካክሏቸዉ አንዳንድ ነገሮች ጋር በተያያዘ ምክኒያት መሆኑንና በዚህ ምክኒያት በቀጣይ ተማሪዎች ላይ የሚከሰተዉን ጫና በተመለከተ ዩኒቨርሲቲዉ እንዲያስብበት ተነጋግረናል በማለት ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
የ2016 ዓ.ም የተማሪዎች የሒሳብ ትምህርት ውድድር የማጠቃለያ መርሐግብር ተካሒዷል።

ውድድሩ ከ3ኛ እስከ 12ኛ ክፍል በሚማሩ ተማሪዎች መካከል ''ማይ ሶሮባን'' ኢትዮጵያ በተሰኘ ድርጅት አዘጋጅነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲካሔድ ቆይቷል፡፡

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመጡ መምህራን ዳኝነት በተካሔደው ውድድር፤ ከ50 ከተሞች የተውጣጡ ተማሪዎች ተሳታፊ መሆናቸው ተገልጿል።

የሒሳብ ትምህርት ከባድ ነው በሚል የሚታሰበውን የተሳሳተ አመለካከት በመቅረፍ ተማሪዎችን በትምህርት አይነቱ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ቀደም ሲል በየአከባቢያቸው በተደረገ ውድድር አሸናፊ ሆነው ለማጠቃለያው ውድድር የደረሱ ተማሪዎች የዋንጫ እና የሜዳልያ ሽልማት በክብር እንግዶች የተበረከተ ሲሆን፤ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድሩ በየክፍል ደረጃው እስከ መጪው ረቡዕ ተካሒዶ ለአሸናፊዎች ዕውቅና እንደሚሰጥ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
ሰመራ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያውን የቀድሞ ተማሪዎች ጉባዔ (Alumni Conference) ሊያካሒድ ነው፡፡

ለዚህም ዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች ኅብረት ለማቋቋም እየተንቀሳቀስ እንደሚገኝና ምዝገባ እያደረገ መሆኑንም ገልጿል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያውን የቀድሞ ተማሪዎች ጉባኤ በ2017 ዓ.ም ለማካሄድ የቀድሞ ተማሪዎቹን በማሰባሰብ ላይ ነው።

ለምዝገባ የተዘጋጀውን ቅፅ 👉 https://forms.gle/qEjb6XLEEpHGsasq6 በመሙላት የቀድሞ ተማሪዎች ኅብረቱን ይቀላቀሉ፡፡

@tikvahuniversity
ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ 'የኮዲንግ' ሰልጣኞች በአዲስ አበባ ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ነው፡፡

'Addis Coder' የተሰኘው መርሐግብር ለአራት ሳምንታት በነጻ የሚሰጥ የክረምት ስልጠና መርሐግብር ሲሆን፤ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች የአልጎሪዝም እና ፕሮግራሚንግ ስልጠናዎች ይሰጣቸዋል፡፡

ስለጠናው በአንጋፋ የዩናይትድ ስቴትስ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚያስተምሩ መምህራን ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የሚሰጥ ነው፡፡

@tikvahuniversity
2024/10/02 18:18:23
Back to Top
HTML Embed Code: