Telegram Web Link
#WoldiaUniversity

ወልድያ ዩኒቨርሲቲ የነባር የክረምት መርሐግብር የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች እንዲሁም የ PGDT ሰልጣኞች ምዝገባ ሐምሌ 15 እና 16/2016 ዓ.ም ያከናውናል።

ትምህርት ሐምሌ 23/2016 ዓ.ም እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡

አዲስ የ PGDT ሰልጣኞች ምዝገባ እስከ ሐምሌ 14/2016 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል።

@tikvahuniversity
አምቦ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ነባር የክረምት መርሐግብር የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ተማሪዎች እንዲሁም የ PGDT ፕሮግራም ሰልጣኞች ምዝገባ ሐምሌ 23/2016 ዓ.ም እንደሚከናወን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
➧ የተፈጥሮ እና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች በዋናው ካምፓስ
➧ የሌሎች ትምህርት ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ሀጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ

ትምህርት ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም በተመዘገባችሁበት ካምፓስ የሚጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡

በመንግሥት ስፖንሰርነት የምትማሩ የመገጣጠሚያ ደብዳቤ መያዝ ይጠበቅባችኋል።

@tikvahuniversity
#NATIONAL_EXAM

ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል፡፡

ሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 09/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና በኦንላይን በመላ አገሪቱ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡

በዛሬው የሦስተኛ ቀን ፈተና፤ በጠዋቱ መርሐግብር የኬሚስትሪ ትምህርት ፈተና የተሰጠ ሲሆን፤ በከሰዓቱ መርሐግብር የባዮሎጂ ትምህርት ፈተና የሚሰጥ ይሆናል፡፡

በትግራይ ክልል ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሐምሌ 9/2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ ሲሆን፤ ነገ ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይታወቃል፡፡

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናዋን በመውሰድ ላይ የነበረችው ተማሪ የወንድ ልጅ እናት ሆናለች፡፡

በቀሉ ተስፋ ከቄለም ወለጋ አካባቢ የ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተናዋን ለመውሰድ ነበር በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የተገኘችው፡፡

ፈተናዋን እየወሰደች የልጅ እናትም ሆናለች፡፡ ልጇም እሷም በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ተማሪ በቀሉ ፈተናዋን እየወሰደች እንደምትገኝ ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

@tikvahuniversity
በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናዋን እየወሰደች የምትገኘው ተማሪ ኒሞ ኢብራሂም የልጅ እናት ሆናለች፡፡ በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ልጇን ወልዳለች፡፡

ብዙ የለፋችበትና የተዘጋጀችበት የ12ኛ ክፍል ፈተና እንዲያመልጣት ያልፈለገችው ተማሪ ኒሞ፤ ከሆስፒታል ሆና የመጨረሻ ቀን ፈተናዋን በመውሰድ ላይ ትገኛለች፡፡

@tikvahuniversity
ለቻርጀር መሯሯጥ ድሮ ቀረ! ገና ቀኑ ሳይጋመስ የሚያልቅ ባትሪ አላማረራችሁም? እንግዲያውስ ቅመም Itel Pro ለእናንተ ነው! ባለ የ4000mAh የባትሪ አቅም ያለው ቅመም Itel በአንድ ጊዜ ቻርጅ ብቻ ለሁለት ቀናት እንደልባችሁ ስልካችሁን መጠቀም ያስችላችኋል! ቅመም Itel Pro በሄዳችሁበት ሁሉ አብሯችሁ ነው!

#SafaicomEthiopia
#MpesaSafaricom
#1Wedefit
#FurtherAheadTogether
#WallagaUniversity

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ የ2016 የክረምት መርሐግብር ነባር የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ እንዲሁም የ PGDT ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 15-16/2016 ዓ.ም እንደሚካሔድ ገልጿል።

ምዝገባ የሚካሔደው በነበራችሁበት ካምፓስ ሲሆን፤ የ PGDT ተማሪዎች ምዝገባ በዋናው ካምፓስ መሆኑ ተገልጿል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
#NATIONAL_EXAM

ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከትግራይ ክልል ውጪ ዛሬ ተጠናቋል።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከማክሰኞ ሐምሌ 9/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና በኦንላይን ሰሰጥ ቆይቷል።

ዛሬ ከሰዓት ከተሰጠው የባዮሎጂ ትምህርት ፈተና በኋላ፣ ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከትግራይ ክልል ውጪ መጠናቀቁ ታውቋል። በዚህም ተፈታኞች ወደየቤተሰቦቻቸው መመለስ ጀምረዋል፡፡

በትግራይ ክልል ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ነገ ሐምሌ 12/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

@tikvahuniversity
2024/10/05 03:16:00
Back to Top
HTML Embed Code: