Telegram Web Link
ተፈታኝ ተማሪዎች ወደቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ ነው።

ላለፉት ሦስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የመጀመሪያው ዙር አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዛሬ ከሰዓት በተሰጠው የኢኮኖሚክስ ፈተና ፍፃሜውን አጊኝቷል።

የመጀመሪያው ዙር ፈተና ከረቡዕ ሐምሌ 3/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በወረቀት እና በኦንላይን በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና በተመረጡ የፈተና ማዕከላት ተሰጥቷል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
Photo
በአዲስ አበባ ከተማ ላለፉት ሦስት ቀናት የተሰጠው የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ የማኅበራዊ ሳይንስ ፈተና ተጠናቋል፡፡

ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ በመዲናዋ በተለዩ 10 የፈተና ማዕከላት ሲሰጥ ቆይቷል።

የፈተናውን መጠናቀቅ ተከትሎ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደቤተሰቦቻቸው ተመልሰዋል።

ሁለተኛው ዙር ፈተና ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች እንደሚሰጥ ይታወቃል።

@tikvahuniversity
የ59 ዓመቱ አባት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናቸውን በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ወስደዋል።

አቶ አሊ ሁሴን ሀመዱ በአፋር ክልል ዞን አምስት በሚገኘው 'ደዌ ወረዳ' መሀመድ ቦዳያ ትምህርት ቤት ነው የተማሩት።

የ59 ዓመት ብርቱ አባት፤ ዕድሜያቸው እና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸው ሳይበግራቸው ትምህርታቸውን አጠናቀው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናቸውን ወስደዋል።

የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪው አቶ አሊ፤ ለሌሎችም አርአያ በመሆን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናቸውን በ59 ዓመታቸው ተፈትነዋል።

@tikvahuniversity
ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ በርካታ ጎልማሳ እና የዕድሜ ባለፀጎች ይገኙበታል።

የ78 ዓመቱ አዛውንት ኢብራሂም ጎዳና፣ በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ፈተናቸውን የልጅ ልጆቻቸው ከሚሆኑ ተማሪዎች ጋር ወስደዋል።

ትምህርታቸውን ለመማር እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ለመውሰድ ዕድሜ እንዳልገደባቸው አሳይተዋል።

@tikvahuniversity
2024/10/06 07:19:30
Back to Top
HTML Embed Code: