Telegram Web Link
ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታቸውን በተቋሙ ከተከታተሉ ተማሪዎች 𝟗𝟔.𝟗 በመቶ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን ገልጿል።

1,507 ተማሪዎች የሪሚዲያል ትምህርታቸውን በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተከታትለው 1,461 ተማሪዎች (𝟗𝟔.𝟗 በመቶ) የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው ጠቁሟል።

@tikvahuniversity
ቦረና ዩኒቨርሲቲ ለሪሚዲያል እና አዲስ ለሚመደቡ ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ አራዝሟል።

በ2016 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ቦረና ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 23 እና 24/2017 ዓ.ም ይከናወናል በማለት ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶች ምዝገባው ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
2024/09/30 15:26:01
Back to Top
HTML Embed Code: