Telegram Web Link
#STEMpower

በስድስት የስቴም ፓወር ስልጠና ማዕከላት ትምህርታቸውን ተከታትለው በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ማለፋቸውን STEMpower ገልጿል።

ቓላሚኖ ስቴም ማዕከል፣ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ስቴም ማዕከል፣ ወላይታ ሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት እና ኦልማ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ካሳለፉ የስቴም ማዕከላት መካከል ይጠቀሳሉ።

STEMpower በኢትዮጵያ 61 የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሒሳብ የስልጠና ማዕከላት አሉት።

@tikvahuniversity
የናይጄርያ መንግሥት በሐሰተኛ የትምህርት ሰነድ ላይ ሀገር አቀፍ ዘመቻ ጀምሯል።

የሀገሪቱ ሲቪል ሰርቪስ ፌደሬሽን የሀሰት ሰርተፊኬት የያዘ የትኛውንም ግለሰብ ከሥራ እንዲያባርር ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኑቡ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

ቀጣሪ ተቋማት ከሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ ሊጠበቁና የብቃት ማረጋገጫዎች ትክክለኛነትን ሊያረጋግጡ እንደሚገባም ገልፀዋል።

ለሀገሪቱ የአካዳሚ ትምህርት መረጃዎች የሚሰጡ የመንግሥት ድርጅቶች እና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሆነ የአሜሪካ ድምፅ ዘገባ ያሳያል።

የናይጀሪያ ትምህርት ሚኒስትር ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንት ቲኑቡ የሀገሪቱ የሲቪል ሰርቪስ ፌደሬሽን ኃላፊ የሀሰት ሰርተፊኬት የያዘ ማንኛውንም ገልሰብ እንዲያባርሩ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

የናይጄርያ መንግሥት ከባለፈው ጥር ጀምሮ በ107 የግል ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ምርመራ በማካሄድ ላይ ይገኛል። ይህም የሀሰት ዲግሪዎችን መስፋፋት ለመከላከል ተጨማሪ ጥረት ነው ተብሏል። #VOA

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ #በሜዲካል_ራዲዮሎጅ_ቴክኖሎጅ ፖስት ቤሲክ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት የሚከታተሉ 20 ተማሪዎችን በ2017 ዓ.ም ተቀብሎ ለማስተማር መዘጋጀቱን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ጊዜ፦
ከመስከረም 10-20/2017 ዓ.ም

የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ወደፊት እንደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

አመልካቾች ሁለት ዓመትና ከዚያ በላይ በመንግሥት እና/ወይም በግል የህክምና ተቋማት ያገለገሉ እንዲሁም በራሳቸው ስፖንሰርነት ወይም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት የስፖንሰርነት ደብዳቤ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

ኦንላይን ለመመዝገብ 👇
http://www.dmu.edu.et/Online-Application-form/

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌንየም ህክምና ኮሌጅ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የህክምና ትምህርት ለመማር ለምትፈልጉና የተቀመጡ መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾችን መቀበል እንደሚፈልግ ኮሌጁ አሳውቋል።

መስፈርቶች፤

➧ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል አማካይ የትራንስክሪፕት ውጤት 80% እና ከዚያ በላይ የሆነ
➧ በ2016 ዓ.ም በመደበኛ ፕሮግራም የ12ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀ/ያጠናቀቀች
➧ ከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከ600 ተፈትነው ለወንድ 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያለው፤ ለሴት 475 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላት
➧ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከ700 ተፈትነው ለወንድ 580 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያለው፤ ለሴት 555 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላት
➧ ለአፋር ክልል፣ ለቦረና ዞን (ኦሮሚያ ክልል)፣ ለደቡብ ኦሞ ዞን (ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል)፣ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ ለጋምቤላ ክልል፣ ለሱማሌ ክልል፣ ለዋግህምራ ዞን (አማራ ክልል) እና ለምእራብ ኦሞ ዞን (ደቡብ ም/ኢ/ክልል) ለወንድ 450 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያለው፤ ለሴት 425  እና ከዚያ በላይ ውጤት ያላት

► ማመልከት የሚቻለው በኦንላይን ብቻ ነው።

► የማመልከቻ ጊዜ፦
ከመስከረም 11-18/2017 ዓ.ም

ለተጨማሪ መረጃ፦
- www.sphmmc.edu.et/
- ስልክ ቁ. - 0118965125

@tikvahuniversity
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ይፋ መሆኑ ይታወቃል።

የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ውጤት ስንት ነው የሚሉ ጥያቄዎች ለቲክቫህ ደረሰዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የሚሰላ (70%) እና በተማሩበት ተቋም የሚሰላ (30%) በድምሩ 50% እና ከዚያ በላይ የማለፊያ ነጥብ መሆኑን ከሚኒስቴሩ ሰምተናል።

በተማሩበት ተቋም 30% ውጤት ያልተሞላላቸው ተማሪዎችን ውጤት ለመሙላት ባለሙያዎች እየሠሩ መሆኑንና በቅርቡ እንደሚለቀቅላቸው ሚኒስቴሩ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ገልጿል።

@tikvahuniversity
በM-PESA ነው መቀበል!
የሱፉ ይላክልን እንጂ ፤ የከረባቱ በእኛ ነው!
ከአሜሪካ፣ ከካናዳ፣ ከእንግሊዝ፣ ከአውሮፓ፣ ከአውስትራሊያ፣ ከሊቢያ፣ ከደቡብ አፍሪካ፣ ከኬንያ፣ ከናይጄሪያ፣ ከእስራኤል ወይም ከቻይና ገንዘብ ስንቀበል በመላ በM-PESA ነው መቀበል! ለምን? 5% ካሽባክ እና ጉርሻ እናገኛለን!

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom  #FurtherAheadTogether
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ ዓመት ልዩ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ! ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮዎት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማኅበራዊ ገፅዎት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮች እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገፆችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማኅበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስትዎት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡

Tag ሲያደርጉን
ለ Facebook @TecnoEt https://www.facebook.com/share/KpViroSyJgPe1bML/?mibextid=qi2Omg
ለ Instagram @TecnoMobileEthiopia https://www.instagram.com/tecnomobileethiopia?igsh=cjdwdjQzbGlvaDV1
ለ TikTok @TecnoEt
https://www.tiktok.com/@tecnoet?_t=8pQuOpSYlGP&_r=1 ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
በተጨማሪም #TecnoEt2017 ኪወርድን መጠቀም እንዳይረሱ!
5_UAT_23_09_2024_Morning_Schedule.xlsx
77.4 KB
#AAU #UAT

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (UAT) መስከረም 13/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

ሰኞ መስከረም 13/2017 ዓ.ም ጠዋት ለሚሰጠው ፈተና የተፈታኞች ኮድና ስም ዝርዝር እንዲሁም የመፈተኛ ካምፓስና ክፍል ከላይ ከተያያዘው ኤክሴል ይመልከቱ፡፡

@tikvahuniversity
#AAU #UAT #ተጨማሪ

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የቅድመ ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ምዝገባ ያደረጋችሁና የዩኒቨርሲቲውን መግቢያ ፈተና (UAT) ለመውሰድ
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቢሾፍቱ ካምፓስ
- አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ
- ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲእና እና
- ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የመፈተኛ ቦታ አድርጋችሁ የመረጣችሁ ፈተናው መስከረም 11 እና 12/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።

ከአዲስ አበባ ውጪ የመፈተኛ ቦታ የመረጣችሁ
- አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
- ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ እና
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ ፈተናችሁ ሰኞ መስከረም 13/2017 ዓ.ም ይሆናል።

የመፈተኛ Password ትኬት እንዴት ያገኛሉ?

የመፈተኛ ቀን፣ ሰዓት፣ የመፈተኛ Username፣ የመፈተኛ Passward ትኬት ለማግኘት፤ ለማመልከት የተጠቀማችሁበትን የኢሜል አድራሻ እና Passward https://portal.aau.edu.et ላይ በመግባት ከዚያ Apply for admission በመምረጥ Login የሚለውን በመክፈት ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

Note:
ስምዎ አሁን ባለው ሊስት ውስጥ ካልተካተተ፣ በሚቀጥሉት የፈተና ሊስት ውስጥ እንደሚካተቱ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
#AdigratUniversity

ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ የቅድመ ምረቃ እና የድኅረ ምረቃ ነባር መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት መስከረም 25 እና 26/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

በ2016 ዓ.ም በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታችሁን ተከታትላችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጣቹ ተማሪዎች፣ በ2017 ዓ.ም አዲስ ከሚመደቡ ተማሪዎች ጋር ጥሪ እንደሚደረግላችሁ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ የሁሉም የአንደኛ ዓመት እንዲሁም የመጨረሻ ዓመት የቅድመ ምረቃ አና የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት መስከረም 22 እና 23/2017 ዓ.ም ሲሆን፤ ምዝገባ መስከረም 27 እና 28/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል።

@tikvahuniversity
#AASTU #ASTU

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ለመማር በዩኒቨርሲቲዎቹ የተዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገባችሁ ተማሪዎች ፈተናው መስከረም 14/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ፈተናው ማክሰኞ መስከረም 14/2017 ዓ.ም በሁለት ክፍለ ጊዜ ማለትም ጠዋት ከ 2፡30-5፡30 እና ከሰዓት ከ7፡30 -10፡30 ይሰጣል።

ከካልኩሌተር እና ለማሰቢያ ከሚሆን ወረቀት ውጭ ማንኛውንም ዓይነት ሞባይል ስልክ ወይም ስማርት ፎን ይዞ ወደ መፈተኛ ማዕከላት አይቻልም ተብሏል።

@tikvahuniversity
#InjibaraUniversity

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ እና ነባር የቅድመ ምረቃ ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።

በዚህም የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች መስከረም 29 እና 30/2017 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ይገባሉ።

የ3ኛ ዓመት፣ የ2ኛ ዓመት፣ የ1ኛ ዓመት ነባር ተማሪዎች እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር አዲስ የተመደባችሁ እና በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥቅምት 14 እና 15/2017 ዓ.ም መሆኑ ተገልጿል።

(የዩኒቨርሲቲው መልዕክት ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ ዓመት ልዩ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ! ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮዎት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማኅበራዊ ገፅዎት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮች እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገፆችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማኅበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስትዎት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡

Tag ሲያደርጉን
ለ Facebook @TecnoEt https://www.facebook.com/share/KpViroSyJgPe1bML/?mibextid=qi2Omg
ለ Instagram @TecnoMobileEthiopia https://www.instagram.com/tecnomobileethiopia?igsh=cjdwdjQzbGlvaDV1
ለ TikTok @TecnoEt
https://www.tiktok.com/@tecnoet?_t=8pQuOpSYlGP&_r=1 ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
በተጨማሪም #TecnoEt2017 ኪወርድን መጠቀም እንዳይረሱ!
#HawassaUniversity

የኖርዌይ ሳውዝ-ኢስተርን ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ አምስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የሚተገብረውን የ NURTURE Project በተመለከት ውይይት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አካሒዷል።

የኖርዌይ ሳውዝ ኢስተርን ዩኒቨርሲቲ ከአምስት የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመማር ማስተማር፣ ዲጅታላይዜሽን-ሽግግር፣ ትምህርት መሳሪያዎች ድጋፍ፣ እኩልነትና የሴቶች ተሳትፎ እንዲሁም መሰል የአቅም ግንባታዎች ላይ በትብብር በመስራት ላይ ይገኛል።

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የ Nurture Project እየተገበሩ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው።

በኢትዮጵያ መሠጠት የተጀመረው የድኅረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT)፣ በነርቸር ፕሮጀክት አማካኝነት በስታፍ ኤክስቼንጅ መምህራንና ሠልጣኞችን ለማስተማር ትልቅ ፈተና መሆኑ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል።

እ.አ.አ. በ2023 አንድም የማስተርስ ተማሪ ፈተናውን አልፎ ፕሮጀክቱን ሊቀላቀል እንዳልቻለ ከሳውዝ ኢስተርን ዩኒቨርሲቲ የመጡት የነርቸር ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ፕ/ር ሸጋው አናጋው ገልፀዋል።

በርካታ የፒ.ኤች.ዲ. እና የማስተርስ ተማሪዎችን ለፕሮጀክቱ ለመቀበል ፍላጎት ቢኖርም፣ የGAT ፈተናን የሚያልፉ ስታፍ ተማሪዎች ማግኘት መቸገራቸውን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ፤ ዩኒቨርሲቲዎች የስታፍ ተማሪ አቅርቦታቸው ሊጠናከር ይገባል ብለዋል።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት በተካሔደው መድረክ፣ ፕሮጀክቱ የገጠሙት ችግሮች ላይ ውይይት ተደርጎ የመፍትሔ ሀሳቦች ቀርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahuniversity
2024/10/04 09:21:11
Back to Top
HTML Embed Code: