Telegram Web Link
Tikvah-University
#ተጨማሪ ከጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና (Licensure Exam) ጋር የተያያዙ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ መድረሳቸውን ተከትሎ ተጨማሪ ማብራሪያ ጤና ሚኒስቴርን ጠይቀናል፡፡ የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በዚህ ወር በድጋሜ የሚሰጥ ሲሆን፤ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ የምዝገባ ጥሪ ዛሬ ወይም ነገ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡ ሀገረ አቀፍ የመውጫ ፈተና #ያለፉ እና ዲግሪ #ያላቸው ሁሉም…
ጥያቄያችን አልተመለሰም ያሉት የፋርማሲ ተማሪዎች ጥያቄያችው ምንድነው ?

ተማሪዎቹ በቅድሚያ ያነሱት የተፈተኑት ፈተና ከብሉፕሪንይ ጋር የተገናኘ እንዳልሆነ ነው።

የተመዘገበው ውጤትም በዚህ ምክንያት እንደሆነ ጠቁመዋል።

" ፈተናችን እንደገና ይታይ መብታችን ይከበር " ያሉት ተማሪዎቹ " ኮምፒውተር አይሳሳትም አይበሉን የሰራነውን እናውቃለን " ብለዋል።

ሌላው ተማሪዎቹ ያነሱት ጥያቄ የተባው ቃል አልተከበረም የሚል ነው።

" ጥዋት እና ከሰዓት ሁለት ፈተና ነበር መውሰድ የነበረብን ግን አንዱን ፈተና ሌላ ቀን ትፈተናላችሁ ብለውን በዛው ቀርቷል " ያሉት ተማሪዎቹ " ውጤቱ የተገለጸው በጥዋቱ ብቻ ነው " ብለዋል።

" ትምህርት ሚኒስቴር ቃሉን አክብሮ እንደሌሎች ዲፓርትመንት የከሰአቱም ይፈትነንና አማያከዩ ይያዝልን " ሲሉ ጠይቀዋል።

ውጤታችን ባልተስተካከለበት " በምን መስፈርት coc አትወስዱም አሉን ? " ያሉት ተማሪዎቹ " ሌላም ጊዜ እንደተያዘው የመውጫ ፈተናው የከሰዓቱንም ተፈትነን አማካዩ ይይዛልን " ብለዋል።

ተማሪዎቹ በሌሎች ጥዋትም ከሰዓትም ፈተና በወሰዱ የጤና ዲፓርትመንት አማካይ መያዙን ጠቁመው " ስለዚህ የኛንም እንደዛ ይያዙልን " ሲሉ ጥይቀዋል።

በወቅቱ የፋርማሲ ፈተና ወጥቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመሰጣቱ መሰረዙን በኃላም የጥዋቱን ብቻ ተፈትነው ሌላ ጊዜ የከሰዓቱን ትፈተናላችሁ ተብለው መቅረቱን አመልክተዋል።

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት መማር ለምትፈልጉ የተዘጋጀ መረጃ፦

ኮሌጁ በሦስት ትምህርት ቤቶች ማለትም በሕክምና ትምህርት ቤት፣ በኅብረተሰብ ጤና ትምህርት ቤት እና በነርሲንግ ትምህርት ቤት ስር በሚገኙ በርካታ የትምህርት ክፍሎች አመልካቾችን በመደበኛ እና በእረፍት ቀናት መርሐግብር ለማስተርስ ዲግሪ ፕሮግራም ይቀበላል።

አመልካቾች ብሔራዊ የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (GAT) ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ማግኘት ይጠበቅባችኋል። እንዲሁም የፅሑፍ እና የቃል ፈተና በምታመለክቱበት የትምህርት ክፍል ይሰጣል።

የመመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው ነሐሴ 12/2016 ዓ.ም

ለማመልከት ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦
https://portal.sphmmc.edu.et/Web/Announcement

ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ፣ የሚፈልጉትን የትምህርት ፕሮግራም በመምረጥ Apply የሚለውን በመጫን አስፈላጊ መረጃ በማስገባት ያመልክቱ። የማመልከቻ 400 ብር በCBE በመክፈል ደረሰኙን ያያይዙ። ከዛም የትምህርት ማስረጃዎችን ያያይዙ።

@tikvahuniversity
#ተራዝሟል

ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም መራዘሙን አሳውቋል።

በተራዘመው ጊዜ https://NGAT.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ይመዝገቡ።

@tikvahuniversity
ጤና ሚኒስቴር በዚህ ወር ለሚሰጠው የብቃት ምዘና ፈተና ምዝገባ ተጀምሯል፡፡

በተለያዩ የጤና ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ ቴምፓራሪ ዲግሪ የተሰጣችሁና የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ የጤና ባለሙያዎች የምዘና ፈተናውን መውሰድ ትችላላችሁ ተብሏል፡፡

የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚወስዱ አመልካቾች ምዝገባ ከነሐሴ 06-15/2016 ዓ.ም እንደሚከናወን ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡

የመንግሥት እንዲሁም የግል ተቋማት ተመዛኞች http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ብቻ ምዝገባ እንድታደርጉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡

ምዝገባ ስታደርጉ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር የያዘ ስሊፕ print አድርጋችሁ በመያዝ ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ ተብሏል፡፡

ማሳሰቢያ፦

በሰኔ 2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተሰጠውን የፋርማሲ ሙያ የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፋችሁ ተመዛኞች፣ በጤና ሚኒስቴር በኩል የሚሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና መውሰድ የሚጠበቅባችሁ በመሆኑ ከላይ በተጠቀሰው ዌብሳይት ላይ በመግባት ምዝገባ አድርጉ፡፡

ሰኔ 19/2016 ዓ.ም በተሰጠው የመውጫ ፈተና አልፋችሁ ዲግሪ የያዛችሁ የአንስቴዥያ ተመዛኞች፣ ይህ የምዝገባ ጊዜ እንደተጠናቀቀ የተግባር ምዘና (OSCE) ምዝገባ የሚጀመር በመሆኑ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡

@tikvahuniversity
#ተጨማሪ

ጤና ሚኒስቴር በዚህ ወር የብቃት ምዘና ፈተና የሚሰጥባቸው 16 ሙያዎች፦

- Medicine
- Nursing
- Public Health
- Anesthesia
- Pharmacy
- Midwifery
- Dental Medicine
- Medical Laboratory Science
- Medical Radiology Technology
- Environmental Health
- Psychiatric Nursing
- Pediatric & Child Health Nursing
- Emergency & Critical Care Nursing
- Surgical Nursing
- Physiotherapy
- Human Nutrition

Note:

እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የተለያዩ የአጭር ጊዜ ስልጠናዎች አዘጋጅቷል፡፡

ስልጠናዎቹ በአራት ፈረቃዎች ማለትም ከ3:00- 5:00 ፣ ከ7፡00- 9፡00 ፣ ከ9:00-12:00 እንዲሁም ማታ ከ12:00-2:00 ሰዓት ይሰጣሉ፡፡ የስልጠና ፈላጊዎችን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ቅዳሜ እና እሁድ መርሐግብር ሊሰጥ እንደሚችልም ተገልጿል፡፡

የስልጠና ርዕሶች፦

► Tourism and Hospitality Marketing
► Hospitality leadership Management
► Tour Operation Service
► Culinary Art
► Barista Service
► Bartender Service
► Food Safety Service
► Butchery Service
► Wellness and Spa Service
► Housekeeping and Laundry Service
► Pastry and Bakery
► Food Beverage Service
► Fast Food Preparation
► Food and Beverage Control
► Front Office Service

የምዝገባ ቦታ፦ በገነት ካምፓስ ሬጅስትራር ጽ/ቤት
የመመዝገቢያ ክፍያ፦ 100 ብር

(የኢንስቲትዩቱ ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
#YHMC

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ የተመደቡ 'አዲስ የህክምና ትምህርት ኢንሼቲቭ' (NIMEI) ተማሪዎች ምዝገባ ከነሐሴ 15-17/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

አጠቃላይ ገልፃ ነሐሴ 20 እና 21/2016 ዓ.ም ይሰጣል የተባለ ሲሆን፤ ትምህርት ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦

► ሁለት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ
► የቅድመ ምረቃ ዲግሪ ዋናውና ኮፒው
► ስቱድንት ኮፒ ዋናውና ኮፒው
► ኦፊሽያል ትራንስክሪፕት ለየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ፖ.ሳ.ቁ. 257 ማስላክ ይኖርባችኋል፡፡

@tikvahuniversity
Vacancy #CBE
=======

Commercial Bank of Ethiopia would like to invite qualified and interested job seekers to apply for the following positions:

1.  IS Trainee (Head Office)
2.  Laboratory Service Officer (Head Office)
3.  Junior Laboratory Service Officer (Head Office)
4.  Graphics Designer and Video Editor (Head Office)
5.  Associate Collateral Valuator –I (Shire Endasilassie District)
6.  Associate Collateral Valuator –II (Shire Endasilassie District)
7.  Collateral Valuator (Shire Endasilassie District)
8.  District Attorney (Shire Endasilassie District)
9.  Associate District Attorney (Shire Endasilassie District)
10.  Bank Trainee (Mekelle and Shire Endasilassie Districts)

Interested and qualified job seekers should apply through CBE career website (https://vacancy.cbe.com.et) from August 12 – 18, 2024
For requirements and other detail information, please use the following link:
https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Extrenal_vacancy_09_08_2024_a4840b9198.pdf
CBE Vacancy Site User Guideline.pdf
1.5 MB
CBE Vacancy Site User Guideline

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ማመልከቻ ድረ-ገፅ (https://vacancy.cbe.com.et ) ክፍት የሥራ ቦታዎች ለማመልከት የሚረዳ መመሪያ

(ንግድ ባንክ)

@tikvahuniversity
እንኳን እስከ 400,000 ብር ለሚደርስ ሽልማት በነጻም እኮ ይዘፈናል! አሁኑኑ ወደ TikTok ሄደን ተሰጥዖአችንን እናሳይ!

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፦

🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትን ከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳትረሱ
📲የ TikTok ደረ-ገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ እንዝፈን! እንላክ! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!


#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
#ጥቆማ

በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት በ2017 የትምርት ዘመን በተመረጡ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን እንደሚቀበል አሳውቋል፡፡

የማስተርስ ፕሮግራሞች፦
1. MSc in Land Administration and Management
2. MSc in Real Property Valuation
3. MSc in Geomatics
4. MSc in Land Use Planning
5. MA in Land Law

የፒ.ኤች.ዲ. ፕሮግራም፦
1. PhD in Land Policy and Governance

ለመማር ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) በመፈተን እና አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የመሬት አስተዳደር ኢንስቲትዩት ገልጿል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፦ 0918164647 / 0977907163

@tikvahuniversity
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ከቡሉምበርግ ሚዲያ ኢኒሼቲቭ አፍሪካ ጋር በመተባበር የፋይናሻል ጋዜጠኝነት ስልጠና ሊሰጡ ነው፡፡

ስልጠናውን በተመለከተ የፕሮግራም ትውውቅ በዛሬው ዕለት የተካሔደ ሲሆን፤ ስልጠናው በዩኒቨርሲቲዎቹ የጋዜጠኝነት ተማሪዎች እንዲሁም በሥራ ላይ ላሉ ጋዜጠኞች የፋይናሻል ዘገባ ግንዛቤያቸውን የሚያሳድግ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ፣ የካፒታል ገበያ ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የሚያደርገው ስልጠናው፤ ፍላጎት ላላቸው ጋዜጠኞች ለተከታታይ ስድስት ወራት እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ወንደወሰን ሙሉጌታ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው በተለይ ወቅቱ የሚጠይቀውን የፋይናንሻል ጋዜጠኝነት ዕውቀትና ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን ለማፍራት ትልቅ ሚና እንደሚኖረው የዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አረጋ ይርዳው (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

የፋይናሻል ጋዜጠኝነት ቁጥራዊ መረጃን በትክክል መርምሮ ከመዘገብ ባለፈ የኢኮኖሚ መረጃን በግልጽ ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል፡፡ #ኢፕድ

@tikvahuniversity
#TVTI

የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የስቴም ስልጠና ማዕከል የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞችን ተቀብሏል።

የወጣቶችን እና ተማሪዎችን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሂሳብ ዕውቀትና ክህሎት ለማጎልበት እንዲሁም የፈጣራ ሃሳብ ለማሳደግ የሚሰራው ማዕከሉ፤ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኝ ወጣቶችን ዛሬ ተቀብሏል።

ማዕከሉ በኢንስቲትዩቱ አካባቢ ለሚገኙ ወጣቶች ተከታታይ ስልጠና እንደሚሰጥ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ወጣቶቹ አንድ የፈጠራ ሃሳብ ይዘው እንደሚወጡ ያላቸውን ተስፋ ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

የኢንስቲትዩቱ የስቴም ስልጠና ማዕከል STEMpower ከተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም ጋር በመተባበር ባለፈው ግንቦት ነበር የተመረቀው፡፡

@tikvahuniversity
#Infinix_Note40_Pro_Plus

ኢንፊኒክስ አዲሱን የኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G ስልኩን እጅግ ደማቅ በሆነ የጌሚኒንግ እና የሙዘቃ ዝግጅት በቃና ስቱዲዮ ለተጠቃሚዎች አስተዋውቋል!

በተለይም ለጌመሮች እና ለሙዚቃ አድናቂዎች የተለየ ነገርን ይዞ የመጣው አዲሱ የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G ስልክ ነሐሴ 4/2016 ዓ.ም በቃና ስቱዲዮ በአይነቱ ለየት ባለ ዘግጅት አዲሱን ስልኩን አንዲሁም የኢንፊኒክስ ቲቪ፣ ላፕ ቶፕ፣ ስፒከሮች፣ ስማርት ሰዓት እና ኤር ፖዶችን ለተጠቃሚዎች አስተዋውቋል፡፡

አዲሱ የኢንፊኒክስ ኖት 40 ፕሮ ፕላስ 5G ስልክ 108 ሜጋ ፒክስል ጥራት ያለው የካሜራ ቴክኖሎጂ ይዞ የመጣ ሲሆን 100 ዋት ፋስት ቻርጀር እና 20 ዋት ያለገመድ ዋየርለስ ቻርጅ ማድረግ የሚያስችል ነው፡፡ በተጨማሪም የዘመኑ የመጨረሻ የኔትወርክ ቴክኖሎጂ የሆነውን 5G ኔትወርክን ማስጠቀም የሚያስችል አቅም ያለው ሲሆን በጌመሮች እና ከፍተኛ አቅም የሚፈልጉ ስራዎችን በስልካቸው በሚከውኑ ስዎች ተመራጭ የሆነውን የ Mediatek Dimesnty 7020 ፕሮሰሰር የተገጠመለት ፈጣን ስልክ ነው፡፡

#Note40Et #Note40Pro #Note40 #Note40ProPlus #InfinixEt
2024/10/02 22:31:24
Back to Top
HTML Embed Code: