Telegram Web Link
የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤትን ይፋ አድርጓል።

ተፈታኞች ውጤታቸውን በተከታዩ ሊንክ ማየት ይችላሉ፦ harari6.ministry.et

(ወደሊንኩ ለመግባት በመጀመሪያ የስልክዎን VPN ማጥፋት ይኖርብዎታል።)

በሀረሪ ክልል የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 17-19/2016 ዓ.ም መሠጠቱ ይታወሳል።

@tikvahuniversity
#National_Exam

አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የመጀመሪያ ቀን ፈተናዎች ተሰጥተዋል፡፡

በጠዋቱ መርሐግብር የእንግሊዝኛ ፈተና የተሰጠ ሲሆን፤ ከሰዓት ተፈታኞች የሒሳብ ትምህርት ፈተና ወስደዋል፡፡

ፈተናዎቹ በወረቀት እንዲሁም በኦንላይን ሲሰጡ መዋላቸውን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተመልክቷል።

የመጀመሪያው ዙር ብሔራዊ ፈተና ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እንደሚሰጥ ይታወቃል።

@tikvahuniversity
ለመማር ዕድሜ ያልበገራቸው እናት

የ54 ዓመቷ ወ/ሮ አዲስ ተስፋዬ በሠመራ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናቸውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ።

የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዋ ወ/ሮ አዲስ፤ ከገቢ ረሱ ዞን-አዋሽ አርባ ከተማ አዲስ ተስፋ ትምህርት ቤት ነው ወደ ሠመራ ዩኒቨርሲቲ የሔዱት።

የቤተሰብ አስተዳዳሪ እና የመንግሥት ሰራተኛ የሆኑት ወ/ሮ አዲስ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተናቸውን በሠመራ ዩኒቨርሲቲ እየወሰዱ ነው።

@tikvahuniversity
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና አርሲ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በደህንነት ካሜራ (CCTV) በመታገዝ እየሰጡ ይገኛሉ።

@tikvahuniversity
2024/10/06 14:30:58
Back to Top
HTML Embed Code: