Telegram Web Link
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኦንላይንም በወረቀትም እንደሚሰጥ የሚገልጸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ አጋርቷል።

' የኦንላይን ፈተናው ቀርቷል ፣ አልቀረም ' ብሎ ውሳኔ የሚሰጠው ማዕከላዊው ትምህርት ሚኒስቴር ብቻ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር አስረግጦ በተደጋጋሚ የኦንላይን ፈተና እንደሚሰጥ አሳውቋል።

ተማሪዎች ተረጋግታችሁ ለፈተናው ተዘጋጁ።

ተማሪዎችን ውዝግብ ውስጥ የከተተው ምንድነው ?

ባለፉት ቀናት በተለይ አዲስ አበባ በተሰጠው የሙከራ ፈተና ወቅት በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ሲስቱም አስቸጋሪ ነበር።

ወላጆችም ሲስተሙ ካስቸገረ " ልጆቻቸው ዩኒቨርሲቲ ገብተው ይፈተናሉ " ተብሎ ከት/ቤት እንደተነገራቸው ለቲክቫህ ተናግረዋል።

በኃላ ግን አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ሲስተሙ ተስተካክሎ ዛሬ በተሳካ ሁኔታ የሙከራ ፈተና መፈተናቸውን ተናግረዋል።

ዛሬ ሁሉም ሳይሆኑ አንዳንድ  ትምህርት ቤቶች ለተማሪዎች " ፈተናው በኦንላይን አይሰጥም " በማለት ኮምፒዩተር እንደመለሱላቸው ተማሪዎች ተናግረዋል።

ይህ ግን በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በወረደ ትዕዛዝ እንዳልነበር እራሱ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ ላይ መመልከት ይቻላል።

ለሁሉም ግን ውሳኔ የሚሰጠው ትምህርት ሚኒስቴር ብቻ ነው።

ተማሪዎች ይህን ሀገራዊ የተማሪዎች ጉዳይ መረጃ መከታተል ያለባችሁ ከትምህርት ሚኒስቴር ብቻ መሆን አለበት።

ፈተናው መቅረቱን፣ በሌላ መንገድ እንደሚሰጥ ወይም በኦንላይን እንደሚሰጥ የሚያሳውቀው ትምህርት ሚኒስቴር ብቻና ብቻ ነው።

ሚኒስቴሩ " የኦንላይ ፈተና ቀርቷል " የሚለው ሀሰት እንደሆነ በማስገንዘብ ተፈታኞች ለኦንላይን ፈተናው እንዲዘጋጁ አሳስቧል።

ተማሪዎች ተረጋግታችሁ የትምህርት ሚኒስቴርን መመሪያ እና ውሳኔዎች ተከተሉ። አትረበሹ !

@tikvahuniversity
#2024_Commencement

12 የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ያስመርቃሉ፡፡

ዛሬ ሰኔ 29/2016 ዓ.ም ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ያሉት ዩኒቨርሲቲዎች የትኞቹ ናቸው?

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
መቱ ዩኒቨርሲቲ
➭  ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ
  ቀብሪደሀር ዩኒቨርሲቲ
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ
  ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ
አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
አርሲ ዩኒቨርሲቲ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት

@tikvahuniversity
#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ሥነ-ስርዓትን በሚሌኒየም አዳራሽ በማካሔድ ላይ ይገኛል።

አጠቃላይ ተመራቂዎች - 5,911
በሦስተኛ ዲግሪ - 337
በሁለተኛ ዲግሪ - 2,837
በቅድመ ምረቃ - 2,737

@tikvahuniversity
#ECSU

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2,269 ተማሪዎች አስመረቀ።

ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው በ2016 ዓ.ም ብቻ 79 ችግር ፈቺና የፖሊሲ ግብዓት መሆን የሚችሉ ጥናትና ምርምሮችን ማከናወኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ገልፀዋል።

አጠቃላይ ተመራቂዎች - 2,269
በሦስተኛ ዲግሪ - 27
በሁለተኛ ዲግሪ - 2,120
በቅድመ ምረቃ - 122

@tikvahuniversity
#KUE

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1,688 ተማሪዎች አስመረቀ።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ፣ በማታ እና በተከታታይ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ዩኒቨርሲቲው ጥራትና ብቃት ያላቸው መምህራን እና ተማሪዎችን ለማፍራት እየሠራ እንደሚገኝ የተቋሙ ፕሬዝዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
#ArsiUniversity

አርሲ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1,535 ተማሪዎች አስመረቀ።

ተመራቂዎቹ በቅድመ እና ድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
#AAU

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን ትምህርት በፒኤችዲ ሦስት ባለሙያዎችን አስመርቋል።

የጥበብ ከጲላጦስ መፃሕፍት ፀሐፊው ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) ከሴት ልጃቸው ጋር የዘንድሮ ዓመት ተመራቂ ሆነዋል።

ጋዜጠኛ እና ፀሐፊ ኃይለጊዮርጊስ ማሞ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሚዩኒኬሽን ክፍል ለመጀመሪያ ጊዜ በፒኤችዲ ካስመረቃቸው ሦስት ምሩቃን አንዱ ናቸው።

@tikvahuniversity
#MattuUniversity

መቱ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1,044 ተማሪዎች አስመረቀ።

50 ተመራቂዎቹ በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ሲሆኑ ቀሪዎቹ 994 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ መመረቃቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity
#ASTU

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 1,100 ተማሪዎችን አስመረቀ።

ከተመራቂዎቹ መካከል 18ቱ በዱዋል ሜጀር (በጥምር ሙያ) የተመረቁ ናቸው።

በቅርቡ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ከወሰዱ
የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ዕጩ ተመራቂዎች የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል።

አጠቃላይ ተመራቂዎች - 1,100
በሦስተኛ ዲግሪ - 32
በሁለተኛ ዲግሪ - 397
በቅድመ ምረቃ - 671

@tikvahuniversity
#DambiDolloUniversity

ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 1,596 ተማሪዎችን አስመረቀ።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በሳምንቱ መጨረሻ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
#DebreMarkosUniversity

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 1,020 ተማሪዎችን አስመረቀ።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ፣ በርቀት እና በተከታታይ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
2024/09/30 15:24:11
Back to Top
HTML Embed Code: