Telegram Web Link
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ "ስማርት ካምፓስ ፕሮጀክት" ለመተግበር የሚያስችለውን ስምምነት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ተፈራርሟል፡፡

ስምምነቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስማርት መማሪያ ክፍሎች እና የተለያዩ ዘመናዊ አሰራሮችን ለማቅረብ የሚያስችል ነው ተብሏል።

ስምምነቱ የትምህርት መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት፣ የቤተ-ሙከራ ፍተሻዎችን በተሻለ ተሞክሮ ለማከናወን፣ የምዘና ፈተናዎችን ለመስጠት የሚያስችል ስማርት የመማሪያ ክፍሎችን መገንባት እንደሚያካትትም ተገልጿል።

የስድስት ኪሎ ግቢ የመግቢያ በሮች፣ ዋና ዋና የአስተዳደር ህንጻዎችን፣ ሙዚየሙንና ሌሎች ስፍራዎች ላይ የሲሲቲቪ ካሜራ መግጠምና ተዛማጅ የመሰረተ ልማት ግንባታ የሚያካትት መሆኑም ተጠቁሟል።

ስምምነቱ የጥቁር አንበሳ አጠቃላይ ስፔሻላይድ ሆስፒታል የህክምና አገልግሎት ክፍያዎችን በቴሌብር ለመፈጸም የሚያስችል መሆኑም ተሰምቷል፡፡

@tikvahuniversity
#MoE

ትናንት የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና "የቴክኒክ ችግር" አጋጥሞት እንደነበር ትምህርት ሚኒስቴር አረጋገጠ።

ስለሆነም ፈተናውን በድጋሜ እንደሚሰጥ ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

ፈተናው በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጠዋት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እና ከሰአት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ይሰጣል ተብሏል።

ለፈተናው ተቀምጣችሁ የነበራችሁ የፋርማሲ ተማሪዎች በየተፈተናችሁበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ በመገኘት በድጋሜ የሚሰጠውን ፈተና እንድትወስዱ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

@tikvahuniversity
በፀጥታ ችግር ምክንያት በአማራ ክልል በ2016 የትመህርት ዘመን ከ2.6 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው መራቃቸውን መንግሥት ገለፀ፡፡

በክልሉ በተካሔደ የትምህርት ንቅናቄ መድረክ ላይ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ እየተጠናቀቀ ባለው ዓመት ከ3 ሺህ በላይ ትምህርት ቤቶችም ዝግ ሆነው ቆይተዋል፡፡

ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች እና መምህራን ላይም ከፍተኛ ጫናና መዋከብ እንደደረሰ ኃላፊዋ ጠቁመዋል፡፡

በርካታ በክልሉ ገጠራማ አካባቢዎች የሚገኙ ተማሪዎች ትምህርት በመቆሙ ወደ ትዳር እየገቡ እንደሆነ ከክልሉ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በቅርቡ የተሰጡትን የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎች የፀጥታ ችግር ባለባቸው የክልሉ አካባቢዎች በተለይም በምዕራብ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች አለመሰጠታቸው ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity
#2024_Commencement

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ከሳምንቱ መጨረሻ ጀምሮ ያስመርቃሉ፡፡

ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
አክሱም ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም
አሶሳ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25-26/2016 ዓ.ም
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 26/2016 ዓ.ም
ቦረና ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 26/2016 ዓ.ም
አምቦ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ደብረ ብርሃን - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#MoE ትናንት የተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና "የቴክኒክ ችግር" አጋጥሞት እንደነበር ትምህርት ሚኒስቴር አረጋገጠ። ስለሆነም ፈተናውን በድጋሜ እንደሚሰጥ ሚኒስቴሩ አሳውቋል። ፈተናው በድጋሜ ቅዳሜ ሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጠዋት ከ3:00 ሰዓት ጀምሮ እና ከሰአት ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ ይሰጣል ተብሏል። ለፈተናው ተቀምጣችሁ የነበራችሁ የፋርማሲ ተማሪዎች በየተፈተናችሁበት የፈተና ጣቢያ በሰዓቱ…
#Update

ነገ ሰኔ 22/2016 ዓ.ም በድጋሜ የሚሰጠው የ2016 ዓ.ም የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ለግማሽ ቀን ብቻ ይሰጣል።

ፈተናው ነገ በሁለት ፈረቃ ጠዋት እና ከሰዓት እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ ከተፈታኞች ቁጥር አንጻር ፈተናው ጠዋት ከ2:30 ሰዓት ጀምሮ ለግማሽ ቀን ብቻ የሚሰጥ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

በዚህ የመውጫ ፈተና የሚቀመጡት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ እና ፈተናውን በድጋሜ የሚወስዱ ተፈታኞች መሆናቸው ተገልጿል።

የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ዕጩ ተመራቂዎች በጤና ሚኒስቴር የሚዘጋጀውን የላይሰንሰር ፈተና በሌላ ጊዜ እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል።

@tikvahuniversity
#Update

የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኳል።

የተማሪዎቹ ውጤት ዛሬ ለተቋማቱ መላኩን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል።

በዚህም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የዘንድሮው የመውጫ ፈተና ለ57 የመንግሥት እና ለ124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ244 የቅድመ ምረቃ መርሐግብሮች መሰጠቱ ይታወቃል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
Photo
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዋን በመግደል ወንጀል የተከሰሰው ግለሰብ በይግባኝ በእድሜ ልክ እስራት መቀጣቱን ፖሊስ ገለፀ።

የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ የነበረችውን ግለሰብ በጩቤ ሦስት ቦታ በጀርባዋ በመውጋት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱ ይታወሳል።

በውሳኔው ቅር የተሰኘው የአሶሳ ከተማ አስተዳደር አቃቤ ህግ ይግባኝ በመጠየቅ የእስራቱ ውሳኔ እንዲሻሻል በማለት የተከሳሹን የወንጀል ድርጊት ክብደትና ድርጊቱን የሚያስረዱ የሰው ማስረጃና የህክምና ማስረጃ በማስደገፍ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ጠቅላይ ፍ/ቤት ልኳል።

የይግባኝ መዝገቡ የደረሰው የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት መዝገቡን ሲመርምር ከቆየ በኃላ፣ ተከሳሹ በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ በመሆኑ በይግባኝ ችሎት ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹንም ያርማል ማህበረሰቡንም ያስተምራል በማለት በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ከአሶሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#2024_Commencement የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ከሳምንቱ መጨረሻ ጀምሮ ያስመርቃሉ፡፡ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም አክሱም ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 23/2016 ዓ.ም አሶሳ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም ወለጋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25…
#2024_Commencement
#የቀጠለ

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ከሳምንቱ መጨረሻ ጀምሮ ያስመርቃሉ፡፡

ዲላ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 27/2016 ዓ.ም
ደምቢ ዶሎዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም
መቱ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 29/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
#RayaUniversity

ራያ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ከወሰዱ የተቋሙ ተማሪዎች መካከል 97.55 በመቶ ማለፋቸውን ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው ካስፈተናቸው 286 ተማሪዎች መካከል 279 ተማሪዎች (97.55 በመቶ) ማለፋቸውን አሳውቋል።

@tikvahuniversity
#አሶሳ_ዩኒቨርሲቲ

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም የመዉጫ ፈተና (Exit Exam) ካስፈተናቸዉ ተፈታኞች መካከል አብዛኞቹ ተፈታኞች ፈተናዉን እንዳለፉ አሳውቋል።

የውጤቱም ዝርዝር መረጃ በቀጣይ ይፋ እንደሚያደግ ገልጿል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ አመት ተመራቂ ተማሪዎች " ከሁለት አመት በፊት Add አድርገን መጨረስ የምንችላቸውን ኮርሶች በዩኒቨርሲቲው ምክንያት ባለመውሰዳችን የመውጫ ፈተና ላይም መቀመጥም ሆነ የመመረቂያ አዳራሽ ውስጥ እንዳንገኝ ዩኒቨርሲቲው ወስኖብናል " በማለት ቅሬታቸውን ለቲክቫህ አቅርበዋል። " ከሁለት አመት በፊት ከ በግዜው በኮቪድ ምክንያት በክረምት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ…
" ሰሚና አዳማጭ አቤት የሚለን አጥተን ቁጭ ብለናል " - ተማሪዎች

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ አመት ተመራቂ ተማሪዎች " ከሁለት አመት በፊት Add አድርገን መጨረስ የምንችላቸውን ኮርሶች በዩኒቨርሲቲው ምክንያት ባለመውሰዳችን የመውጫ ፈተና ላይም መቀመጥም ሆነ የመመረቂያ አዳራሽ ውስጥ እንዳንገኝ ዩኒቨርሲቲው ወስኖብናል " በማለት ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበው ነበር።

እኛም የተማሪዎቹን ጉዳይ እየተከታተልን የቆየን ሲሆን ተገቢ ምላሽ ሳናገኝ ቀርተናል።

ተማሪዎቹ ባለው ጊዜ መፍትሄ እንዲሰጣቸውና በምርቃቱ ላይ እንዲገኙ ጠይቀዋል።

ዩኒቨርሲቲው በገባው ቃል አለመገኘቱን ተከትሎ የመውጫ ፈተና ላይ እንዳልተቀመጡ ፤ ከዚህ ባለፈ የምረቃ ስነስርዓት ላይ እንዳይገኙ በመወሰኑን ቅሬታ ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

ተማሪዎቹ " ቤተሰብ ይመረቃሉ ብሎ ቢጠብቀንም መመረቂያ አዳራሽ ውስጥ እንኳን እንዳንገባ ወስነውብናል " ብለዋል።

" ሰሚ እና ችግራችንን አይቶ የሚመልስልን አካል አጥተናል " ያሉት ተማሪዎቹ " ከዩኒቨርሲቲው ሰዎች ንቀትና ያልተገባ ባህሪ ነው የምናየው " ብለዋል።

በቲክቫህ ላይ የወጣውን ዜና አመራሮቹ ቢደርሳቸውም ከቁብ ሳይቆጥሩት በውሳኔያቸው ቀጥለዋል። ከምንም በላይ ክብር እንኳን አልተሰጠንም ሲሉ ወቅሰዋል።

@tikvahuniversity
#HawassaUniversity

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2016 መውጫ ፈተና ምን ያህል ተማሪ እንዳለፈ ይፋ አደርጓል።

መረጃው ከሀዋሳ የተማሪዎች ህብረት የተገኘ ነው።

@tikvahuniversity
የ2016 ሀገር አቀፉ የሬሜዲያል ፈተና ይፋ ተደርጎ ተማሪዎች በኦንላይን ውጤታቸውን በመመልከት ላይ ይገኛሉ።

ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ነው እየተመለከቱ ያሉት።

ድረገጹ በተመሳሳይ ጊዜ ብዙ ተማሪዎች እየሞከሩት ስለሆነ ከፍተኛ መጨናነቅ አለ።

ደጋግሞ በመሞከር ውጤት መመልከት ይቻላል።

ውድና የተከበራችሁ ተማሪዎች በኮሜንት መስጫው ውስጥ ሀሳብ መቀያየር እና ጥቆማ ማስቀመጥ ትችላላችሁ።

@tikvahuniversity
#WolloUniversity

አወል ሰይድ (ዶ/ር) የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተወካይ ሆነው ተመድበዋል፡፡

የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት መንገሻ እየነ (ዶ/ር) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው በቅርቡ መመደባቸው ይታወቃል፡፡

ይህንን ተከትሎ አወል ሰይድ (ዶ/ር) በቀጣይ አመራር እስኪመደብ ድረስ ከስኔ 20/2016 ዓ.ም ጀምሮ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሥራን በተጨማሪ ደርበው እንዲሰሩ ውክልና በትምህርት ሚኒስቴር ተሰጧቸዋል፡፡

@tikvahuniversity
#2024_Commencement
#የቀጠለ

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች ከሳምንቱ መጨረሻ ጀምሮ ያስመርቃሉ፡፡

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ጅማ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ - ሰኔ 26 እና 27/2016 ዓ.ም

@tikvahuniversity
2024/09/29 23:26:39
Back to Top
HTML Embed Code: