Telegram Web Link
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ የሚያስተምሩ የተወሰኑ መምህራን “ቤት ተከራይቶ መኖር እንደከበዳቸው” ለተቋሙ ማመልከታቸውን ተከትሎ፤ በተማሪዎች ማደሪያ ዶርም “በጊዜያዊነት” እንዲኖሩ ተፈቅዶላቸው እየኖሩ መሆኑ ተሠማ።

የዩኒቨርስቲው መምህራን በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የ17 ወር ደመወዝ ያልተከፈላቸው መሆኑ፤ በአስር ሺህዎች የሚቆጠር ውዝፍ የቤት ኪራይ እንዲከማችባችው አድርጓል። 

ለመምህራን ሳይከፈል የቀረው የ17 ወር ደመወዝ ዘንድሮ “ይከፈላል ተብሎ እየተጠበቀ” መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። ውዝፍ ክፍያው ከተፈጸመ በኋላ ወደ ተማሪዎች መኖሪያ እንዲገቡ የተደረጉት መምህራን፤ ዶርሞቹን ሊለቁ እንደሚችሉ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዝርዝር ዘገባን ያንብቡ፦
https://ethiopiainsider.com/2024/13369/

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

ለ Fulbright African Research Scholars Program (FARSP) ያመልክቱ!

የዩኒቨርሲቲ መምህር ነዎት? ምርምርዎትን በዩናይትድ ስቴትስ ማከናወን ይፈልጋሉ?

ዓመታዊው የፉልብራይት አፍሪካ የምርምር ምሁራን ፕሮግራም (FARSP) 2025/26 ለአመልካቾች ክፍት ነው፡፡

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው 👇
ሐምሌ 8/2016 ዓ.ም

ለማመልከት 👇
https://apply.iie.org/fvsp2025

ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እንዲሁም ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት 👇 [email protected]

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
Tikvah-University
Photo
#ETQRA

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለ2017 የትምህርት ዘመን በከተማዋ ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

በአዲስ አበባ ለ2017 የትምህርት ዘመን የተቀመጡ መስፈርቶችን አሟልተው ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው 125 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መሆናቸውን ባለስልጣኑ ገልጿል።

(የትምህርት ቤቶቹ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
#ጥቆማ
#EthiopianAviationUniversity

የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ በማርኬቲንግ ዘርፍ የአቪዬሺን መስክ ስልጠና ለግል አመልካቾች ይሰጣል።

ለግል አመልካቾች የሚሰጡ ስልጠናዎች፦

➧ የኤርፖርት መንገደኞች አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
➧ የአየር መንገድ የስልክ ማዕከልና የቲኬት አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና
➧ የካርጎ አገልግሎት የኤጀንትነት ስልጠና

ስልጠናዎቹ ዕውቅና ያላቸው፣ እጅግ ዘመናዊ በሆነ የተግባር መለማመጃ እና ልምድ ባላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች የሚሰጡ መሆኑ ተገልጿል።

ለማመልከት 👇
https://eau.edu.et/admission/applyonline

ለበለጠ መረጃ 👇
- [email protected]
- [email protected]
- ስልክ ቁ. 0115174600 / 0115178598

@tikvahuniversity
በሀረሪ ክልል የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና መሰጠት ጀምሯል።

76 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 5,350 ተማሪዎች ለፈተናው መቀመጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ጌቱ ነገዎ ገልፀዋል።

ፈተናው በ29 የፈተና ጣቢያዎች ዛሬን ጨምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የተገኘ መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
ለ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ፌዴራል ፖሊስ ገለፀ፡፡

ለፈተናው የሚደረገውን ዝግጅት አስመልክቶ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከባለድረሻ አካላት ጋር ተወያይቷል፡፡

ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት፣ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከክልል የትምህርት ቢሮዎች እና የፀጥታ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ተብሏል።

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከትግራይ ክልል ውጭ ከሐምሌ 3/2016 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ ይታወቃል።

@tikvahuniversity
Tikvah-University
መንገሻ አየነ (ዶ/ር) የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመደቡ፡፡ መንገሻ አየነ (ዶ/ር) ከሰኔ 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸውን ሰኔ 10/2016 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ የወጣ የምደባ ደብዳቤ ያሳያል፡፡ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ፍሬው ተገኝ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን…
አዲስ የተመደቡት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መንገሻ አየነ (ዶ/ር) የሥራ ርክክብ አድርገዋል።

አዲሱ ፕሬዝዳንት የትምህርት ሚኒስቴር ተወካዮች በተገኙበት ከዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት እና የሴኔት አባላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን ራስ ገዝ ማድረግ፣ አዲሱን ተቋማዊ የሰራተኞች የሥራ ምደባ ማስፈጸም እንዲሁም የተቋሙን የምርምር ዩኒቨርሲቲነት እውን ሊያደርጉ የሚችሉ ተግባራትን ማከናወን ቅድሚያ የሚሰጧቸው ጉዳዮች እንደሆኑ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል።

@tikvahuniversity
ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለክረምት ፕሮግራም ተማሪዎች ጥሪ አድርጓል።

የነባር የክረምት ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 2 እና 3/2016 ዓ.ም ይከናወናል ተብሏል።

አዲስ የPGDT ኮርስ ተመዝጋቢዎች ምዝገባ ከሰኔ 25-30/2016 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡

የክረምት ትምህርት ከሐምሌ 08/2016 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገልጿል።

(ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
#Update

የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ውጤት ከመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ይፋ እንደሚደረግ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ሰምቷል።

የፈተናው ውጤት መቼ ይፋ እንደሚደረግ በርካታ ተማሪዎች ጥያቄያቸውን አድርሰውናል።

የፈተናው ውጤት መቼ ይገለፃል ስንል የጠየቅናቸው የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር፤ "በቅርቡ፥ ከመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት" ሲሉ መልሰውልናል።

የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና ከሰኔ 3-11/2016 ዓ.ም መሰጠቱ ይታወሳል።

@tikvahuniversity
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ትናንት የኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ የመውጫ ፈተና ለወሰዱ ተፈታኞች ፈተናው በድጋሜ ዛሬ ከሰዓት እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡

በዚህም ፈተናው በድጋሜ ዛሬ ሰኔ 18/2016 ዓ.ም ከሰዓት 8:00 ላይ እንደሚሰጥ ተፈታኞች እና ፈታኞች እንዲያውቁ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

በተመሳሳይ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ እና የኮምፒውተር ኢንጂነሪንግ የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ዛሬ ከሰዓት ፈተናውን እንደሚወስዱ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
2024/09/29 19:26:11
Back to Top
HTML Embed Code: