Telegram Web Link
በስርአተ_ትምህርት_ጥሰትና_ስታንዳርድ_ባለማሟላት_የተዘጉ_ተቋማት_ዝርዝር.pdf
901.1 KB
#AddisAbaba : በስርዓተ ትምህርት ጥሰት እና ስታንዳርድ ባለለመሟላት የተዘጉ ትምህርት ቤቶች ዝርዝር።

እነዚህ ትምህርት ቤቶች በ2017 የትምህርት ዘመን አይቀጥሉም የተባሉ ናቸው።

ፍኖተ ሎዛን በተመለከተ ግን ይህን ያንብቡ፦ https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88408

#ETQRA
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በራሳቸው የዘጉ ተቋማት ዝርዝር.pdf
1015.4 KB
#AddisAbaba

በራሳቸው የዘጉ ትምህርት ቤቶች ዝርዝርን ይመለከቱ።

#ETQRA
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ለ2017_የትምህርት_ዘመን_መስፈርቱን_አሟልተው_ምዝገባ_ማከናወን_የተፈቀደላቸው_የቅድመ_አንደኛ_ተቋማት.pdf
10.8 MB
#AddisAbaba : ለ2017 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን አሟልተው ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው የቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይመልከቱ።

#ETQRA
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ለ2017_የትምህርት_ዘመን_መስፈርቱን_አሟልተው_ምዝገባ_ማከናወን_የተፈቀደላቸው_የአንደኛና_መካከለኛ_ደረጃ.pdf
6.1 MB
#AddisAbaba : ለ2017 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን አሟልተው ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው የአንደኛ እና መካከለኛ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይመልከቱ።

#ETQRA

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ለ2017_የትምህርት_ዘመን_መስፈርቱን_አሟልተው_ምዝገባ_ማከናወን_የተፈቀደላቸው_የአጠቃላይ_2ኛ_ደረጃ.pdf
1.8 MB
#AddisAbaba : ለ2017 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን አሟልተው ምዝገባ ማከናወን የተፈቀደላቸው የአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ዝርዝር ይመልከቱ።

#ETQRA

#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#DStv

🔥 የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታዎች በድምቀት ቀጥለዋል!

ዛሬ ምሽት፡ ⚽️ Netherlands vs France ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት | 10፡00 PM በSS Football 225 ጎጆ ፓኬጅ በSS Euro2024 222 በሜዳ ፓኬጅ

🤔 ዋንጫው የማን ነው? የእርሶን አስተያየት ያጋሩን

በጀርመን የሚደረጉትን ደማቅ ጨዋታዎች በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ቻናሎች በወር ከ350 ብር ከጎጆ ፓኬጅ ጀምሮ ይከታተሉ!

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2
#RosewoodFurniture

Functional Kids room/ home library storage and desk.

Order yours today
For any inquiry :
Call us  📲   0905848586
Text us 💬   @Rosew0od

ኣድራሻ :📍4ኪሎ ኣምባሳደር ሞል 2ኛ ፎቅ 
            📍 እንቁላል ፋብሪካ ሩፋኤል
            📍 አያት አደባባይ (በቅርቡ ይጠብቁን)

ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ  👇
https://www.tg-me.com/R0seWood
https://www.tg-me.com/R0seWood
https://www.tg-me.com/R0seWood
#Tigray

➡️ " እስከ ሰኔ 30 ወደ ቄያችን መልሱን !! - ተፈናቃዮች

➡️ " ከክረምት በፊት ወደ ቄያችሁ እንድትመለሱ ከፌደራልና ከአማራ ክልል መንግስት እየተነጋገርን ነው " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ 

በእንዳስላሰ ሽረ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋ ፣ ዓዲግራት ፣ ዓብዪ ዓድዋና መቐለ የሚገኙ ከምዕራብ ፣ ከሰሜናዊ ምዕራብና ምስራቅ የትግራይ ዞኖች የተፈናቀሉ ወገኖች ዛሬ እሁድ ሰኔ 16/2016 ዓ.ም ወደ ቁያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳቸው ተነግሯል።

ከምዕራባዊ ዞን ወረዳዎች ፣ ከሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ባድመ ፣ ፀለምቲና አከባቢው  እንዲሁም ከምስራቃዊ ዞን ዛላንበሳና የኢሮብ ወረዳዎች ከቄያቸው መፈናቀላቸውን የገለጹት ተፈናቃዮቹ ፦
- እስከ ሰኔ 30 ወደ ቄያችን መልሱን !
- አርሰን እንድንበላ ወደ ቄያችን መልሱን !!
- የፕሪቶሪያ ውል በአግባቡ ይተግበር !
- የፌደራልና የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ሃላፊነታቸው ይወጡ !
- የትግራይ ግዝታዊ አድነት ይከበር !
- የተፈናቃዮች ድምፅ ይሰማ ! የሚሉና ሌሎችም መፈክሮችን አሰምተዋል።

በተለይ በመቐለ ከተማ የሚገኙ በርካታ ተፈናቃዮች በሰልፋቸው ማጠቃለያ ወደ ትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፅህፈት በመሄድ ድምፃቸው ያሰሙ ሲሆን ክረምት ከመግባቱ በአስቸኳይ ወደ ቄያችን መልሱን ብለዋል።

ሴቶችና ህፃናት የሚበዙባቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የተፈናቃይ ሰልፈኞቹ ምሬት የተሞላበት ድምፅና ሃሳብ ያደመጡትና ምላሽ የሰጡት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ " የዛሬው ሰልፍ የመጨረሻው እንዲሆንና ከክረምት በፊት እንድትመለሱ ከሚመለከተው አካል በቅንጅት እንሰራለን " ብለዋል።

" ወደ ቄያችሁ መመለስ በማስመልከት ከአማራ ክልል መንግስት እየተነጋገርን ነው " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ህዝቡ ወደ ቄየው ሲመለስ ከቂምና በቀል በፀዳ መልኩ በቦታው ከቆዩ ወንድም እህቶቻቹ  የመተማመንና የመቻቻል መንፈስ በማጎልበት በአብሮነት መኖር ይገባዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia            
#ኢትዮጵያ

ጤፍን ጨምሮ በሌሎች የግብርና ግብዓት ምርቶች ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መሆናቸውን የሚወስነዉ መመሪያዉ ተግባራዊ መደረግ እንደጀመረ ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

የገንዘብ ሚኒስቴር በአገር ውስጥ የሚመረቱ እና ከውጭ አገር የሚገቡ እቃዎች እንዲሁም በአገር ውስጥ የሚሰጡ አገልግሎቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ መሆናቸውን አረጋግጧል።

ከሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ በተጀመረው በዚህ መመሪያ ዉስጥ የእህልና ጥሬጥሬ ፣ የግብርና ምርቶች እና የበሰሉ ወይም የተዘጋጁ ምግቦች / መጠጦች ይገኙበታል ።

በዚህ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ የሚሆኑ  እቃዎችን ለመወሰን በወጣው  መመሪያ ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል መሰረታዊ የሆኑ የምግብ አቅርቦቶችን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ ሆኖ እንዲገዛ ማድረግ የወጪ ጫናውን በማርገብ ረገድ ጠቀሜታ አለው ተብሏል።

ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ከተደረጉት መካከል ፦
➡️ ጤፍ፣
➡️ ስንዴ፣
➡️ ገብስ ፣
➡️ ማዳበሪያ ፣
➡️ የእንስሳት መድሃኒት እንዲሁም በካፒታል ሊዝ ስምምነት የሚቀርብ የካፒታል ዕቃዎች ይገኙበታል።

መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia
BK  C  O  M  P  U  T  E  R S

ማንኛውንም አይነት አዳዲስ ላፕቶፖች ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች ዴስክ ቶፖችን ጨምሮ ከብዛትና ቅናሽ ጋር ያዘንላቹ መተናል።
ለቢሮዎች ፣ ለተማሪዎች፣ለግሪፊክስ ዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች እንዲሁም ለጨረታ የሚሆኑ በጥራት እና በ ብዛት  ከ1 አመት ዋስትና ጋር እኛ ያገኛሉ።

የላፕቶፕ አማራጮችን ለማየት የቴሌግራም ፔጃችንን Join ያድርጉ https://www.tg-me.com/BKComputers
Inbox @bkcomputer27
አድራሻ አዲስ አበባ መገናኛ ሲቲ ሞል ከ መሰረት ደፋር ህንፃ አጠገብ 1 ፎቅ ላይ እንገኛለን ፤ 0911448148. 0955413433
we make IT easy!
#ሴጅ_ማሰልጠኛ

20% ቅናሽ ሊጠናቀቅ 5 ቀናት ቀሩት ፤ ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ
Telegram: https://www.tg-me.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
#EthiopianOrthodoxTewahedo

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዓመቱ ውስጥ ከሚጾሙ አጽዋማት መካከል  ' ጾመ ሐዋርያት ' (በተለምዶ የሰኔ ጾም) በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።

ይህ ጾም የሚፈሰከው ሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ/ም ነው።

ከሰባቱ የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነው ጾመ ሐዋርያት በየትኛውም አመት ላይ ቢውል ሰኞ ቀን ከሚጀምሩት አፅዋማት አንዱ ነው፡፡

ይህ ጾም የሚፈሰክበት ከሐምሌ 5 አይበልጥም ፤ የሚጀመርበት ቀን ደግሞ በዓለ ጰራቅሊጦስ እንደ ገባ ባለው የመጀመሪያው ሰኞ ነው።

እንደ ቤተክርስቲያኗ አስተምሮ ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ሰማያዊ ተልእኮ ስለተሰማቸው ከ5ዐ ቀን በኋላ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ማግስት የጀመሩት ጾም ነው።

ጾሙ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ነው።

ቤተክርስቲያኗም ትንሳኤ ከዋለ ከበዓለ 50 በኃላ የፆሙን አዋጅ ለልጆቿ አውጃለች።

ይህ ጾም እንደ ሌሎቹ አጽዋማት ሁሉ እያንዳንዱ ምእመን ሊጾመው የሚገባ እንደሆነ ቤተክርስቲያን ታዛለች።

ከዚህ ጾም በኃላ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል የሆነው ጾመ ድኅነት (ረቡዕ እና ዓርብ) የሚጀምር ይሆናል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 “ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል። የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ…
🇪🇹 የፓለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ መንግስት እንደ መንግስት ሥራውን እየሰራ አይደለም ” ሲል ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ተቸ።

የፓርቲው ሊቀመንበር ፤ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ስለወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች የፓርቲያቸውን ምልከታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርተዋል።

ሊቀመንበሩ በነበራቸው ቆይታ  ፦
- የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ጉዳይ
- የኑሮ ውድነት
- የሰላም እና ጸጥታ ጉዳይ
- ከሰሞኑን እየወጡ ስላሉ አዳዲስ አዋጆች
- ስለ ፖለቲካ ህዳሩ
- የመልካም አስተዳደር እጦት
- የኢኮኖሚ ጉዳይ ... ሌሎችም ተነስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም " መፍትሄው ምንድነው ? " ሲል ላቀረበው ጥያቄ ፓርቲው ምላሽ ሰጥቷል።

ምጣኔ ሀብትን በተመለከተ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ምን አሉ ?

“ የMacro Economy መናጋት አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የከፋ ሁኔታ ላይ ደርሷል።

የኢትዮጵያ የልማት ስትራቴጂ ሁኔታዎችን ያላገናዘበ ነው።

ይልቁንም ትኩረት የሚሹት ፦
➡️ ኢንፍራስትራክቸር፣
➡️ መብራት፣
➡️ ጤና፣
➡️ ውሃ መሠረታዊ ችግሮች ናቸው፤ ዜጎች በእነዚህ ነገሮች ተቸግረዋል።

ብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ በሚል የሚሰራቸው ፕሮጀክቶች መቃኘት አለባቸው።

ከፍተኛ የሆነ የንግድ ጉድለት አለ። የምንሸጠው እና የምንገዛው ልዩነቱ የሰፋ ነው። የበጀት Deficit አለ።

መንግስት የሚሰበስበውና የሚያወጣውን ገንዘብ ለዚያውም አስፈላጊነታቸው አጠራጣሪ ፕሮጀክቶች ላይ ገንዘቡ ወጪ ይሆናል።

ይሄ ኢኮኖሚው እንዲናጋ አድርጓል ብለን እናምናለን።”

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-24

#ነእፓ #ኢትዮጵያ #የፖለቲካፓርቲዎችምንይላሉ?
#AddisAbaba

ግለሰብን አግተው የዘረፉ የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመሰረተ።

አንድን ግለሰብ አስገድደው በያዙት ተሽከርካሪ ውስጥ በማገት ዶላርና የተለያዩ ንብረቶቹን ወስደዋል የተባሉ 3 የፖሊስ አባላት ላይ የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቷል።

3ቱ የፖሊስ አባላት ፦
ኮንስታብል ክብሩ በለጠ
ረ/ሳጅን ያለምሰው ዱሬ
ረ/ሳጅን ባህረዲን አለሙ ይባላሉ።

1ኛው ተከሳሽ በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ መምሪያ የተጠርጣሪ አስተዳደር ስር የጥበቃ አባል፣

2ኛው ተከሳሽ የተጠርጣሪ ክትትል እና ኦፕሬሽን ክፍል የኢኮኖሚ ነክ ጉዳዮች ወንጀሎች የፍርድ ቤት አስገዳጅ አባል፣

3ኛው ተከሳሽ በፎረንሲክ ምርመራ መምሪያ ስር በሹፌርነት ሲሰሩ ነበር።

ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ በ9 ሰዓት አካባቢ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 '  ጆን ጋራዥ  ' አካባቢ ካልተያዘ ሲቪል ከለበሰ ግብረአበራቸው ጋር በመሆን አንድ የግል ተበዳይን አስገድደው 3ኛ ተከሳሽ ለስራ አላማ የተረከበው ተሽከርካሪ ውስጥ በማገት ያስገባሉ።

አግተው ተሽከርካሪ ውስጥ ካስገቡም በኃላ ከግል ተበዳዩ ፦
° 2 ሺህ 600 ዶላር፣
° 2 የእጅ ስልክ
° 50 ሺህ ብር አስገድደው በመውሰድ ከተሽከርካሪው ገፍትረው ጥለውት እንደሄዱ በዐቃቤ ህግ የቀረበው የክስ መግዘብ ያስረዳል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዐቃቤ ሕግ የተመሰረተውን ክስ ዝርዝር ለተከሳሾች እንዲደርሳቸው ካደረገ በኋላ ጉዳያቸውን ማረሚያ ቤት ወርደው  እንዲከታተሉ በማዘዝ ለሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
2024/06/24 13:08:05
Back to Top
HTML Embed Code: