Telegram Web Link
" የተፈጸመው ወንጀል ጭካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ወንጀል ነው " - ፖሊስ

በጫጉላ ምሽት ሚስቱን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን የሃላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

ሟች ሪባቴ ትባላለች።

ሟች እና ወንድሟ በግድያ ተጠርጣሪው ግለሰብ አማካኝነች ቁርዓን እንደሚቀሩ ከሟች እህት አመደልሃዲ አንደበት ለመስማት ተችሏል።

ተጠርጣሪው ሟችን ማግባት እንደሚፈልግና ለሟች ወንድም በጓደኛው አማካኝነት ሃሳቡን ይገልጽለታል።

የሟች ወንድም አብዱልሃዲም ሟች እህቱን " ተስማምተሻል ወይ ? " በሚል መጠየቁንና ከሀፍረት መግለጽ ብትፈራም እንደተስማማች በመረዳቱ ወደ ጋብቻ ቅድመ ሁኔታው ማለፋቸውን ይገልጻል።

ከዚያም ወደ ጥሎሽና ኒካህ ተኪዷል።

ኒካህ ከታሰረ በኃላ ከለሊቱ 10 ሰዓት ገደማ ስልክ ተደወለልኝ የሚለው ወንድሟ " ሪባቴ ታማለች ና " ተብሎ ተነገረኝ ሲል ሁኔታውን አስታውሷል።

ወደ ቤታቸው ሲሄድ ግን ቤቱ በፖሊስ ተከቦ ነበር።

ሌላኛው የሟች ወንድም በርገና  " አባቴ ኒካህ እሰር ብሎ ከወከለኝ ቀን ጀምሮ ያለው ነገር ብቻ ነው ማውቀው ከዚያም ወንድሜን ወከልኩት ኒካሀው ታሰረ አለኝ ከዛ ለሊት 10 ሰዓት ስልክ ተደወለልኝ ቦታው ስንደርስ ቤቱ በፖሊስ ተከቧል " ሲል ገልጿል።

" በጭራሽ ያልገመትነው ነገር ሆኖ አገኘን " የሚለው የሟች ወንድም " ፖሊሶች እኛ ወደ አስክሬኑ እንዳንጠጋ አድርገው አስክሬኑን ወደ ሆስፒታል ወስደው እሱን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስዱት " በማለት አስረድቷል።

" ለሟች እህታችን ተገቢው ፍትህ ተሰጥቶን ተጠርጣሪው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኝ እንፈልጋለን " ብሏል።

የሃላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ በበኩሉ ድርጊቱ ከተፈጸመበት ሰዓት አንስቶ ተጠርጣሪውን በህግ ጥላ ስር አውሎ 5 አባላት ያለው መርማሪ ቡድን በማዋቀር ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አመልክቷል።

የተፈጸመው ወንጀል " ጭካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ወንጀል ነው " ሲል ገልጿል።

ፖሊስ የተጠርጣሪውን የእምነት ክህደት ቃል እንደተቀበለና በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርመራው አልቆ  ውሳኔ እንዲያገኝ እንደሚሰራ አመልክቷታ።

የሃላባ ህዝብ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና መረጃ በመስጠት ላደረገው ርብርብ ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሀሩን ሚዲያ ነው። #HarunMedia

@tikvahethiopia
#USA

ዶላንድ ትራምፕ በቅርብ በሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉና ፕሬዜዳንት ከሆኑ ፥ " በአስቸኳይ የስደተኞችን ወረራ አስቆማለሁ፣ ማንኛውም አይነት የህገወጥ ስደተኞችን በረራ እንዲቆም እንዲሁም በማንኛውም መንገድ ወደ አሜሪካ ምድር እንዳይገቡ አደርጋለሁ " ብለዋል።

ከዚህ ባለፈ በስልጣን ዘመናቸው በአሜሪካ ታሪክ ትልቅ የተባለ ዲፖርቴሽን (ከሀገር የማስወጣት) ስራ እንደሚሰሩ ከወዲሁ ተናግረዋል።

" ከአሜሪካ ምድር ጓዛቸውን አስይዘን ወደ መጡበት እንልካቸዋለን " ያሏቸው ዶክመንት አልባ ህገወጥ ስደተኞችን ነው።

በስድተኞች ጉዳይ ላይ ያላቸው አቋም ከዚህ ቀደምም የሚታወቀው ትራምፕ አሁን ስመጣ " አጠነክረዋለሁ " እያሉ ለደጋፊዎቻቸው ቃል በመግባት ላይ ናቸው።

" ከተሞቻችን አድንላችኋለሁ " እያሉ ያሉት ትራምፕ ቢያንስ ቢያንስ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን ህገወጥ ስደተኞችን ከአሜሪካ ለማስወጣት እቅድ አላቸው ተብሏል።

ምናልባትም ተመርጠው ፕሬዜዳንት ከሆኑ በኃላ ይሄን ሁሉ የሰው ቁጥር እንዴት ከአሜሪካ ዲፖርት እንደሚያደርጉ ለጊዜው በዝርዝር የሚታወቅ ነገር የለም።

#USA #deport

@tikvahethiopia
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የመስቀል በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡

እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ፡፡

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!! ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
[Telegram] [Facebook]
                              
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ    
    የስኬትዎ አጋር!

https://www.tg-me.com/LionBankSC
#WELL_Computer

ለተማሪዎች እና ለሠራተኞች ታላቅ ቅናሽ !ጥሩ ላፕቶፕ ለመግዛት አሰበዋል? እንግዲያውስ 𝐖𝐄𝐋𝐋 ኮምፒውተር አለልዎት!

እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የ2023/24 ሞዴል ላፕቶፖች እና ኮምፒዩተሮችን ለጨረታም ሆነ ለግልዎ፣ የተለያዩ አዳዲስ ጌሚንግ እንዲሁም ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖችን ከአስተማማኝ ዋስትና ጋር እናቀርባለን።

አድራሻ፦ መገናኛ ከዘፍመሽ ዝቅ ብሎ 3ኤም ሲቲ ሞል / 3M City Mall 1ኛ ፎቅ ቁ. FL04 Well Computer

የሚፈልጉትን ላፕቶፕ ይምረጡ፦ https://www.tg-me.com/welllaptop የአንድ ዓመት ሙሉ ዋስትና
Call Us: @cr7_well
ስልክ ፦0943847549 / 0910238672
#Urgent🚨

በሊባኖስ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥሪ ቀርቧል።

በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤት በተለይ በደቡብ እና ምሥራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥሪ አቅርቧል።

ጽ/ቤቱ በደቡብ እና ምሥራቅ ሊባኖስ ያለው የፀጥታ ችግር እየተባባሰ እንደመጣ አመልክቷል።

ይህን ተከትሎ በአካባቢዎች ያሉ ዜጎችን ለይቶ ማወቅ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ጠቁሟል።

በአካባቢው የሚኖሩ ወገኖች ከታች በተቀመጠው መሠረት ፦

➡️ ስማቸውን ፓስፖርት ላይ እንደተፃፈው፣

➡️የፓስፖርት ቁጥር

➡️ ስልክ ቁጥራቸውን እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡

° በደቡብ ሊባኖስ (ታየር ፣ ሱር ፣ ቢንት ጅቤል ፣ ማርጃዩን፣ ነበትዬ፣ ሳይዳ እና አካባቢው) የሚገኙ ወገኖች በስልክ ቁጥር 03-7354 51 ወይም 03-87-10-89

° በምሥራቅ ሊባኖስ (አልቤክ፣ ቤካ ሸለቆ እና አካባቢው) የሚገኙ ደግሞ በስልክ ቁጥር 81 77-62-51 ወይም 81-63-07-98 በመደወል እንዲመዘገቡ ጄኔራል ጽሕፈት ቤት አሳስቧል፡፡

#Share #ሼር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " እኔ ድርድር ያስፈልጋል በሰላም ይፈታ ስል ፤ እሱ ግን ' ከማን ጋር ነው የምንደራደረው ? ' ነበር ያለው " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፤ ጄነራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ስልጣን ለመጠቅለል በማቀድና የቆየ ቂም ለመወጣት በሚል ከሰሱ። በደብረጽዮን (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ባሳለፍነው ሳምንት የመጨረሻ ቀናት መቐለን ጨምሮ በተለያዩ የትግራይ ከተሞች…
#Tigray
 
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፥ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራውን የህወሓት ቡድን አስጠነቀቁ።

ፕሬዜዳንቱ በማስጠንቀቂያቸው " ቡድን " ሲሉ የጠሩት ሃይል የወረዳና የከተማ የህዝብ ምክር ቤቶች ለመረበሽ እየሄደበት ያለው ርቀትና በማድረግ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ማቆም አለበት ብለዋል።

መስከረም 14/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንቱ ፊርማ ተፈርሞ ለሁሉም የወረዳና የከተማ ም/ቤቶች የተፃፈው የማስጠንቀቅያ ደብዳቤ " የህዝብ ምክር ቤቶች የትግራይ ጊዚያዊ መንግስትና የህዝቡ አካል እንጂ የህወሓት መዋቅር አለመሆናቸው አውቆ ' ቡድኑ ' የራሱ መሳሪያ ለማድረግ እያካሄደ ያለውን መሯሯጥና ውንብድና ማቆም አለበት " ይላል።

ስለሆነም ምክር ቤቶቹ የመንግስትና የህዝብ መዋቅር መሆናቸው በማመን ' ቡድኑ' ምክር ቤቶቹ በመጠቀም ያልደገፉትንና ሃሳቡ ያልተቀበሉት የመንግስት ሹመኞች ጥላሸት ለመቀባትና ከሃላፊነት ለማውረድ የሚያደርገው ጥረት መቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል።

ምክር ቤቶቹም ይህንን የመንግሰትና የፓለቲካ ድርጅት የሚቀላቅል ህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ማውገዝ አለባቸው ብሏል።

" ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን ህግና ስርዓት ለማስከበር ሲባል ወደ ህጋዊ ተጠያቂነት መሸጋገር የግድ ይሆናል " በማለት አክለዋል።  

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ከቀናት በፊት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ  ያወጣውን የአቋም መግለጫ የሚቃወም መግለጫ  አውጥቷል።

በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት መስከረም 14/2017 ዓ.ም ያወጣው  ባለ 4 ነጥብ የተቋውሞ መግለጫ ፤ " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጊዚያዊ  ስራዎች ለመስራት መቋቋሙ ተዘንግቶ ከተቀመጠለት የቆይታ የጊዜ ሰሌዳ በላይ እንዲቆይና ራሱን ወደ ተሟላ የመንግስት ሃላፊነት  ለመለወጥ የሚያደርገው ጥረት ፀረ ዴሞክራሲና ኢ-ህገመንግስታዊ ነው " ብሏል።

ምንም እንኳን " ኢ-ህገመንግስታዊ " ብሎ ቢገልጽም የአገር ወይም የክልሉ ህገ-መንግስት አንቀፆችን አላጣቀሰም።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ቡድን " ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጠው ተልእኮ ወደ ጎን በመተው ህወሓት ለማፍረስ ፣ ሰራዊት ለማዘዝና የመንግስትና ህዝብ ሃብት በመጠቀም የትግራይ ህዝብ አንድነት ለመበተን እየሄደበት ያለውን የተሳሳተ መንገድ ሊያቆም ይገባል " ሲል አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

አዲስ አበባ ውስጥ ከነገ ማለዳ 12 ሠዓት እስከ ዓርብ ማለዳ 12 ሠዓት ድረስ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ተከለከለ።

የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ፥ " ለመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የመንገድ ትራንስፖርት ደህንነት ሲባል ከመስከረም 16 እና 17 ቀን 2017 ዓ.ም ማለዳ 12 ሠዓት ድረስ በመዲናዋ የሞተር ብስክሌት የትራንስፖርት አገልግሎት ተከልክሏል " ሲል አሳውቋል።

የትራንስፖርትና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እና የትራፊክ ፖሊሶች አፈፃፀሙን ተግባራዊ እንዲያደርጉም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#MPESASafaricom

በዕለታዊ የዳታ ጥቅሎች ቀኑን ሙሉ ፈታ እንበል! 🥳 በM-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው! 

በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በፈጣን ዳታ እንንበሽበሽ!

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ: https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቦታችንን https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#SafaricomEthiopia
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
" ወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በአጠቃላይ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል " - የዞኑ ፖሊስ መምሪያ

በወላይታ ሶዶ ዞን ዛሬ (ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም) ከቀኑ 7 ሰዓት ደረሰ በተባለ የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ሕይወት ሲያልፍ በ47 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡

አደጋው የደረሰው መነሻውን ከወላይታ አድረጎ ወደ ዳውሮ ዞን ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ፓፓታ ቀበሌ ሲደርስ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል፡፡

በአደጋው የሞቱትና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ምን ያክል ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ንጋቱ በሰጡን ምላሽ፣ " በወደ 28 ሰዎች ናቸው የሞቱት፡፡ በ14 ሰዎች ከባድ፣ በ5 ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሷል " ብለዋል።

" አጠቃላይ ወደ 47 ሰዎች ላይ ሞት፤ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል " ብለዋል፡፡

" ከሕጻን እስከ አዋቂ ድረስ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ጉዳት የደረሰባቸው " ነው ያሉት፡፡

" የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል፡፡ አሁን ወደ 8 ሰዎችም ወደ ከፍተኛ ህክምና ሪፈር እየተላኩ ስለሆነ ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል " ሲሉ ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡

አደጋው የደረሰበት ምክንያት ታውቋል ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ " የቴክኒክ ምርመራ ተደርጎ ወደፊት ነው የሚገለጸው፡፡ ለአሁን ግን ዳገት ተሽከርካሪው ዳገት እየወጣ እስክራፕ ነው የገጠመው፡፡ ከትልቅ ዳገት ላይ ወደ ቁልቁለትና ርቀት ባለው ወንዝ ውስጥ ነው አጠቃለይ ተሳፋሪዎችን ይዞ የገባው " ሲሉ መልሰዋል።

ተሽከርካሪው ስንት ሰዎችን ነበር ያሳፈረው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ፣ " አጠቃላይ ቁጥሩን እየመዘገብን ነው፡፡ እስካሁን ባለው መረጃ በ47 ሰዎች ላይ ነው ሞትና ጉዳት የደረሰው፡፡ ጉዳት ሳይደርስባቸው የተረፉ ወደ 6 ሰዎች አሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

" ጠቅላላ ተሳፋሪዎቹ ከ56 እስከ 60 ሰዎች ይደርሳል የሚል ግምት አለን " ነው ያሉት፡፡

" ቦታው ወንዝ ውስጥ ነው፡፡ የአካባቢው ማህበረሰብም የጸጥታ ኃይልም ተረባርቦ ጉዳት የደረሰባቸውን የማንሳት፣ የተጎዱ በፍጥነት ወደ ህክምና እንዲደርሱ እየተደረገበት ያለ ሁኔታ አለ " ነው የተባለው፡፡

ምን ያክል ሰዎች ናቸው ወደ ሕክምና የተላኩት ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ፣ " ጠቅላላ ወደ 21 ሰዎች ወደ ወደ ሆስፒታሎች ተልከዋል፡፡ 8 ሰዎች ከሆስፒታል ሪፈር ተብለው ወደ ክርስቲያን ሆስፒታል ተጭነው እየወጡ ያሉት ሁኔታ ነው ያለው " ተብሏል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

ነገ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ተደርገዋል።

መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

መስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5:00 ሰአት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የሚከተሉት ናቸው።

- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ

- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)

- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ

- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ

- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ

- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ

- ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ

- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከመስከረም 16 ቀን 2017 ዓ/ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ይዘጋል።

በተጨማሪም በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ ነው።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
2024/09/26 04:37:48
Back to Top
HTML Embed Code: