Telegram Web Link
#MesiratEthiopia

አስፈላጊ መረጃ! የሐዋሳ ኢንፎ ሴሽን የቦታ ለውጥ
📍 አዲሱ አድራሻ፦ ሳውዝ ስታር ሆቴል (South Star Hotel)፣ ሐዋሳ
🗓 መስከረም 20, 2017 ዓ.ም
🕒 ከጠዋቱ 3:30 እስከ 6:30 ሰዓት

የመስራት ፕሮግራም ንግድዎን እንዴት ማጎልበት እንደሚችል፣ ስለ ሥራ ፈጠራ ፕሮግራማችን ቁልፍ ግንዛቤዎች እና ስለ ቴሌግራም ቦት ስልጠና ጥቅሞች ምንመለከትበት ዝግጅት ነው።

ከታች ባለው ሊንክ ተመዝገቡ!
https://forms.gle/RFt2RTUhznLSi7np9

#Mesirat #Entrepreneurship #Hawassa #BusinessGrowth
“ 21 ቤቶች ከአገልግሎት ውጪ ሆነዋል፡፡ አያገለግሉም፤ መልሶም ለማልማትም በጣም አስቸጋሪ ነው ” - የደሴ ከተማ አስተዳደር

በአማራ ክልሏ ደሴ ከተማ ሆጤ ክፍለ ከተማ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ/ም ሌሊት ባተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ በሰዎች ሕይወት ላይ ጉዳት ባይደርሰም በመኖሪያ ቤቶች ላይ ውድመት እንደደረሰ ከተማ አስተዳደሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡

የከተማዋ የኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ነስረዲን ኃይሌ “ ቄራ የሚባል አካባቢ ነው የመሬት መንሸራተቱ የተከሰተው ” ብለዋል፡፡

“ መንሸራተቱ ተፈጥሯዊ በሆነ ምክንያት ከክረምቱ ክብደት ጋር ተያይዞ የተከሰተ ነው፡፡ እስካሁን 21 አባወራዎች (በቤተሰብ አባላት ደረጃ 116 ግለሰቦች) ከቦታቸውና ከንብረታቸው ላይ ተፈናቅለው ወደ ካምፕና ዘመድ ቤት ተጠግተዋል ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

“ 21 ቤቶች ከአገልግሎት ውጪ ሆነዋል (እስከ ትላንትና ምሽት ድረስ ዳሜጅ ሆነዋል)፡፡ ኦረዲ አያገለግሉም፡፡ መልሶም ለማልማትም በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ በሰዎች ሕይወት ግን ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ” ነው ያሉት፡፡

ከዚህ ቀደም እንዲህ አይነት አደጋ ተከስቶ ያውቃል እዚሁ አካባቢ ? ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ፣ “ እንደከተማ ሦስተኛ ቦታ ላይ ነው ይሄ የመሬት መንሸራተት የተከሰተው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የአሁኑ የመንሸራተት አደጋ እንደቀጠለ ነው ወይስ ቆሟል ? ምንስ እየተሰራ ነው ? ለሚለው ጥያቄ ፣ “ ችግሩ በመሠረቱ ጨምሯል አሁን፡፡ እዛ አካባቢ ላይ ያሉ ነዋሪዎችን የማንሳት ሥራም የከተማ አስተተዳደሩ ሰርቷል ” ብለዋል።

“ ትላንት ከተከሰተ በኋላ ዛሬ አዳር ላይ ሊከሰት ይችላል ብለን በሰጋንባቸው ቦታዎች ሙሉ ለሙሉ ግለሰቦችን አንስተን በቅርብ ዘመድ ያላቸው ወደ ዘመድ ቤት እንዲሄዱ፤ ካልሆነ ደግሞ ከተማ አስተዳደሩ ካምፕ አዘጋጅቶ እዚያ ካምፕ ላይ እንዲያድሩና አሰፈላጊውን ጊዜያዊ ድጋፍ እያደረግን ነው ” ብለዋል፡፡

" የመሬት መንሸራተቱ የሚያሰጋቸውን
አካባቢዎች የግለሰቦችን ንብረት ጭምር የማሸሽ ሥራ ትላንት ተሰርቷል ” ሲሉ አክለዋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-09-24-2

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቤንዚን ? በአዲስ አበባ ቤንዚን ረጅም ሰዓት ሰልፍ ሳይሰለፉ ማግኘት ዘበት ከሆነ ሰነባብቷል። ባለፉት ሳምንታት በትንሽ በትንሹ የጀመረው የቤንዚን ሰልፍ ከሰሞኑን እጅግ ብሶበታል። በአንዳንድ ማደያዎች " ቤንዚን የለም " እየተባለ ሲለጠፍ ቤንዚን ያለባቸው ማደያዎች እጅግ በጣም ረጅም ሰልፍ ነው ያለው። በዚህም ምክንያት የመኪና አሽከርካሪዎች ቀናቸውን በቤንዚን ሰልፍ ለማሳለፍ እየተገደዱ ይገኛሉ።…
#ቤንዚን

° " ቤንዚን ማግኘት ፈተና ሆኖብልናል " - አሽከርካሪዎች

° " የቤንዚን አቅርቦት ችግር የለም " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን

አሁን ላይ በአዲስ አበባ ቤንዚን ማግኘት አስቸጋሪ እንደሆነባቸው አሽከርካሪዎች እየገለጹ ናቸው።

የተለያዩ ማደያዎች ላይ " ቤንዚን የለም " የሚል የተለጠፈ ሲሆን ቤንዚን አለባቸው የሚባሉና የሚቀዳባቸው ማደያዎች ላይ እጅግ በጣም ረጅም ሰልፎች ነው ያሉት።

አሽከርካሪዎች ቤንዚን ለመቅዳት ሰዓታትን ለመሰለፍ እየተገደዱ ነው። በዚህም ቀናቸውን በሰልፍ እያሳለፉ በመሆኑ ስራቸው እየተበደለ ነው።

ምንም እንኳን ከሰሞኑን ችግሩ ብሶ ቢታይም ባለፉት ሣምንታት አንዳንድ ቦታዎች ላይ ሰልፎች ይታዩ ነበር።

ለመሆን ምንድነው የተፈጠረው ?

በዚህ ጉዳይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን መ/ቤትን ማብራሪያ ጠይቋል።

የተፈጠረው ነገር ምንድን ነው ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የባለስልጣኑ አንድ አካል በሰጡን አጭር ማብራሪያ፣ " የቤንዚን እጥረቱ የለም " ብለዋል፡፡

በከተማዋ ያለውን ችግር በተመለከተ ፤ " የእኛ ልጆች ኢስፔክሽን ሲወጡ ያዩት ነገር አሁን የቴሌ ብር አጠቃቀም ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ ነው፡፡ ምክንያቱም በካሽ ግብይት መፈጸም አይቻልም ፤ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ስለሆነ አብዛኛው ሰው ያንን ሲስተም ሳይጠቀም ቆይቶ በካሽ ትራንሰፈር እያደረገ ነበር፡፡ በዚያ ምክንያት አንዱ ከማደያ ላይ ነዳጅ ቀድቶ ለመውጣት ረጅም ሰዓት ይወስዳል " ብለዋል፡፡

" እናም ረጃጅም ሰልፍ የሚፈጠረው በዛ ነው እንጅ በእጥረት አይደለም " ብለው ለተጨማሪ መረጃ ወደ ሌላ የሚመለከተውን የተቋሙ አካልን የመሩን ሲሆን ሌላኛው አካል ማብራሪያ ለመስጠት ለዛሬ ቀጠሮ ቢሰጡም በቀጠሮ ሰዓት በተደጋጋሚ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

በሌላ በኩል ፥ ባለስልጣን መ/ቤቱ ለካፒታል ጋዜጣ በሰጠው ቃል ፥ በአዲስ አበባ ከተማ በአማካይ እስከ 1.4 ሚሊየን ሊትር ቤንዚን እያቀረበ መሆኑን አመልክቷል።

" በአዲስ አበባ ከሰሞኑ በነዳጅ ማደያዎች ላይ የተስተዋለው ያልተለመደ ሰልፎች ባለፈው ሣምንት በነበሩት ሁለት ቀናት ከበዓላት ጋር በተያያዘ የአቅርቦት መቀነስ በመኖሩ ነዉ " ብሏል።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ፥ " በከተማዋ በቀን በአማካይ እስከ 1.4 ሚሊየን ሊትር ቤንዚን የሚቀርብ ቢሆንም የማደያዎቹ አገልግሎት አሰጣጥ ዝግታ መኖሩ እና የቤኒዚን ምርት ላይ ከፍተኛ የጥቁር ገበያ ፍላጎት መኖር ሠልፎችን ምክኒያት በማድረግ የአቅርቦት ዕጥረት ያለ በማስመሰል አጋጣሚውን ለትይዩ ገበያዉ ለመጠቀም መሞከር ይታያል " ሲል አስረድቷል።

" ከነዳጅ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ያለው ሁኔታ በአፋጣኝ እንዲስተካከል የተደረገበት እርምጃ እንዲወሰድ ተደርጓል " ያለዉ መ/ቤቱ " በዚህም በመዲናዋ ከመደበኛ ኮታ ተጨማሪ ቤንዚን እንዲቀርብ ሆኗል " ሲል አስታዉቋል።

" የየቤኒዚን ተጠቃሚ አሽከርካሪዎች አቅርቦት በበቂ ሁኔታ መኖሩን ተረድተው በተለያዩ አከባቢዎች የሚገኙ ማደያዎችን በመጠቀም መገልገል ይችላሉ " ሲል አሳስቧል።

#AddisAbaba #Benzine

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara “ የእኛ አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶቻችን ደረጃ 2 ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ደረጃቸው ዝቅተኛ ግን መማር ማስተማሩን ማስኬድ የሚችሉ እንደማለት ነው ” - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በአማራ ክልል በተለይ በጸጥታ ችግር ሳቢያ የግብዓት እጥረት ያለባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳሉ፣ ይህም ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ማነቆ እንደሆነባቸው ወላጆች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገጸዋል፡፡ ለአብነትም እንደ…
#Amhara #Education

" ልጆች ወደ ትምህርት ቤት ገብተው እንዲማሩ ሁሉም ይተባበር " - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

ለ2017 ትምህርት ዘመን ምን ያህል ተማሪ ተመዘገበ ?

በአማራ ክልል ፣ ባለፈው ዓመት ት/ቤት መግባት ከነበረባቸው 6 ሚሊዮን ተማሪዎች መካከል ግማሽ ያክሉ በክልሉ ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ትምህርት እንዳልተከታተሉ በወቅቱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አመልክቷል።

በተለይም በጎጃም ቀጠና የሚገኙ አብዛኛዎቹ የ6ኛ፣ የ8ኛና የ12 ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና መውሰድ አልቻሉም።

እስካሁን በ2017 ወደ ትምህርት ቤት የመጡ ተማሪዎች በጣም ጥቂቶች ናቸው።

ችግሩ ሳይቃለል በዚህ ዓመት ቢሮው 7 ሚሊዮን ተማሪዎችን ለማስተማር ቢያቅድም ከነሐሴ 20/2016 ዓ ም ጀምሮ ባደረገው ምዝገባ ግን እስካሁን የተመዘገቡት 2 ሚሊዮን አይሞሉም።

➡️ እድሜያቸው ከ4 እስከ 6 ዓመት የሆናቸውን 1 ሚሊዮን 760 ህፃናትን ለመመዝገብ ታቅዶ የተመዘገቡት 324 ሺህ ያክሉ ናቸው፡፡

➡️ ከ1ኛ ክፍል እስከ 8ኛ ክፍል 4 ሚሊዮን 800 ሺህ ተማሪዎች ይመዘገባሉ ቢባልም ባለፉት 20 ቀናት የተመዘገቡት ግን ከ1 ሚሊዮን 300 ሺህ አይበልጡም።

➡️ በሁለተኛ ደረጅ ትምህርት ቤት 1 ሚሊዮን 200 ሺህ ተማሪዎች ይመዘገባሉ ተብሎ የታቀደ ሲሆን ወደ ትምህርት ቤት የመጡት ግን 300 ሺህ ያክሉ ናቸው።

ተማሪዎች ለምን ወደ ትምህርት ቤት አልመጡም ?

ለአፈፃፀሙ ዝቅተኛ መሆን ፦
- በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ፣
- ተማሪዎች ዘግይቶ የመመዝገብ ልማድ፣
- ፖለቲካን ከትምህርት ጋር የማያያዝ ጉዳዮችና ሌሎች ምክንያቶች እንደሚጠቀሱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጠው ቃል አመልክቷል።

የክልሉ የትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ፥ " ልጆች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ፦
° የሀገር ሽማግሌዎች፣
° የሐይማኖት አባቶች፣
° ተፅዕኖ ፈጣሪዎች
° መንግስትና ኃላፊው
° በጫካ ያሉ ወንድሞች ጭምር ሊተባበሩ ይገባል " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ወላጆች በሰጡት ቃል የልጆች ወደ ትምህርት ቤት አለመሄድ እንዳሳሰባቸው እና ጉዳዩ ከባድ እንደሆነ ጠቁመዋል። በአንዳንድ የገጠሩ ክፍል " ትምህርት ቅንጦት እየሆነ ነው " ሲሉም ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

አማራ ክልል በብዙ ፈተና ውስጥ እያለፈ ያለ ክልል ቢሆንም በተለይ በብሔራዊ ፈተና በየዓመቱ እጅግ ምጡቅ ልጆች የሚወጡበትና ከፍተኛ ውጤት የሚመዘገብበት ነው። ለአብነት እንኳን ባለፈው ዓመት በብሔራዊ ፈተና ሁለተኛው የሀገሪቱ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በዚሁ ክልል ነው።

#Amhara #Education

@tikvahethiopia
" የተፈጸመው ወንጀል ጭካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ወንጀል ነው " - ፖሊስ

በጫጉላ ምሽት ሚስቱን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን የሃላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

ሟች ሪባቴ ትባላለች።

ሟች እና ወንድሟ በግድያ ተጠርጣሪው ግለሰብ አማካኝነች ቁርዓን እንደሚቀሩ ከሟች እህት አመደልሃዲ አንደበት ለመስማት ተችሏል።

ተጠርጣሪው ሟችን ማግባት እንደሚፈልግና ለሟች ወንድም በጓደኛው አማካኝነት ሃሳቡን ይገልጽለታል።

የሟች ወንድም አብዱልሃዲም ሟች እህቱን " ተስማምተሻል ወይ ? " በሚል መጠየቁንና ከሀፍረት መግለጽ ብትፈራም እንደተስማማች በመረዳቱ ወደ ጋብቻ ቅድመ ሁኔታው ማለፋቸውን ይገልጻል።

ከዚያም ወደ ጥሎሽና ኒካህ ተኪዷል።

ኒካህ ከታሰረ በኃላ ከለሊቱ 10 ሰዓት ገደማ ስልክ ተደወለልኝ የሚለው ወንድሟ " ሪባቴ ታማለች ና " ተብሎ ተነገረኝ ሲል ሁኔታውን አስታውሷል።

ወደ ቤታቸው ሲሄድ ግን ቤቱ በፖሊስ ተከቦ ነበር።

ሌላኛው የሟች ወንድም በርገና  " አባቴ ኒካህ እሰር ብሎ ከወከለኝ ቀን ጀምሮ ያለው ነገር ብቻ ነው ማውቀው ከዚያም ወንድሜን ወከልኩት ኒካሀው ታሰረ አለኝ ከዛ ለሊት 10 ሰዓት ስልክ ተደወለልኝ ቦታው ስንደርስ ቤቱ በፖሊስ ተከቧል " ሲል ገልጿል።

" በጭራሽ ያልገመትነው ነገር ሆኖ አገኘን " የሚለው የሟች ወንድም " ፖሊሶች እኛ ወደ አስክሬኑ እንዳንጠጋ አድርገው አስክሬኑን ወደ ሆስፒታል ወስደው እሱን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስዱት " በማለት አስረድቷል።

" ለሟች እህታችን ተገቢው ፍትህ ተሰጥቶን ተጠርጣሪው ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኝ እንፈልጋለን " ብሏል።

የሃላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ በበኩሉ ድርጊቱ ከተፈጸመበት ሰዓት አንስቶ ተጠርጣሪውን በህግ ጥላ ስር አውሎ 5 አባላት ያለው መርማሪ ቡድን በማዋቀር ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አመልክቷል።

የተፈጸመው ወንጀል " ጭካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ወንጀል ነው " ሲል ገልጿል።

ፖሊስ የተጠርጣሪውን የእምነት ክህደት ቃል እንደተቀበለና በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርመራው አልቆ  ውሳኔ እንዲያገኝ እንደሚሰራ አመልክቷታ።

የሃላባ ህዝብ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና መረጃ በመስጠት ላደረገው ርብርብ ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሀሩን ሚዲያ ነው። #HarunMedia

@tikvahethiopia
#USA

ዶላንድ ትራምፕ በቅርብ በሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉና ፕሬዜዳንት ከሆኑ ፥ " በአስቸኳይ የስደተኞችን ወረራ አስቆማለሁ፣ ማንኛውም አይነት የህገወጥ ስደተኞችን በረራ እንዲቆም እንዲሁም በማንኛውም መንገድ ወደ አሜሪካ ምድር እንዳይገቡ አደርጋለሁ " ብለዋል።

ከዚህ ባለፈ በስልጣን ዘመናቸው በአሜሪካ ታሪክ ትልቅ የተባለ ዲፖርቴሽን (ከሀገር የማስወጣት) ስራ እንደሚሰሩ ከወዲሁ ተናግረዋል።

" ከአሜሪካ ምድር ጓዛቸውን አስይዘን ወደ መጡበት እንልካቸዋለን " ያሏቸው ዶክመንት አልባ ህገወጥ ስደተኞችን ነው።

በስድተኞች ጉዳይ ላይ ያላቸው አቋም ከዚህ ቀደምም የሚታወቀው ትራምፕ አሁን ስመጣ " አጠነክረዋለሁ " እያሉ ለደጋፊዎቻቸው ቃል በመግባት ላይ ናቸው።

" ከተሞቻችን አድንላችኋለሁ " እያሉ ያሉት ትራምፕ ቢያንስ ቢያንስ ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን ህገወጥ ስደተኞችን ከአሜሪካ ለማስወጣት እቅድ አላቸው ተብሏል።

ምናልባትም ተመርጠው ፕሬዜዳንት ከሆኑ በኃላ ይሄን ሁሉ የሰው ቁጥር እንዴት ከአሜሪካ ዲፖርት እንደሚያደርጉ ለጊዜው በዝርዝር የሚታወቅ ነገር የለም።

#USA #deport

@tikvahethiopia
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የመስቀል በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኝ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡

እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉ፡፡

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!! ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
[Telegram] [Facebook]
                              
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ    
    የስኬትዎ አጋር!

https://www.tg-me.com/LionBankSC
#WELL_Computer

ለተማሪዎች እና ለሠራተኞች ታላቅ ቅናሽ !ጥሩ ላፕቶፕ ለመግዛት አሰበዋል? እንግዲያውስ 𝐖𝐄𝐋𝐋 ኮምፒውተር አለልዎት!

እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የ2023/24 ሞዴል ላፕቶፖች እና ኮምፒዩተሮችን ለጨረታም ሆነ ለግልዎ፣ የተለያዩ አዳዲስ ጌሚንግ እንዲሁም ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖችን ከአስተማማኝ ዋስትና ጋር እናቀርባለን።

አድራሻ፦ መገናኛ ከዘፍመሽ ዝቅ ብሎ 3ኤም ሲቲ ሞል / 3M City Mall 1ኛ ፎቅ ቁ. FL04 Well Computer

የሚፈልጉትን ላፕቶፕ ይምረጡ፦ https://www.tg-me.com/welllaptop የአንድ ዓመት ሙሉ ዋስትና
Call Us: @cr7_well
ስልክ ፦0943847549 / 0910238672
#Urgent🚨

በሊባኖስ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥሪ ቀርቧል።

በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤት በተለይ በደቡብ እና ምሥራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጥሪ አቅርቧል።

ጽ/ቤቱ በደቡብ እና ምሥራቅ ሊባኖስ ያለው የፀጥታ ችግር እየተባባሰ እንደመጣ አመልክቷል።

ይህን ተከትሎ በአካባቢዎች ያሉ ዜጎችን ለይቶ ማወቅ አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ጠቁሟል።

በአካባቢው የሚኖሩ ወገኖች ከታች በተቀመጠው መሠረት ፦

➡️ ስማቸውን ፓስፖርት ላይ እንደተፃፈው፣

➡️የፓስፖርት ቁጥር

➡️ ስልክ ቁጥራቸውን እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቅርቧል፡፡

° በደቡብ ሊባኖስ (ታየር ፣ ሱር ፣ ቢንት ጅቤል ፣ ማርጃዩን፣ ነበትዬ፣ ሳይዳ እና አካባቢው) የሚገኙ ወገኖች በስልክ ቁጥር 03-7354 51 ወይም 03-87-10-89

° በምሥራቅ ሊባኖስ (አልቤክ፣ ቤካ ሸለቆ እና አካባቢው) የሚገኙ ደግሞ በስልክ ቁጥር 81 77-62-51 ወይም 81-63-07-98 በመደወል እንዲመዘገቡ ጄኔራል ጽሕፈት ቤት አሳስቧል፡፡

#Share #ሼር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " እኔ ድርድር ያስፈልጋል በሰላም ይፈታ ስል ፤ እሱ ግን ' ከማን ጋር ነው የምንደራደረው ? ' ነበር ያለው " - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ፤ ጄነራል ጻድቃን ገ/ትንሳኤን ስልጣን ለመጠቅለል በማቀድና የቆየ ቂም ለመወጣት በሚል ከሰሱ። በደብረጽዮን (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ባሳለፍነው ሳምንት የመጨረሻ ቀናት መቐለን ጨምሮ በተለያዩ የትግራይ ከተሞች…
#Tigray
 
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፥ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራውን የህወሓት ቡድን አስጠነቀቁ።

ፕሬዜዳንቱ በማስጠንቀቂያቸው " ቡድን " ሲሉ የጠሩት ሃይል የወረዳና የከተማ የህዝብ ምክር ቤቶች ለመረበሽ እየሄደበት ያለው ርቀትና በማድረግ ላይ ያለውን እንቅስቃሴ ማቆም አለበት ብለዋል።

መስከረም 14/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንቱ ፊርማ ተፈርሞ ለሁሉም የወረዳና የከተማ ም/ቤቶች የተፃፈው የማስጠንቀቅያ ደብዳቤ " የህዝብ ምክር ቤቶች የትግራይ ጊዚያዊ መንግስትና የህዝቡ አካል እንጂ የህወሓት መዋቅር አለመሆናቸው አውቆ ' ቡድኑ ' የራሱ መሳሪያ ለማድረግ እያካሄደ ያለውን መሯሯጥና ውንብድና ማቆም አለበት " ይላል።

ስለሆነም ምክር ቤቶቹ የመንግስትና የህዝብ መዋቅር መሆናቸው በማመን ' ቡድኑ' ምክር ቤቶቹ በመጠቀም ያልደገፉትንና ሃሳቡ ያልተቀበሉት የመንግስት ሹመኞች ጥላሸት ለመቀባትና ከሃላፊነት ለማውረድ የሚያደርገው ጥረት መቆም አለበት ሲል አስጠንቅቋል።

ምክር ቤቶቹም ይህንን የመንግሰትና የፓለቲካ ድርጅት የሚቀላቅል ህገ-ወጥ ጣልቃ ገብነት ማውገዝ አለባቸው ብሏል።

" ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን ህግና ስርዓት ለማስከበር ሲባል ወደ ህጋዊ ተጠያቂነት መሸጋገር የግድ ይሆናል " በማለት አክለዋል።  

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ከቀናት በፊት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ  ያወጣውን የአቋም መግለጫ የሚቃወም መግለጫ  አውጥቷል።

በዶ/ር ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት መስከረም 14/2017 ዓ.ም ያወጣው  ባለ 4 ነጥብ የተቋውሞ መግለጫ ፤ " ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጊዚያዊ  ስራዎች ለመስራት መቋቋሙ ተዘንግቶ ከተቀመጠለት የቆይታ የጊዜ ሰሌዳ በላይ እንዲቆይና ራሱን ወደ ተሟላ የመንግስት ሃላፊነት  ለመለወጥ የሚያደርገው ጥረት ፀረ ዴሞክራሲና ኢ-ህገመንግስታዊ ነው " ብሏል።

ምንም እንኳን " ኢ-ህገመንግስታዊ " ብሎ ቢገልጽም የአገር ወይም የክልሉ ህገ-መንግስት አንቀፆችን አላጣቀሰም።

የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ቡድን " ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጠው ተልእኮ ወደ ጎን በመተው ህወሓት ለማፍረስ ፣ ሰራዊት ለማዘዝና የመንግስትና ህዝብ ሃብት በመጠቀም የትግራይ ህዝብ አንድነት ለመበተን እየሄደበት ያለውን የተሳሳተ መንገድ ሊያቆም ይገባል " ሲል አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
2024/09/27 07:31:12
Back to Top
HTML Embed Code: