Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮፌሰር በየነ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። ፕሮፌሰር በየነ ረዘም ላለ ጊዜ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውንም ጠቁመዋል። " በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ " ሲሉም ገልጸዋል።  @tikvahethiopia
#ProfessorBeyenePetros

" ከጠዋቱ 2 ሰዓት በጀግናው ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ የለቅሶ እና ሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ይከናወናል " - ሀድያ ዞን

የጉምቱው ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ስርዓተ ቀብር ነገ ይፈጸማል።

የፕሮፌሰሩ አስክሬን በህክምና ሲረዱ ከቆዩበት ኬንያ ናይሮቢ ትላንት ምሽት ነው አዲስ አበባ የገባው።

የቀብር ስርዓቱን ለማስፈጸም የተቋቋመ አብይ ኮሚቴ ሊኢብኮ በሰጠው ቃል ፤ የፕሮፌሰሩ ስርዓተ ቀብር በአዲስ አበባ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው እና የሙያ ባልደረቦቻቸው በተገኙበት እንደሚፈጸም አሳውቋል።

በሌላ በኩል በሀዲያ ዞን ሆሳዕና ነገ ሐሙስ ከጠዋቱ 2 ሰዓት በጀግናው ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ የለቅሶ እና ሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ይከናወናል።

መላው የዞኑ ነዋሪ ሕዝብ  በተገለፀው ሰዓት እና ቦታ በመገኘት በፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ሀዘን እንዲገልጽ ጥሪ ቀርቧል።

ፕሮፌሰር በየነ ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ዕንቁ ምሁራን መካከል ከቀዳሚቹ ተርታ ይጠቀሳሉ። ከዚህ ባለፈ በሀገሪቱ የፖለቲካ ውስጥ የሰላማዊ ትግል ተምሳሌት ነበሩ፡፡

ነፍስ ይማር !

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ጉቦ በመቀበል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ሰራተኞች ፍርድ ቤት ቀረቡ።

ሰራተኞቹ የግብር መጠንን በመቀነስ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ጉቦ በመቀበል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የአዲስ አበባ ፖሊስ መርማሪ ያቀረበውን የጥርጣሬ መነሻንና የተጠርጣሪ ጠበቃ መከራከሪያ ነጥቦችን ተመልክቷል።

ችሎት ቀርበው ጉዳያቸው የታዩት ተጠርጣሪዎች ፦

የአ/አ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ ሃብታሙ ግዲሳ፣

የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ስምረት ገ/እግዚአብሔር፣

የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ዮሴፍ ባቡ፣

የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር አቤኔዘር ቶሎሳ፣

ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር ለሚ ሲሌ

ገንዘብ ተቀባይ ባለሙያ ወ/ሮ መቅደስ አረጋዊ ናቸው።

ተጠርጣሪዎቹ የተሰጣቸውን የስራ ኃላፊነትን ወደ ጎን በመተው ከግብር ከፋይ ግለሰቦች ጋር በጥቅም በመመሳጠር ከግብር ከፋይ ድርጅቶች " ግብር እንቀንስላችኋለን " በማለት በመደራደር ከ100 ሚሊየን ብር የግብር መጠንን ወደ 13 ሚሊየን ብር ዝቅ በማድረግ ግብርን በመቀነስ ከተለያዩ ድርጅቶች በተለያዩ መጠኖች ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ጉቦ ተቀብለዋል በማለት መርማሪ ፖሊስ የጥርጣሬ መነሻውን ለጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ አቅርቧል።

መርማሪ ፖሊስ በባንክ ሂሳባቸው የጉቦ ገንዘብ ገቢ የተደረገላቸው ተጠርጣሪዎች መኖራቸውን የሚያሳይ ማስረጃ መሰብሰቡን በማመላከት ተጨማሪ ግብረ አበር ለመያዝና ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ማስረጃዎች አሰባስቦ ለመቅረብ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ በበኩሏ ደንበኞቿ በመርማሪ ፖሊስ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት " አልፈጸሙም " በማለት በመከራከር የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቃለች።

መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢወጡ ማስረጃ ሊያሸሹ ይችላሉ በማለት በጠበቃቸው የቀረበውን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ እንዲደረግ በመጠየቅ ተከራክሯል።

የፖሊስ የጥርጣሬ መነሻን እና ግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ የምርመራ መዝገቡ ጅምር በመሆኑ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ለፖሊስ መስጠት አስፈላጊ መሆኑን በማመን የተጠርጣሪ የዋስትና ጥያቄን በማለፍ ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።

መረጃው የኤፍ ቢ ሲ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

ከፖሊስ የተገኘ መረጃ  ፦

በአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የታክስ ኦዲት ቡድን አስተባባሪ እና ባለሙያዎች የሆኑት ፦
- አቶ ሃብታሙ ግዲሳ
- ስምረት ገ/እግዚአብሔር (የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- አቶ ዮሴፍ ባቡ (የከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- አቶ አቤኔዘር ቶሎሳ (የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- አቶ ለሚ ሲሌ (ከፍተኛ ግብር ከፋይ የታክስ ኦዲት ከፍተኛ ኦፊሰር)
- ወ/ሮ መቅደስ አረጋዊ (ገንዘብ ተቀባይ)

ጳጉሜ 05/2016 ዓ.ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ውስጥ ግብር ከፋይ የሆኑ ግለሰብ የ2011 ዓ.ም እና 2012 ዓ.ም የአንድ አመት ግብር ኦዲት እንዲደረግላቸዉ የሚጠበቅበትን ሰነድ ያቀረበላቸዋል።

መክፈል ያለብህ 100,000,000 ብር ነዉ ይሉታል።

ይህን ያህል " አልከፍልም ካልክ ግማሹን አስይዘህ ነዉ ይግባኝ የምታቀርበዉ " በማለት ይገልጹለታል።

ለጊዜዉ በቁጥጥር ስር ያልዋለ ግለሰብ ሂሳብ አስጨራሽ በሚል የቀረ ደላላ ጉዳዩን አስተካክላለሁ በሚል በማግባባት ለራሱ 3,000,000 ብር እና ለሰራተኞቹ ስምንት 8,000,000 ብር ለመንግስት ከመቶ ሚሊየን በመቀነስ " 13,000,000 ብር ትከፍላለህ " በማለት ያስማማሉ።

በዚህም 8,000,000 ብር #በቤተሰቦቻቸዉ አማካኝነት በመቀበል 13,000,000 ብር የመንግስት የሚከፈለዉን እንዲከፍል መተማመኛ ሲሰጡት በተደረገ ክትትል እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

ግለሰቦቹ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

ለፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዷል።

@tikvahethiopia
#AAU

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎች በውድድር ነጻ የትምህርት እድል (ሶኮላርሺፕ) ሊሰጥ እንደሆነ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን የመጀመርያው ራስገዝ ዩኒቨርሲቲ እንዲሆን ተወስኖ ተማሪዎችን በራሱ የቅበላ ስርዓት ተቀብሎ ለማስተማር ምዝገባ እያከናወነ ነው።

ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ ያዘጋጀውን የተማሪዎች መግቢያ ፈተና ይሰጣል። በዚህም ብቃትን፣ ብዝሃነትንና ፍትሐዊነትን ማዕከል አድርጎ ተማሪዎችን እንደሚቀበል ገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ላስመዘገቡ 200 ተማሪዎችን በውድድር ነፃ የትምህርት እድል ከዶርሚታሪና የካፌ አገልግሎት ጋር እንደሚሰጥ አሳውቋል።

አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ " ብቃትና ተሰጥዖ ያላቸው ተማሪዎች መዳረሻ ለመሆን ያለኝን ቁርጠኝነት እገልጻለሁ " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AAU ራስ ገዙ አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል በመጀመሪያ ዲግሪ በ2017 ዓ/ም መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ያቀረበው ጥሪ ነገ ያበቃል። በ2017 ዓ/ም በቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ ግብር በትምህርት ሚኒስቴር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  የተማሪዎች ምደባ እንደማይኖር  ይታወቃል። በመንግስት ስኮላርሺፕ እንዲሁም በግል ከፍለው በዩኒቨርሲቲው…
ተማሪዎች እስከ መቼ ማመልከት ይችላሉ ?

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው መረጃ የማመልከቻው ቀን ከዚህ ቀደም በነበረው ማስታወቂያ ዛሬ መስከረም 08/2017 እንደሚያበቃ ቢገለጽም እስከ ነገ መስከረም 09/2017 ድረስ መራዘሙን አስታውቋል።

በዚህም በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጾች ፦
➡️
www.aau.edu.et
➡️
https://portal.aau.edu.et ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር የማመልከቻ መስፈርቶች በማሟላት መመዝገብ የሚችሉ መሆኑን ገልጿል።

#ማስታወሻ ፦ ለነፃ የትምህርት እድል ( #ስኮላርሺፕ ) የሚመዘገቡ የተለየ መመዝገቢያ አለመኖሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጸው ዩኒቨርሲቲው ከላይ በተጠቀሰው የመመዝገቢያ አማራጭ ብቻ እንዲያመለክቱ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#SafaricomEthiopia

በSMS ጨዋታችን ስልክ መሸለማችንን ቀጥለናል! 🎊 ሌሎችም  ከ2ሺህ በላይ አሸናፊዎች በየቀኑ በሽ በሽ እያሉ ነው!

አሁንም በSMS ጨዋታ ፈታ💬🎊 እያልን በየቀኑ እንሸለም! 🎁 ከሳፋሪኮም ቁጥራችን 'START’ ብለን ወደ 34000 ወይም *799# በመላክ እንወዳደር! እናሸንፍ! በአንድ መልስ 1ብር ብቻ!

በሽልማት በሽ በሽ እያልን ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት ⚡️ 🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.
mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የነዋሪዎችድምጽ • “ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚተገበረው ግን መቼ ነው ? ” - የቡለን ወረዳ ነዋሪዎች • “ ‘ለምን አልመርጣችሁኝም ’ በማለት በበቀል ህዝብን መጉዳት ተገቢ አይደለም ” - ዶ/ር መብራቱ አለሙ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ‘ ለምን ፓርቲውን መረጣችሁ ’ በሚል ሰበብ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት እና ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ…
" ከምርጫ ወዲህ ከፍተኛ ጫና እየደረሰብን ነው " - ቦሮ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚንቀሳቀሰው የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የፖለቲካ ድርጅት ሰኔ 16 ቀን፣ 2016 ዓ.ም በክልል ምርጫ ከተካሄደ ወዲህ በፓርቲው ላይ ከፍተኛ ጫና እንደደሰበት እንደሚገኝ አሳውቋል።

ፓርቲው ምን አለ ?

- መተከል ዞን 3 ለክልል ምክርቤት እና አንድ የህዝብ ተወካዩች ምክርት ቤት ወንበር ማግኘት ችለናል።

- በቡሌን ወረዳ " ተቃዋሚ ፓርቲ መርጣቹሀል " ተብሎ የፓርቲው ደጋፊዎች ፣ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች ላይ ዛቻ እና ማስራርያ እየደረሰ ይገኛል። የፓርቲ አባላትም ለእስር እየተዳረጉ ይገኛሉ።

- የተቀናጀ ወከባና ዛቻ ነው የሚደርሰው። በተለይ ከምርጫው ውጤት በኃላ።

- ቡሌን ወረዳ ላይ አባላት በተለያዩ ወቅቶች ይታሰራሉ። ከልዩ ልዩ የፖለቲካ እና ማህበራዊ ተሳትፎ ተከልክለዋል። በንግድ፣በግብርና እንዲሁም በመንግስት ስራ ላይ የተሰማሩ የፓርቲው ደጋፊዎች ላይ " ተፎካካሪ ፓርቲ ደግፋቹሀል፣ መርጣቹሀል " በሚል ማስፈራሪያና ዛቻ ይደርሳል።

- የፓርቲውን አባላት መብት በመንፈግ የፖለቲካ አመለካትን መሰረት ያደረገ ጫናዎች እየደረሱ ነው።

- በፓርቲው ላይ የደረሱ የመብት ጥሰቶችን የሰብአዊ መብት ተቋማት ሊከታተሉት ይገባል።

የቡሌን ወረዳ ፖሊስ ለቀረበው ክስ ምን ምላሽ ሰጠ ?

የፖሊስ ፅ/ቤት አዛዥ ዋና ኢንስፔክተር ብርሀኑ ኤጄታ ፦

" በወረዳው በፖለቲካ አመለካከቱ የታሰረ ሆነ በደል የደረሰበት ግሰለብም ሆነ ቡድን የለም።

በአካባቢው የፖለቲካ ድርጅቶች ሰላማዊ በሆነ መንገድ በምርጫ ተሳትፈዋል።

ፓርቲው ያቀረበው ቅሬታ ተቀባይነት የሌለው ክስ ነው። " #ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ProfessorBeyenePetros " ከጠዋቱ 2 ሰዓት በጀግናው ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ አደባባይ የለቅሶ እና ሻማ ማብራት ስነ-ስርዓት ይከናወናል " - ሀድያ ዞን የጉምቱው ፖለቲከኛ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ስርዓተ ቀብር ነገ ይፈጸማል። የፕሮፌሰሩ አስክሬን በህክምና ሲረዱ ከቆዩበት ኬንያ ናይሮቢ ትላንት ምሽት ነው አዲስ አበባ የገባው። የቀብር ስርዓቱን ለማስፈጸም የተቋቋመ አብይ ኮሚቴ ሊኢብኮ…
የፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የቀብር ስነ ስርዓት ነገ መስከረም 9 ይፈፀማል።

ነገ ከጠዋቱ 3 ሰዓት  ሳሪስ አደይ አበባ ከሚገኘው የመኖሪያ ቤታቸው ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ አሸኛኘት ይደረጋል።

ከአራት ሰዓት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ የተለያዩ ስነስርዓቶች ይካሄዳሉ።

የቀብር ስርዓታቸው ከቀኑ 8 ሰዓት በአዲስ አበባ ብርሐናተ ዓለም ጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ይፈጸማል።

መረጃው የሀድያ ቴሌቪዥን ነው።

(መስከረም 8/2017 ዓ/ም)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

° “ ልጆቻችን ችግር ላይ ናቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕይወታቸው ይድረስልን ” - በማይናማር ያሉ ኢትዮጵያን ቤተሰቦች

° “ የእኛ ኤምባሲ ከዛ አገር መንግስት ጋር እየተነጋገረ ልጆች የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሞከረ ነው ” - የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጭ (ባለሥልጣን)

በማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፦
➡️ ከአገር ሲወጡ በተዋዋሉት መሠረት ሳይሆን በተቃራኒው ህገወጥ የማጭበርበር ተግባር ላይ እንዲሰማሩ እንደተገደዱ፣
➡️ በአግባቡ ደመወዝ እንደማይከፈላቸው፣
➡️ ይባስ ብሎ ድብደባ እየተፈጸመባቸው አካላቸው እስከመጉደል እንደደረሱ በቤተሰቦቻቸው ጭምር በቲክቫህ ኢትዮጵካ በኩል መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ስለጉዳዩ ምላሽ የጠየቅናቸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ “ መረጃው ትክክል ነው፡፡ ዜጎች ችግር ላይ ናቸው ተቋሙም ኃላፊነት ወስዶ ለወገኖቻችን ለመድረስ ጥረት እያደረገ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥተውን ነበር፡፡

በማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አሁንስ ቤተሰቦች ምን አሉ ?

“ ልጆቻችን ችግር ላይ ናቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በሕይወታቸው ይድረስልን፡፡ ትንሽ ክፍተት አግኝተው ደውለው ሲነግሩን የከፋ ችግር ውስጥ እንደሆኑ ነው የሚያስረዱን፡፡ ተጨነቅን እኮ!

በእርግጥ የኢትዮጵያ መንግስት ጥረት እያደረገ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ ግን ልጆቻችን በዬቀኑ ድብደባና እንግልቱ እየከበደባቸው ነውና መንግስት በቻለው መጠን ተነጋግሮ ወደ አገራቸው እንዲገቡ እንድያደርግልን እንማጸናለን፡፡

መንግስትንም ለማጣደፍ የተገደድነው የወላጅ አንጀት አልችል ቢለን ነው፡፡ ልጆች በባዕድ አገር በእንዲህ አይነት የከፋ ችግር ውስጥ ሆነው ማየት ሀዘኑ መራራ እንደሆነ የወለደ ሁሉ ያውቀዋል ” ብለዋል።

በችግር ላሉት ኢትዮጵያዊያን ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉና ጉዳዩን ከጅምሩ ጀምሮ የሚያውቁት ባለሥልጣን በበኩላቸው ተከታዩን ምላሽ ሰጥተውናል፡፡

“ ኢትዮጵያ እንደ አገር እዛ አካባቢ ካሉ አገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነት የላትም፡፡ ስለዚህ ልጆቹ በግላቸው ነው የሄዱት፡፡ ማንኛውም ሰው ለሥራ የመንቀሳቀስ መብት አለው፡፡ ከዛ አኳያ ሂደዋል፡፡

ነገር ግን ዜጎች ችግር ላይ ሲወድቁ መንግስት ዝም ብሎ ስለማይመለከት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን ከሰማ ጀምሮ እየሰራ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያኑ የሚሄዱት በታይላንድ በኩል ነው፡፡ ጉዳዩን የሚከታተሉት ህንድና ጃፓን ያሉት የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ናቸው፡፡

ከዚህ ቀደም ታይላንድ ላይ ታግተው የነበሩ ኢትዮጵያዊያንን ማስመለስ ተችሏል፡፡ እኛም የሥራ ስምሪት ወደ እዛ አገር ስለሌለ ዜጎች ወደዛ ባይሄዱ ይመረጣል የሚል መልዕክት ሰጥተናል፡፡

መሄዳቸው ልክ አይደለም ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትም መውሰድ መቻል አለባቸው፡፡ ችግር ሲያጋጥም ብቻ መንግስት ላይ መጮህ ተገቢ አይደለም፡፡

ግን እዛ አካባቢ ተቸግረው የነበሩ ልጆችን መንግስት አስመልሷል፡፡ ነገር ግን ወደ ማይናማር የተሻገሩ አሉ፡፡ ወደ ማይናማር የተሻገሩት የሄዱበት ቦታ አስቸጋሪና ታጣቂዎች ያሉበት ቦታ ነው፡፡ የእኛ ኤምባሲ ከዛ አገር መንግስት ጋር እየተነጋገረ ልጆች የሚመለሱበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እየተሞከረ ነው። ” ብለዋል፡፡

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ከሰጡን ማብራሪያ በተጨማሪ፣ “ በተለይ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ፣ ወደ ደቡብ አፍሪካ መስመር ነበር የተለመዱት፡፡ አሁን ደግሞ ባልተለመደ ሁኔታ በጣም አዲስ ነገር ነው ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

“ ሕገ ወጥ ሰዎች ዝውውር በተለይ በደላሎች አማካኝነት ለአደጋ የሚያጋልጥ እንደሆነ ማንኛውም ዜጋ በተለይ ወደ ውጭ አገር ሲንቀሳቀሱ መጠየቅ፣ ማጣራት ያስፈልጋል ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የሆነው ሆኖ ግን ውጪ ጉዳይ ኢትዮጵያዊያኑ ካሉበት ችግር እንዲወጡ እየሰራ መሆኑን አመላክቷል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia 📣 ሰምተዋል ℹ️

ለእረፍት ቀንዎ ልዩ ነገር ይዘን መጥተናል 🥁🔥

የፊታችን ቅዳሜ መስከረም 11 እና እሁድ መስከረም 12 ቀን የሚደረጉትን አስሩንም የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዋች ፥ ማን ሲቲ ከ አርሰናል ጨምሮ ሌሎች አጓጊ ጨዋታዎችን በጎጆ ፓኬጆች ከ350 ብር ብቻ በቀጥታ መመልከት ይችላሉ።

ይህ ልዩ አጋጣሚ አያምልጥዎ! ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!

#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
Hey Mobile !

Tab A9 - 19,500 ETB
•Tab A8 - 29,500 ETB
•Tab A9+ 5G - 31,000 ETB
•Tab S6 Lite - 47,000 ETB
•Tab S9 FE - 59,000 ETB
•Tab S9 +5G - 99,000 ETB
•Tab S9 Ultra - 129,000 ETB

Contact us :
0936222222 @heymobile1
0925927457 @eBRO4

@Heyonlinemarket
#ኢትዮ130

ኢትዮ ቴሌኮም በአዲሱ አመት በነበረው የደንበኞች ጨዋታ በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ ደንበኞቹን መሸለሙን ይህም በእጅጉ አዳዲስ ደንበኞችን ለማግኘት ያገዘው እንደሆነ ገልጿል።

ኩባንያው ከተመሰረተ 130 ዓመታትን ማስቆጠሩን አስመልክቶ በተያዘው ዓመት ለስድስት ወር የሚቆይ "ኢትዮ 130" የተሰኘ ጨዋታ በተመሳሳይ ለደንበኞቹ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።

ኩባንያው በስራቴጂው የመጨረሻ ዓመት ሊያከናውናቸው ባቀዳቸው ተግባሮች ዙሪያ በዛሬው ዕለት ተቋሙ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

በዚህም፥ በ2016 በጀት ዓመት የተገኘውን 93 ቢሊየን ብር ገቢ በ74.7% በማሳደግ 163.7 ቢሊዮን ብር ለማድረስ እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት መጠንንም ወደ 282.85 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ለማሳደግ አቅዷል።

በተጨማሪም፦

- የደንበኞችን ብዛትንም በ6% በመጨመር 83 ሚሊዮን ለማድረስ፤

- የሞባይል ደንበኞችን በ5.5% በመጨመር 79.7 ሚሊዮን ለማድረስ፤

- የሞባይል ዳታና ኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን በ16% በመጨመር 47.4 ሚሊዮን ለማድረስ፤

- የፊክስድ ብሮድባንድ ደንበኞችን በ25% በመጨመር 934 ሺህ በማድረስ አጠቃላይ የቴሌኮም ስርጸት መጠንን 73% ለማድረስ ታቅዷል፡፡ 

- 1,298 አዲስ የሞባይል ጣቢያዎችን ለመገንባት፤ 500 ተጨማሪ ከተሞችን የ4ጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግና 15 ተጨማሪ ከተሞችን የ5ጂ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ማቀዱንም ነው የገለጸው።

ኢትዮ ቴሌኮም “ሊድ” የተሰኘ የሦስት ዓመት ስትራቴጂውን በ2015 በጀት ዓመት ማስተዋወቁ ይታወሳል። አዲሱ የ2017 በጀት አመት የስትራቴጂ ዘመኑ ሶስተኛው አመቱ ይሆናል።

ተጨማሪ ያንብቡ https://telegra.ph/Ethio130-09-19

@tikvahethiopia
2024/09/29 22:24:51
Back to Top
HTML Embed Code: