Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

ሁሉም የፓለቲካ ፓርቲዎች በእኩል የሚያሳትፍ በምክር ቤት የሚመራ ሲቪል ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም አራት የትግራይ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጠየቁ።

የጋራ መግለጫውን ያወጡት ፦
- ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ፣
- ባይቶና ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፣
- ውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት)
- ዓረና ንሉኣላውነትን ዴሞክራስን  (ዓረና)  ናቸው።

ፓርቲዎቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ ፤ " በትግራይ ያጋጠመው ችግር መነሻው ፓለቲካዊ ውድቀት ስለሆነ ከውድቀቱ ለመውጣት አካታች ፓለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልጋል " ብለዋል።

" ችግሩ የሚፈታው አንድ የፓለቲካ ፓርቲ በሚያራምደው የበላይነት አመራር ሳይሆን ሁሉም አቀፍ በሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ለዚህም ሁሉም የፓለቲካ ሃይሎች በእኩል የሚሳተፉበት በምክር ቤት የሚመራ ስቪል ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋም እንደ አንድ የችግር መፍቻ አስቀምጠዋል።

ፓርቲዎቹ በአሁኑ ወቅት በሁለት የህወሓት ሃይሎች የተፈጠረው ፓለቲካዊ መሳሳብ ወደ ጎን በመተው ወጣቶች ፣ ሴቶች ፣ የዳያስፓራ ማህበረሰብ መላው የትግራይ ህዝብ ዓላማቸው ደግፎ ከጎናቸው ሆኖ እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። 

" የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ከማንኛውም የፓለቲካ ሃይል ውግንና ነፃ በመሆን የሲቪል መንግስትና ህግ በመመራት ለህዝብና አገር ጥቅም መቆም አለባቸው " ሲሉ አሳስበዋል። 

በቅርቡ የሚፈፀሙት ተጨማሪ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ፣ ግዛታዊ አንድነት የማስመለስ ፣ ታጣቃዎች ትጥቅ የማስፈታትና ወደ ህብረተሰቡ የመቀላቀልና ሌሎች በትግራይ በኩል የሚፈፀሙ ስምምነቶችና ውሎች ለህዝብና ጉዳዩ  ለሚመለከታቸው አካላት ግልፅና ይፋ እንዲደረግም ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ክስ ተመሰረተባቸው። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ? - አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ - የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል…
#Update

የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።

ግለሰቦቹ ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።

ዐቃቤ ህግ በ6ቱ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

የቀረበባቸው ክስ ለተከሳሾች ከደረሰ በኋላ በተከሳሾች ጠበቆች በኩል ደንበኞቻቸው " የተከሰሱበት ድንጋጌ በመርህ ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል አይችልም " በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ፤ የወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 67/ለ ጠቅሶ በልዩ ሁኔታ ዋስትና ሊያስከለክል ስለሚችል በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው ማለትም ፦
➡️ ከወንጀሉ ከባድነትና ከክሱ ተደራራቢነት፣
➡️ ከጉዳዩ ባህሪና ከከባቢያዊ ሁኔታዎች አንጻር ዋስትና ሊያስከለክሉ የሚችሉበትን ትርጉም የተሰጠባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥሮችን ጠቅሶ የዋስትና መብታቸው እንዲታለፍ ጠይቆ ነበር።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት ብይን ሰጥቶበታል።

በዚህም ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም በማለት የጠየቁት የዋስትና ጥያቄን ውድቅ ተደርጎ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል።

ክሱን ለመመልከትም ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#MesiratEthiopia

🌟 በቅርቡ መውሰድ ያለባችሁ ስልጠናዎች 🌟
የግል በጀት አወጣጥ መሠረታዊ ነገሮች (Basics of Personal Budgeting) 👇
📅 መስከረም 10, 2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት
🔗 Register Here: https://forms.gle/t2KczdEpPrNstvjz5

መሠረታዊ መብቶች (Fundamental Rights) 👇
📅 መስከረም 15, 2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት
🔗 Register Here: https://forms.gle/Vk2Yd44t8Cnba6Jm6

የንድፍ አስተሳሰብ (Design Thinking) 👇
📅 መስከረም 20, 2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት
🔗 Register Here: https://forms.gle/6aurE6Q8nAZQdNz18
ይህ አጋጣሚ እንዳያመልጥዎ!
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት🚨 ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል። " ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል። ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች…
🔈 #የነዋሪዎችድምፅ

በመስቃንና ማረቆ እየሆነ ያለው ምንድን ነው ?

በማረቆ እና መስቃን መካከል ለዓመታት በሚስተዋለው ግጭት ግድያና መፈናቀል ሊቆም እንዳልቻለ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

አሁንም ከፍተኛ የሆነ የበቀል ሥሜት ስላለ ሥጋት እንዳለባቸው ገልጸው፣ የሚመለከታቸው ባለድረሻ አካላት ለጉዳዩ እልባት እንዲሰጡት ጠይቀዋል፡፡

የማረቆ ልዩ ወረዳ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

“ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በምሽት ንፁሃንን ይገድላሉ። ከሳምንት በፊትም ግድያ ነበር። በጣም ግራ የሚያጋባ ወቅት ነው፡፡

መገደሉ፣ መፈናቀሉ እየተለመደ መጣ፡፡ ምን እናድርግ ?

ነገሩ ለረጅም ጊዜ ትክክለኛ መፍትሄ ሳያገኝ የግጭት ቀጠና በመሆኑ ጉዳዩ እያሳሰበው ግማሹ የአይምሮ እና ለተለያዩ የህመም አይነቶች እየተዳረገ ይገኛል፡፡

የችግሩ ምንጭ የማረቆ ህዝብ የጠየቀው የ9 ቀበሌ የማካለል ጉዳይ ነው፡፡

ጥያቄው ለብዙ አመታት ሲሆን፣ በዚህ ረጅም ዓመት በህግ አግባብ ከክልል ምክር ቤት እስከ ፌደሬሽን ሲጠየቅ ቆይቷል፡፡

ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ግን ከአምስት ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡

ለዚህ ግጭት ዋና ተጠያቂ ተብለው የሚወሰዱት ከጉራጌ ዞን እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮችና የጸጥታ አካላት ናቸው።

በምሽት በሀሰተኛ ጥቆማና ጥርጣሬ ወጣቱን እያሳደዱት ስለሆነ ነገሩ ትኩረት ያስፈልገዋል ” ብለዋል፡፡

የምሥራቅ መስቃን ነዋሪዎች በበኩላቸው ፥ ከማረቆ ተፈናቅለው ወደ መስቃን የመጡ ወገኖች እንዳሉ ገልጸው፣ ችግሩ ያለው ሰላም ከማይፈልጉ ኃላፊነት ላይ ያሉ አካላት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

ግድያም በተለያየ ጊዜ እንደሚፈጸም ጠቁመዋል።

“ በማረቆ ተወላጆች ከስምንት በላይ ቀበሌዎች ተወስደውብናል ” የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ ለዚህ ድርጊትም ኃላፊነት ላይ ያሉ አካላትን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡

አንድ ስለጉዳዩ ያጫወቱን በምሥራቅ መስቃን የሚገኙ የእድሜ ባለጸጋ፣ “ ሁለቱ ብሔረሰቦች ተስማምተው መኖር እንዳይችሉ እያደረጉ ያሉት የፖለቲካ ትርፍ የሚፈልጉ አካላት ናቸው ” ብለዋል፡፡

በሁለቱ ወረዳዎች መካከል የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር የተከሰተው በ2010 ዓ/ም ሲሆን፣ በ2014 ዓ/ም እርቀ ሰላም እንዲወርድ ተደርጎ ነበር፡፡

ይሁን እንጅ ከእርቀ ሰላሙ ወዲህም ችግር አገርሽቶ በየጊዜው ሞትና መፈናቀሉ ሊቆም አልቻለም፡፡

የሚመለከታቸው አካላት ምን እየሰሩ እንደሆነ ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው አልተሳካም፡፡ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዕለታዊ ዛሬ ንግድ ባንክ የዶላር መግዣ ላይ ጭማሪ በማድረግ ወደ 108 ብር ከ0728 ሳንቲም አስገብቷል። መሸጫው 119 ብር ከ9608 ሳንቲም ነው። በአቢሲኒያ ባንክ አንዱ ዶላር 108 ብር ከ0729 ሳንቲም መግዣ ፤ 121 ብር ከ0416 ሳንቲም መሸጫ ተቆርጦላታል። በወጋገን ባንክ የዶላር መግዣው 115 ብር ከ0121 ሳንቲም ነው። አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ደግሞ አንዱን የአሜሪካ ዶላር በ107…
#ዶላር

የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ አሳይቷል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ7 ቀናት ጭማሪ ያልታየበት ወጥ የምንዛሬ ዋጋ ነበር።

ባንኩ ዛሬ ሲያገበያይበት የነበረው የምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ የታየበት ነበር።

አንዱ የአሜሪካ ዶላር መግዣው ወደ 112 ብር ከ3957 ሳንቲም ደርሷል።

የመጫው ዋጋም 124 ብር ከ7592 ሳንቲም ገብቷል።

በፓውንድ ላይም ጭማሪ ተመዝግቧል።

አንዱ ፓውንድ መግዣው 141 ብር ከ6314 ሳንቲም ተቆርጦለት ውሏል። መሸጫው 157 ብር ከ9487 ሳንቲም ነበር።

ዩሮ መግዣው 125 ብር ከ0177 ሳንቲም መሸጫው 138 ብር ከ7697 ሳንቲም ሆኖ ውሏል።

የUAE ድርሃም መግዣው 30 ብር ከ6030 ሳንቲም መሸጫው 33 ብር ከ9693 ሳንቲም ገብቷል።

#Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የመመዝገቢያ ቀናት ከጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም - መስከረም 8/2017 ዓ.ም ድረስ ነው " - የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋዉ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2017 ዓ /ም  ለቅድመ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች ለመቀበል መዘጋጀቱን አሳውቆናል። ዩኒቨርሲቲው ለ2017 ቅድመ ምረቃ ትምህርት በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል ከፍለዉ ለሚማሩ እንዲሁም በማታ በተከታታይ መርሃ ግብር…
#AAU

ራስ ገዙ አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል በመጀመሪያ ዲግሪ በ2017 ዓ/ም መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ያቀረበው ጥሪ ነገ ያበቃል።

በ2017 ዓ/ም በቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ ግብር በትምህርት ሚኒስቴር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  የተማሪዎች ምደባ እንደማይኖር  ይታወቃል።

በመንግስት ስኮላርሺፕ እንዲሁም በግል ከፍለው በዩኒቨርሲቲው መማር ለሚፈልጉ በሙሉ የአ.አ.ዩ  የሚያወጣውን የመግቢያ ፈተና (UAT) እንዲሁም ሌሎች መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

በዚህም መሠረት በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጾች ፦
➡️ www.aau.edu.et
➡️ https://portal.aau.edu.et ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር የማመልከቻ መስፈርቶች በማሟላት መመዝገብ ይችላሉ።

የመመዝገቢያ ቀኑ ነገ መስከረም 8/ 2017 ዓ.ም ያበቃል።

የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀናት ወደፊት ይገለጻል።

በመንግስት ስኮላርሽፕ ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመማር የሚያያዘው ማስረጃ ምንድነው ?

በቀን መደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሽፕ ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለማመልከት ከተጠየቁት መስፈርቶች አንዱ የቤተሰብ የገቢ መጠንን የሚገልፅ ማስረጃ ማያያዝ ነው።

በዚህ መሰረት ፦

1. ከወረዳ/ቀበሌ ወይም መስሪያ ቤት ስለገቢያቸዉ ዝቅተኛነት የሚገልፅ ማስረጃ ከሚመለከተዉ ከወረዳ ወይም ቀበሌ ወይም መስሪያ ቤት ዘርፍ ኃላፊ ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

2. የቤተሰቡ ኃላፊ ጡረታ ላይ የሚገኙ መሆናቸዉን የሚገልፅ ደብዳቤ ወይም የታደሰ የጡረተኝነት መታወቂያ ወይም የባንክ ደብተር ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

https://www.tg-me.com/TikvahUniversity/12317

(Addis Ababa University)

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በሀሰተኛ የብር ኖት ግብይት የፈፀሙ 2 ተጠርጣሪዎች እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ ገብርኤል አካባቢ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12፡ 30 ሰዓት ላይ ነው።

ግለሰቦቹ ከአንድ ሸቀጣ ሸቀጥ መሸጫ እና ዘይት አከፋፋይ ከሆነ ሱቅ ውስጥ በርከት ያለ ባለ 20 ሊትር ዘይት ለመግዛት ተስማምተው ያስጭናሉ።

በኋላም ሒሳብ ሲከፍሉ ገንዘቡ ከባንክ እንደወጣና ህጋዊ ለማስመሰል አሽገው 42 ሺህ 350 ብር ለነጋዴው ይከፍሉታል፡፡

ሆኖም የግል ተበዳይ ገንዘቡ ሀሰተኛ መሆኑን ተጠራጥሮ በአካባቢ ነዋሪዎች ትብብር እንዲያዙ አድርጓል።

ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይ መጠራጠሩን ሲረዱ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 30791 ተሽከርካሪ በመጠቀም ለማምለጥ ቢሞክሩም በአካባቢው በነበሩ ሰዎች ሊያዙ ችለዋል።

ግብይት ሊፈፅሙበት ከነበረ 42 ሺህ 3 መቶ 50 ብር ውስጥ 39 ሺህ 4 መቶ ሃሰተኛ ብር እጅ ከፍንጅ ተይዘው ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy,
@CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com
Online Live class - Cisco CCNA Professional Networking Course Training & Certification Preparation.

Registration Date: August 19 to October 04, 2024
Class start date: October 05, 2024.

Course Recognitions: CCNA trainees will receive 3 Certificate of Completion, 3 Letter of Merit, 3 Digital Badge that recognized and accepted in USA, Canada, and Europe, and you will award 58% CCNA certification exam discount voucher.

Mobile #: 0902-340070/ 0935-602563/ 0945-039478
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
Hey Mobile !

Tab A9 - 19,500 ETB
•Tab A8 - 29,500 ETB
•Tab A9+ 5G - 31,000 ETB
•Tab S6 Lite - 47,000 ETB
•Tab S9 FE - 59,000 ETB
•Tab S9 +5G - 99,000 ETB
•Tab S9 Ultra - 129,000 ETB

Contact us :
0936222222 @heymobile1
0925927457 @eBRO4

@Heyonlinemarket
" በጣም አስቸጋሪ የሚባለውን መንገድ ተከትለን በእግር፥ በመኪና እና በሞተር ሳይክል ነው የወጣነው " - ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው

ለወራት በእስር ላይ ከቆዩ በኃላ ከእስር የተፈቱት ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናዬ ወደ ሙያቸው መመለስ ስላልቻሉ ከአገር መሰደዳቸውን ተናገሩ።

ሁለቱ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ከአገር ለመውጣት ከነሐሴ 28፤ 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ለአስራ አንድ ቀናት መጓዛቸውን ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

እንዴት ከአገር ወጡ ?

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ፥ " በጣም አስቸጋሪ የሚባለውን መንገድ ተከትለን በእግር፥ በመኪና እና በሞተር ሳይክል ነው የወጣነው። የነበሩብን የጉዞ እገዳዎች እና ክትትሎች መደበኛውን የጉዞ መንገድ እንድንጠቀም አላስቻለንም። " ሲል ተናግሯል።

ሁለቱም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች በጸጥታ ኃይሎች ከታሰሩ በኋላ አንድ ጊዜ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ነው ከእስር የተለቀቁት።

ከእስር ከተለቀቁ 3 ወራት ገደማ በኋላ ደግሞ አገር ጥለው ተሰድደዋል።

ከአገር ተሰዶ ለመውጣት ምክንያት ያሉት ምንድነው ?

ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ፦

" ከእስር ስንወጣ ያናገሩን የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት ሰዎች እና የፌደራል ፖሊስ አባል ከዚህ በኋላ የምናደርገውን እንቅስቃሴ እንደሚከታተሉን ገልጸውልናል። ይህ የመጀመሪያ ምክንያት ነው።

ወደ ሙያችን መመለስ ስላልቻልን ያለውን ችግር እና አፈናም መስበር የምንችልበት አቅም ስለሌለን ከአገር ወጥተናል።

ያንን ማድረግ የምንችለበት ዕድል ልናገኝ የምንችለው ከሀገር ስንወጣ ነው፥ መጀመሪያ ሕይወታችንን ማትረፍ አለብን በሚል ነው። በመንግሥት በኩል ሊገድሉን የሚችሉበት ዕድል ነበራቸው በተደጋጋሚ በእስር ቤት ውስጥ የሚነግሩን ያንን ነው።

መውጣቱ ሕይወትን ለማትረፍ ያሰብነው ነው፤ ቀጥሎ ደግሞ በሙያችን ለመስራት ያስችለን ይሆናል ብለን የገመትነው ነው።

በሙያችን መስራት ነው ዕቅዳችን በሀገር ውስጥ ካሉ ችግሮች አንጻር ስንሰራ የነበረውን ስራ የማስቀጠል ፍላጎት ነው ያለን። "

መረጃው የቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF #Tigray በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ። በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል። የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ…
#Tigray

" ... የቆየው አመራር በአካልና በስልክ ስልጣን ለማስረከብ ቢጠየቅም ፍቃደኛ መሆን አልቻለም  " -  አዲሱ የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተኽላይ ፍቓዱ 

በቅርብ በትግራይ ጊዜያዊ አስታዳደር የተሾሙት  የትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተኽላይ ፍቓዱ " የቆየው አመራር በአካልና በስልክ ስልጣን ለማስረከብ ቢጠየቅም ፍቃደኛ መሆን አልቻለም " ሲሉ ተናገሩ።

ይህን ያሉት ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ነው።

አቶ ተኽላይ ፥ በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ይፋዊ ደብዳቤ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ከተሾሙ ሁለት ሳምንት መቆጠሩን ተናግረዋን።

ነገር ግን የቆየው አስተዳደር በአካልም ሆነ በስልክ የስልጣን ርክክብ ለማደረግ ቢጠየቅም ፍቃደኛ መሆን አልቻለም።

" በመንግስት በጀት የመንግስት ተፃፃራሪ ሆኖ መቆም ሽፍትነት ነው " ያሉት አቶ ተኽላይ " ከዚህ በኋላ መንግስት ሕግና ስርዓት ለማስከበር ይገደዳል " በማለት አስጠንቅቀዋል፡፡

በቅርቡ የተከሰተው የህወሓት መሰነጣጠቅ ተክትሎ በየቀኑ አዳዲስ ክስተቶች በመታየት ላይ ይገኛሉ።

(ለማስታወስ)

በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው ተተኪ የሚባሉ 16 የማእከላዊ ኮሚቴ  አባላት ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ያልሰጡትን 14ኛው ጉባኤ አካሂደዋል፡፡

14ኛው ድርጅታዊ ጉባኤው ህጋዊ አይደለም ያሉት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በጉባኤው የስራ አሰፈፃሚ አድርጎ የመረጣቸው የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ ሊያ ካሳና የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተኽላይ ገ/መድህን ምትክ አዳዲስ የዞን አስተዳዳሪዎች ሹመዋል፡፡

የዶ/ር ደብረፅዮኑ ህወሓት መስከረም 6 /2017 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ 14ኛ ጉባኤው ያልተሳተፉት የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙባቸው 16 የማእከላይ ኮሚቴ  አባላት ከአባልነትና ከድርጅታዊ የስራ ሃላፊነታቸው ማባረሩን አሳውቋል።

የእነ ዶክተር ደብረፅዮኑ ህወሓት " ከአባልነትና ከድርጅት ሃላፊነት አባርሪያቸዋለሁ " ብሎ መግለጫ ካወጣባቸው 16 የድርጅቱ የማእከላይ ኮሚቴ 5 አሁንም በጊዚያዊ አስተዳደሩ እውቅናና ተቀባይነት ያላቸው የትግራይ ደቡባዊ ፣ ደቡባዊ ምስራቅ ፣ ምስራቅ ፣ ማእከላዊ ፣ ሰሜናዊ ምዕራብና የምዕራብ ዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች ናቸው፡፡

በእነ ዶክተር ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት በቅርቡ ባካሄደው ጉባኤ የማእከላይ ኮሚቴ አመራር በመሆን ከተመረጡት መካከል ይትባረክ ኣማሃና ኤልያስ ካሕሳይ የመቐለ ከተማ ዋናና ምክትል በመሆን በማስተዳደር ላይ ይገኛሉ በሃላፊነት ይቀጥሉ ይሆን ? በቀጣይ የምናየው ይሆናል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
2024/09/30 00:29:02
Back to Top
HTML Embed Code: