Telegram Web Link
#AASTU #ASTU

በ2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ገብተው በአፕላይድ ሳይንስና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ ጥሪ ቀርቧል።

ዩኒቨርሲቲዎቹ በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን ተጨማሪ የመግቢያ ፈተና በቀጥታ (online) በመስጠት ነው የሚቀበሉት።

የትምህርት መስኮቹ ምን ምን ናቸው ?

/ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል እና ኮምፒዩተር ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሮ መካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ፣ ማይኒንግ ኢንጂነሪንግ ፣ ኢንቫይሮሜንታል ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፉድ ሳይንስ፣ አፕላይድ ኒውትሪሽን ፣ ጂኦሎጂ፣ ባዮቴክኖሎጂ

/ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ /

#ኢንጂነሪንግ ፦ አርክቴክቸር፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ፣ ወተር ሪሶርስ ኢንጂነሪንግ ፣ ኬሚካል ኢንጂነሪንግ ፣  ሜካኒካል ኢንጂነሪንግ ፣ ማቴሪያል ሳይንስና ኢንጂነሪንግ ፣ ኤሌክትሪካል ፓወር እና ኮንትሮል ኢንጂነሪንግ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና ኮሚኒኬሽን ኢንጂነሪንግ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ ኢንጂነሪንግ፣ ሶፍት ዌር ኢንጂነሪንግ

#አፕላይድሳይንስ ፦ አፕላይድ ቦዮሎጂ፣ አፕላይድ ኬሚስትሪ፣ ኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ፣ ፋርማሲ፣ አፕላይድ ፊዚክስ ፣ አፕላይስ ጂኦሎጂ፣ አፕላይድ ማቲማቲክስ

የምዝገባ ጊዜ፡- ከመስከረም 06 እስከ መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሆነ ተገልጿል።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው መስከረም 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ ነው።

የምዝገባ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች በማንኛውም ስፍራ በኢንተርኔት (online https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et ድረገጽን በመጠቀም መመዝገብ ይችላሉ፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ቀን በድህረ ገጽ የምዝገባው ቀን ካበቃ በኋላ ይደረጋል።

ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ ፤ በምዝገባ ወቅት በመረጡት ዩኒቨርሲቲ (የፈተና ጣቢያ) በአካል በመቅረብ ይሆናል፡፡

NB. ለምዝገባና ለፈተና ምንም አይነት ክፍያ የማይጠየቅ ሲሆን የፈተና ጣቢያዎቹ ያላቸው የመፈተኛ ቦታ ውስን በመሆኑ ፍላጎቱ ያላቸው አመልካቾች ይህን አውቀው ቅድሚያ እንዲመዘገቡ ተብሏል።

@tikvahethiopia
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፕሮፌሰር በየነ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

ፕሮፌሰር በየነ ረዘም ላለ ጊዜ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውንም ጠቁመዋል።

" በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ " ሲሉም ገልጸዋል። 

@tikvahethiopia
🌼 ፍካት ከመስከረም፣ በረከት ከቴሌብር ሐዋላ!
17% ተጨማሪ ስጦታ ከበርካታ የዕድል ሽልማቶች ጋር!!


ከባሕር ማዶ በቴሌብር ሬሚትና በአጋሮቻችን በኩል ዓለም አቀፍ ሐዋላ የተላከልዎን ገንዘብ በቴሌብር ሲቀበሉ 17% የገንዘብ ስጦታ እንዲሁም:-

💁‍♂️ 5 ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!

✈️ የውጭ ሀገር ደርሶ መልስ የበረራ ትኬት - እያንዳንዳቸው 480,000 ብር
🏞 ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ ቤተሰብ ፓኬጅ - እያንዳንዳቸው 44,000 ብር
🐏 የበግ ስጦታዎች - እያንዳንዳቸው 20,000 ብር...

የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!

🗓 እስከ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

ሁሉም የፓለቲካ ፓርቲዎች በእኩል የሚያሳትፍ በምክር ቤት የሚመራ ሲቪል ጊዚያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም አራት የትግራይ ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጠየቁ።

የጋራ መግለጫውን ያወጡት ፦
- ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ፣
- ባይቶና ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፣
- ውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት)
- ዓረና ንሉኣላውነትን ዴሞክራስን  (ዓረና)  ናቸው።

ፓርቲዎቹ ባወጡት የጋራ መግለጫ ፤ " በትግራይ ያጋጠመው ችግር መነሻው ፓለቲካዊ ውድቀት ስለሆነ ከውድቀቱ ለመውጣት አካታች ፓለቲካዊ መፍትሄ ያስፈልጋል " ብለዋል።

" ችግሩ የሚፈታው አንድ የፓለቲካ ፓርቲ በሚያራምደው የበላይነት አመራር ሳይሆን ሁሉም አቀፍ በሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ለዚህም ሁሉም የፓለቲካ ሃይሎች በእኩል የሚሳተፉበት በምክር ቤት የሚመራ ስቪል ጊዚያዊ አስተዳደር ማቋቋም እንደ አንድ የችግር መፍቻ አስቀምጠዋል።

ፓርቲዎቹ በአሁኑ ወቅት በሁለት የህወሓት ሃይሎች የተፈጠረው ፓለቲካዊ መሳሳብ ወደ ጎን በመተው ወጣቶች ፣ ሴቶች ፣ የዳያስፓራ ማህበረሰብ መላው የትግራይ ህዝብ ዓላማቸው ደግፎ ከጎናቸው ሆኖ እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። 

" የትግራይ የፀጥታ ሃይሎች ከማንኛውም የፓለቲካ ሃይል ውግንና ነፃ በመሆን የሲቪል መንግስትና ህግ በመመራት ለህዝብና አገር ጥቅም መቆም አለባቸው " ሲሉ አሳስበዋል። 

በቅርቡ የሚፈፀሙት ተጨማሪ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው የመመለስ ፣ ግዛታዊ አንድነት የማስመለስ ፣ ታጣቃዎች ትጥቅ የማስፈታትና ወደ ህብረተሰቡ የመቀላቀልና ሌሎች በትግራይ በኩል የሚፈፀሙ ስምምነቶችና ውሎች ለህዝብና ጉዳዩ  ለሚመለከታቸው አካላት ግልፅና ይፋ እንዲደረግም ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ክስ ተመሰረተባቸው። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ? - አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ - የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል…
#Update

የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።

ግለሰቦቹ ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።

ዐቃቤ ህግ በ6ቱ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

የቀረበባቸው ክስ ለተከሳሾች ከደረሰ በኋላ በተከሳሾች ጠበቆች በኩል ደንበኞቻቸው " የተከሰሱበት ድንጋጌ በመርህ ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል አይችልም " በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ፤ የወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 67/ለ ጠቅሶ በልዩ ሁኔታ ዋስትና ሊያስከለክል ስለሚችል በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው ማለትም ፦
➡️ ከወንጀሉ ከባድነትና ከክሱ ተደራራቢነት፣
➡️ ከጉዳዩ ባህሪና ከከባቢያዊ ሁኔታዎች አንጻር ዋስትና ሊያስከለክሉ የሚችሉበትን ትርጉም የተሰጠባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥሮችን ጠቅሶ የዋስትና መብታቸው እንዲታለፍ ጠይቆ ነበር።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት ብይን ሰጥቶበታል።

በዚህም ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም በማለት የጠየቁት የዋስትና ጥያቄን ውድቅ ተደርጎ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል።

ክሱን ለመመልከትም ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ
1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @ TecnoEt ፣ ለ Instagram @ TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @ TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
#MesiratEthiopia

🌟 በቅርቡ መውሰድ ያለባችሁ ስልጠናዎች 🌟
የግል በጀት አወጣጥ መሠረታዊ ነገሮች (Basics of Personal Budgeting) 👇
📅 መስከረም 10, 2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት
🔗 Register Here: https://forms.gle/t2KczdEpPrNstvjz5

መሠረታዊ መብቶች (Fundamental Rights) 👇
📅 መስከረም 15, 2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት
🔗 Register Here: https://forms.gle/Vk2Yd44t8Cnba6Jm6

የንድፍ አስተሳሰብ (Design Thinking) 👇
📅 መስከረም 20, 2017 ዓ.ም
🕒 ከቀኑ 8:00 እስከ 11:00 ሰዓት
🔗 Register Here: https://forms.gle/6aurE6Q8nAZQdNz18
ይህ አጋጣሚ እንዳያመልጥዎ!
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትኩረት🚨 ዛሬም ድረስ የሰው ህይወት የሚቀጠፍባቸው የመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች ነዋሪዎች " በፈጣሪ ስም መፍትሄ ይፈለግልን ፤ ተሰቃየን ህይወታችን በሰቀቀን መግፋት ደከመን " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጥሪ አቅርበዋል። " ተደጋጋሚ እርቅ ይፈጸማል ግን ሳይቆይ ያገረሽና ደም ይፈሳል፣ ሰው ይገደላል የምንገባበት አጣን ድምጻችን ይሰማ " ብለዋል። ከሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ልዩ ወረዳዎች…
🔈 #የነዋሪዎችድምፅ

በመስቃንና ማረቆ እየሆነ ያለው ምንድን ነው ?

በማረቆ እና መስቃን መካከል ለዓመታት በሚስተዋለው ግጭት ግድያና መፈናቀል ሊቆም እንዳልቻለ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

አሁንም ከፍተኛ የሆነ የበቀል ሥሜት ስላለ ሥጋት እንዳለባቸው ገልጸው፣ የሚመለከታቸው ባለድረሻ አካላት ለጉዳዩ እልባት እንዲሰጡት ጠይቀዋል፡፡

የማረቆ ልዩ ወረዳ ነዋሪዎች ምን አሉ ?

“ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በምሽት ንፁሃንን ይገድላሉ። ከሳምንት በፊትም ግድያ ነበር። በጣም ግራ የሚያጋባ ወቅት ነው፡፡

መገደሉ፣ መፈናቀሉ እየተለመደ መጣ፡፡ ምን እናድርግ ?

ነገሩ ለረጅም ጊዜ ትክክለኛ መፍትሄ ሳያገኝ የግጭት ቀጠና በመሆኑ ጉዳዩ እያሳሰበው ግማሹ የአይምሮ እና ለተለያዩ የህመም አይነቶች እየተዳረገ ይገኛል፡፡

የችግሩ ምንጭ የማረቆ ህዝብ የጠየቀው የ9 ቀበሌ የማካለል ጉዳይ ነው፡፡

ጥያቄው ለብዙ አመታት ሲሆን፣ በዚህ ረጅም ዓመት በህግ አግባብ ከክልል ምክር ቤት እስከ ፌደሬሽን ሲጠየቅ ቆይቷል፡፡

ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ግን ከአምስት ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡

ለዚህ ግጭት ዋና ተጠያቂ ተብለው የሚወሰዱት ከጉራጌ ዞን እስከ ወረዳ ያሉ አመራሮችና የጸጥታ አካላት ናቸው።

በምሽት በሀሰተኛ ጥቆማና ጥርጣሬ ወጣቱን እያሳደዱት ስለሆነ ነገሩ ትኩረት ያስፈልገዋል ” ብለዋል፡፡

የምሥራቅ መስቃን ነዋሪዎች በበኩላቸው ፥ ከማረቆ ተፈናቅለው ወደ መስቃን የመጡ ወገኖች እንዳሉ ገልጸው፣ ችግሩ ያለው ሰላም ከማይፈልጉ ኃላፊነት ላይ ያሉ አካላት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

ግድያም በተለያየ ጊዜ እንደሚፈጸም ጠቁመዋል።

“ በማረቆ ተወላጆች ከስምንት በላይ ቀበሌዎች ተወስደውብናል ” የሚሉት ነዋሪዎቹ፣ ለዚህ ድርጊትም ኃላፊነት ላይ ያሉ አካላትን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡

አንድ ስለጉዳዩ ያጫወቱን በምሥራቅ መስቃን የሚገኙ የእድሜ ባለጸጋ፣ “ ሁለቱ ብሔረሰቦች ተስማምተው መኖር እንዳይችሉ እያደረጉ ያሉት የፖለቲካ ትርፍ የሚፈልጉ አካላት ናቸው ” ብለዋል፡፡

በሁለቱ ወረዳዎች መካከል የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር የተከሰተው በ2010 ዓ/ም ሲሆን፣ በ2014 ዓ/ም እርቀ ሰላም እንዲወርድ ተደርጎ ነበር፡፡

ይሁን እንጅ ከእርቀ ሰላሙ ወዲህም ችግር አገርሽቶ በየጊዜው ሞትና መፈናቀሉ ሊቆም አልቻለም፡፡

የሚመለከታቸው አካላት ምን እየሰሩ እንደሆነ ምላሽ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው አልተሳካም፡፡ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆኑ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዕለታዊ ዛሬ ንግድ ባንክ የዶላር መግዣ ላይ ጭማሪ በማድረግ ወደ 108 ብር ከ0728 ሳንቲም አስገብቷል። መሸጫው 119 ብር ከ9608 ሳንቲም ነው። በአቢሲኒያ ባንክ አንዱ ዶላር 108 ብር ከ0729 ሳንቲም መግዣ ፤ 121 ብር ከ0416 ሳንቲም መሸጫ ተቆርጦላታል። በወጋገን ባንክ የዶላር መግዣው 115 ብር ከ0121 ሳንቲም ነው። አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ደግሞ አንዱን የአሜሪካ ዶላር በ107…
#ዶላር

የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ አሳይቷል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ7 ቀናት ጭማሪ ያልታየበት ወጥ የምንዛሬ ዋጋ ነበር።

ባንኩ ዛሬ ሲያገበያይበት የነበረው የምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ የታየበት ነበር።

አንዱ የአሜሪካ ዶላር መግዣው ወደ 112 ብር ከ3957 ሳንቲም ደርሷል።

የመጫው ዋጋም 124 ብር ከ7592 ሳንቲም ገብቷል።

በፓውንድ ላይም ጭማሪ ተመዝግቧል።

አንዱ ፓውንድ መግዣው 141 ብር ከ6314 ሳንቲም ተቆርጦለት ውሏል። መሸጫው 157 ብር ከ9487 ሳንቲም ነበር።

ዩሮ መግዣው 125 ብር ከ0177 ሳንቲም መሸጫው 138 ብር ከ7697 ሳንቲም ሆኖ ውሏል።

የUAE ድርሃም መግዣው 30 ብር ከ6030 ሳንቲም መሸጫው 33 ብር ከ9693 ሳንቲም ገብቷል።

#Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የመመዝገቢያ ቀናት ከጳጉሜ 5/2016 ዓ.ም - መስከረም 8/2017 ዓ.ም ድረስ ነው " - የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋዉ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2017 ዓ /ም  ለቅድመ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች ለመቀበል መዘጋጀቱን አሳውቆናል። ዩኒቨርሲቲው ለ2017 ቅድመ ምረቃ ትምህርት በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል ከፍለዉ ለሚማሩ እንዲሁም በማታ በተከታታይ መርሃ ግብር…
#AAU

ራስ ገዙ አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በቀን በመደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሺፕ እና በግል በመጀመሪያ ዲግሪ በ2017 ዓ/ም መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ያቀረበው ጥሪ ነገ ያበቃል።

በ2017 ዓ/ም በቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ ግብር በትምህርት ሚኒስቴር ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  የተማሪዎች ምደባ እንደማይኖር  ይታወቃል።

በመንግስት ስኮላርሺፕ እንዲሁም በግል ከፍለው በዩኒቨርሲቲው መማር ለሚፈልጉ በሙሉ የአ.አ.ዩ  የሚያወጣውን የመግቢያ ፈተና (UAT) እንዲሁም ሌሎች መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

በዚህም መሠረት በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጾች ፦
➡️ www.aau.edu.et
➡️ https://portal.aau.edu.et ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር የማመልከቻ መስፈርቶች በማሟላት መመዝገብ ይችላሉ።

የመመዝገቢያ ቀኑ ነገ መስከረም 8/ 2017 ዓ.ም ያበቃል።

የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀናት ወደፊት ይገለጻል።

በመንግስት ስኮላርሽፕ ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለመማር የሚያያዘው ማስረጃ ምንድነው ?

በቀን መደበኛ መርሃ ግብር በመንግስት ስኮላርሽፕ ለመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርት ለማመልከት ከተጠየቁት መስፈርቶች አንዱ የቤተሰብ የገቢ መጠንን የሚገልፅ ማስረጃ ማያያዝ ነው።

በዚህ መሰረት ፦

1. ከወረዳ/ቀበሌ ወይም መስሪያ ቤት ስለገቢያቸዉ ዝቅተኛነት የሚገልፅ ማስረጃ ከሚመለከተዉ ከወረዳ ወይም ቀበሌ ወይም መስሪያ ቤት ዘርፍ ኃላፊ ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

2. የቤተሰቡ ኃላፊ ጡረታ ላይ የሚገኙ መሆናቸዉን የሚገልፅ ደብዳቤ ወይም የታደሰ የጡረተኝነት መታወቂያ ወይም የባንክ ደብተር ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

https://www.tg-me.com/TikvahUniversity/12317

(Addis Ababa University)

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በሀሰተኛ የብር ኖት ግብይት የፈፀሙ 2 ተጠርጣሪዎች እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ጎሮ ገብርኤል አካባቢ መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 12፡ 30 ሰዓት ላይ ነው።

ግለሰቦቹ ከአንድ ሸቀጣ ሸቀጥ መሸጫ እና ዘይት አከፋፋይ ከሆነ ሱቅ ውስጥ በርከት ያለ ባለ 20 ሊትር ዘይት ለመግዛት ተስማምተው ያስጭናሉ።

በኋላም ሒሳብ ሲከፍሉ ገንዘቡ ከባንክ እንደወጣና ህጋዊ ለማስመሰል አሽገው 42 ሺህ 350 ብር ለነጋዴው ይከፍሉታል፡፡

ሆኖም የግል ተበዳይ ገንዘቡ ሀሰተኛ መሆኑን ተጠራጥሮ በአካባቢ ነዋሪዎች ትብብር እንዲያዙ አድርጓል።

ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይ መጠራጠሩን ሲረዱ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 30791 ተሽከርካሪ በመጠቀም ለማምለጥ ቢሞክሩም በአካባቢው በነበሩ ሰዎች ሊያዙ ችለዋል።

ግብይት ሊፈፅሙበት ከነበረ 42 ሺህ 3 መቶ 50 ብር ውስጥ 39 ሺህ 4 መቶ ሃሰተኛ ብር እጅ ከፍንጅ ተይዘው ምርመራ እየተደረገ እንደሆነ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
2024/10/01 17:41:46
Back to Top
HTML Embed Code: