Telegram Web Link
🌟 17% የገንዘብ ስጦታ ያግኙ፤ የበረራ ትኬት ጨምሮ ልዩ ሽልማቶችን ያሸንፉ!

ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሐዋላ የተላከልዎን ገንዘብ ሲቀበሉ 17% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡

💁‍♂️ በተጨማሪም 5 ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!

✈️ ደርሶ መልስ የበረራ ትኬት - እያንዳንዳቸው 480,000 ብር
🏞 ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ ቤተሰብ ፓኬጅ - እያንዳንዳቸው 44,000 ብር
🐏 የበግ ስጦታዎች - እያንዳንዳቸው 20,000 ብር...

የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!

🗓 እስከ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba #ባጃጅ በአዲስ አበባ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት በሂደት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ አይቀሬ እንደሆነ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ከተማ የባለሶስት እና አራት እግር ተሽከርካሪ ወይም ባጃጅ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች  የአሰራር ፣ የአጀረጃጀት፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የዲሲፒሊን ቁጥጥር አፈጻጸም መመሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጎ ነበር።                               …
#AddisAbaba

“ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ ” - የኡ/ ትራንስፖርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ውጪ መጥተው የሚሰሩ ባለሦስትና አራት እግር አሽከርካሪዎች የአዲስ አበባ መታወቂያ፣ የአዲስ አበባ ሰሌዳ እስከሚያሟሉና በማኅበር እንስከሚደራጁ ድረስ በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይሰጡ እንደሚደረግ ማሳወቁ ይታወሳል።

ቢሮው ይህን ያለው በእነዚህ የተሽከርካሪ አይነቶች ወንጀል እየተፈጸመ መሆኑን በመግለጽ ነው፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ጉዳዩን በተመለከተ ከወጣው መግለጫ በተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጥ ከከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡

Q. በታገዱት የትራንስፖርት አይነቶች ሥራ ተሰማርተው ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ አሽከርካሪዎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ለምን ሰፋ ያለ ጊዜ አልተሰጣቸውም ? ቀድሞ ማሳወቅ አይቻልም ነበር ?

አቶ ዳኛቸው ፦

“ አዲስ አበባ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርት ነው፡፡ ከማስ ትራንስፖርት አንጻር አዲስ አበባ አውቶብስ ድርጅት አለ፡፡ ድጋፍ ሰጪ የምንላቸው ሦስት ቁጥር ታክሲዎች አሉ፡፡ ከዚያ ውጪ ቁጥር አንድ የምንላቸው ታክሲዎች አሉ፡፡

ከእነዚህም የበለጠ የሚበረታታውና የሚደገፈው ማስ ትራንስፖርቱ ነው፡፡ ከባጃጅ ትራንስፖርት ጋር ባለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደራጅቶ ስምሪት መስጠት የሚችለው በአዋጁ መሠረት ራሱ የሰጠውን ታርጋ ብቻ ነው፡፡

ይሄ በአዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ክልሎችና ከተሞች በራሳቸው ታርጋ የሰጡት፣ የመዘገቡት ብቻ ነው አደራጅተው ማሰማራት የሚችሉት፡፡

ከባጃጂ ጋር ተያይዞ አዲስ አበባ ውስጥ ወደ 5,000 አካባቢ የሚጠጉ ባጃጆች በ93 ማኅበራት፣ እንዲሁም በ73 መስመሮች አካባቢ ላይ ታፔላ ወስደው እየተሰማሩ ነው ያሉት፡፡

አዲስ አበባ በዚህ ደረጃ አጣዳፊ ሥራውን ማሰማራት ተገቢነት የለውም፡፡

ከአዋጅ ውጪ ነው የሚል ቅሬታዎች በተደጋጋሚ ሲነሳ ነው የቆየው፡፡ ቅሬታውም ተገቢ ነው፡፡  ስለዚህ በዚህ ሰዓት ባጃጅን ማበረታታት፣ ማሰማራት አይደገፍም፡፡

በአንድ በኩል የአዲስ አበባ ታርጋ የላቸውም ኦልሞስት 99 ፐርሰንት፡፡ 243 ብቻ ናቸው የአዲስ አበባ ታርጋ ያላቸው ከ5 ሺዎቹ፡፡

አንደኛ ሕጉ መከበር አለበት፡፡ ስህተት በስህተት ላይ መደገም የለበትም፡፡ ሁለተኛ እነዚህ ባጃጆች አካባቢ ሌብነት ይካሄዳሉ፡፡

ህዝቡም እሮሮ ያቀርበል፡፡ ብዙ ቅሬታዎች ናቸው የሚቀርቡት፡፡ የጽንፈኛ ኃይልም አጋዢ ሆነው የሚሰሩ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ለከተማው ጸጥታ ስጋት የሆኑ ባጃጆች አሉ፡፡

ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ስለዚህ እንዚህ ባጃጆች እንዲቆሙ ሳይሆን ወደ ሕግ እንዲመለሱ ነው፡፡ ወደ ሕግ እንዲመለሱ ሲደረግ ደግሞ አንደኛ መደረግ ያለበት አንደኛ ታርጋ ማውጣት ነው፡፡

ታርጋ ለማውጣት ደግሞ እዘዚህ ባጃጆች ታርጋ ያወጡበት ሂደው ክሊራንስ፣ ሊብሬ አምጥተው የአዲስ አበባ ታርጋ ወስደው እንዲደራጁና ወደ ስምሪት እንዲገቡ ማድረግ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ታርጋ ይወስዳሉ፣ ይዘጋጃሉ፣ ወደነበሩበት ይመለሳሉ”።


Q. ቢሮው አጣድፎ ውሳኔውን የወሰነበት ምክንያት ምንድን ነው? አጭር ጊዜ አልሆነም ወይ? ለሚለው ጥያቄ ቀጥታ ምላሽ እንዲሰጡ በድጋሚ ጠይቀናቸዋል፡፡

አቶ ዳኛቸው፦

“ ከተማ አስተዳደሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ለከተማው ሰላም ነው፡፡ ትራንስፖርት ሰላምን መሆንን፣ ምቹ መሆንን፣ ተደራሽ መሆንን ይፈልጋል። ስለዚህ በባጃጆች አካባቢ ያለው ሌብነት፣ ዝርፊያ፣ ያለው የከተማውን ሰላም የማናጋት መጠቀሚያነት ከህዝብ በተደጋጋሚ እሮሮ የመጣበት ነው።

ሁለተኛ ታርጋ የሰጥዋቸው ክልሎች፣ ‘አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እኛ የሰጠነውን ካርታና ሊብሬ አደራጅቶ የማሰማራት ስልጣን የለውም ሕገ ወጥ ሥራ ነው እየሠራ ያለው’ የሚል ቅሬታ፣ ስሞታ፣ ክስ አለ፡፡

እውነት ነው በሰላማዊ መንገድ ሥራ የሚሰሩ ልጆች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ እነርሱንና ጤናማ ያልሆኑትን ለመለየት ወደ ሕጋዊ መስመር መመለስ ግድ ስለሆነ፡፡

ሰፊ ጊዜ የሚፈልግ ጉዳይ አይደለም፤ ምርምር አይደለም፡፡ ታርጋ ያወጡበት፣ መረጃቸው ያለበት ሂደው ማምጣት ነው፡፡ አብዛኛው ደግሞ መረጃ የሚያሳየው ሸገር ዙሪያ ነው፡፡

ምክንያቱም አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባጃጂ ታርጋ ሲሰጥ ስላልነበረ አብዛኛው ያወጡት እዚህ አካባቢ ናቸው። አማራ ክልልም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡ ሌሎች አካባቢዎችም ተጭነው የመጡ አሉ ይታወቃል፡፡

ዞሮ ዞሮ ግን ለምን ተጣደፋችሁ? ለሚለው ነገር የከተማውን ሰላምና ጸጥታ ለማስጠበቅ ማንኛውም ተሽከርካሪ ሕግ አክብሮ እንዲሰራ ለማድረግ ነው”፡፡


Q. አሽከርካሪዎቹ በከተማዋ ለመስራት እንደያሟሉ ከተጠየቁት መስፈርት አንዱ የአዲስ አበባ የነዋሪነት መታወቂያ መሟላት ነው፡፡ ይህን አገልግሎት ደግሞ ኤጀንሲው እየሰጠ አይደለም፡፡ መታወቂያውን የት አምጥው ያሟላሉ ተብሎ ነው እንዲህ የተደረገው ? ቢሮው ጉዳዩን አጢኖት ነበር ?

አቶ ዳኛቸው፦

“ ይሄ ጥያቄ ለምን Issue ሆኖ ይነሳል? የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መታወቂያ እየሰጠ አይደለም የሚለው መረጃ ስህተት ነው፡፡

ወሳኝ ኩነት ከከተማ ጀምሮ እስከ ወረዳ አደራጅቶ በቴክኖሎጅ ታግዞ ነዋሪው ግልጽ በሆነ መንገድ መታወቂያ እንዲያገኝ አመቻቾቶ መስራት ከጀመረ አመታት ተቆጥረዋል። "


Q. ከክልል ከተሞች በመሸኛ ለሚመጡት እየሰጠ እንዳልሆነ መረጃው እንዳለን ገልጸንላቸው፣ በድጋሚ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀናቸዋል፡፡
አቶ ዳኛቸው፦


“ አሁን እኛ እያወራን ያለነው ከክልል ሰው አዲስ አበባ ውስጥ መታወቂያ አውጥቶ ሥራ ይስራ እያልን አይደለም ያለነው፡፡ ግልጽ ነው አቅጣጫው ለምንድን ነው የአዲስ አበባ ነዋሪ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈለገው ?

ዝርፊያዎች፣ ሌብነት፣ ተለያዩ ጽንፈኛ ኃይሎች መጠቀሚያ መሆን ማስቀረት ከተፈለገ የነዋሪነት ወታወቂያ የግድ ያስፈልጋል። ”
ብለዋል፡፡

ሌላ ጥያቄ እያቀረብንላቸው በነበረበት ወቅትም ማብራሪያቸውን መቅዳት እንድናቆም አስገድደው፣ ለጥያቄው ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምላሽ ላልሰጠባቸው ሌሎች በርከት ያሉ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፍ/ቤት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ፤ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል " ተብለው የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱ ተሰማ። የፌደራል መርማሪ ፖሊስ የምርመራ ቡድን፦ - ዮሃንስ ዳንኤል - አማኑኤል መውጫ፣…
ክስ ተመሰረተባቸው።

" የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ?

- አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣
- የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል የወንጀል ክስ ነው።

በተጨማሪም በ1ኛ ተከሳሽ ዮሃንስ ዳንኤል ላይ ብቻ " የአየር መንገዱን መልካም ስም ለማጉደፍ ተንቀሳቃሽ ምስል በኮምፒውተር ስርዓት አማካኝነት ማሰራጨት ወንጀል የሚል ክስ " አቅርቧል።

ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#MPESASafaricom

የበዓል ጉዞውን በM-PESA እንቁረጥ እና 5% ተመላሻችን ፈጥኖ ይደርሰናል!
Bon voyage !

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
 
#FurtherAheadTogether
#flyethiopian
" 60 ሰዎችን አግተው ወስደዋል ፤ 369 ከብቶች ተዘርፈዋል ፤ 19 ቤቶችን አቃጥለዋል " - በትግራይ ክልል የምስራቃዊ ዞን

የኤርትራ መንግስት ወታደሮች 60 ሰዎች አግተው መውሰዳቸው 369 ከብቶችን በመዝረፍ 19 ቤት ማቃጠላቸው ተገልጿል።

የኤርትራ መንግስት ወታደሮች የእገታ የዝርፍያና ቤቶች የማቃጠል ተግባር የፈፀሙት በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የኢሮብና ጉሎመኸዳ ወረዳዎች እንደሆነ የዞኑ የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት አሳውቋል።

ከዞኑ ኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ፥ ታግተው ከተወሱዱት 60 ሰዎች ሁለቱ ሴቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ወጣቶችና የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች ናቸው።

የኢሮብና የጉመኸዳ ወረዳዎች 8 የቀበሌ ገበሬ ማህበራት የትግራይ ጦርነት ከተጀመረበት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ወዲህ ሙሉ በሙሉና በከፊል በኤርትራ መንግስት ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።

ለድህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉት የጉሎመኸዳ ወረዳ ቀበሌ ገበሬ ማህበራት አርሶ አደሮች በሰጡት አስተያየት ፥ ባሳለፍነው ዓመት መጨረሻ በዜጎች ላይ ያነጣጠረ አፈና ተባብሶ መቀጠሉ አመልክተዋል።

" በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የትግራይ ክልል ግዛታዊ አንድነት ወደነበረበት ባለመመለሱና የኤርትራ ሰራዊት ከአከባቢያቸው ሙሉ በሙሉ ባለመውጣቱ ለአፈናና ለከባድ የፀጥታ ስጋት አደጋ ተጋልጠናል " ብለዋል።

የጉሎመኸዳ ወረዳ የሰላምና የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊ ነብዩ ስዩም በበኩላቸው " በሙሉና በከፊል በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ከሚገኙ የወረዳው 4 ቀበሌ ገበሬ ማህበራት አስከአሁን 52 ወገኖች ታፍነው መወሰዳቸው እረጋግጠናል " ብለዋል።

" ማርታ ፣ አዲስ ተስፋ ፣ አዲስ ዓለም ሙሉ በሙሉ ሸዊት ለምለም በከፊል በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ይገኛሉ " ያሉት ሃላፊው " የኢትዮጵያ የአገር መከላከያ ሰራዊት በአከባቢው የለም " ሲሉ ገልፀዋል።

በተያያዘ ባለፈው ዓመት መጨረሻ ከተለያዩ የኢሮብ ወረዳ ቀበሌ ገበሬ ማህበራት 8 ሰዎች ታፍነው 222 ከብት፣ 157 ፍየልና በጎች ሲዘረፉ 19 ቤቶች በኤርትራ መንግስት መቃጠላቸው የዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) ሊቀ-መንበር ዶሪ አስገዶም አስታውቀዋል። 

የወረዳው የኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት እንደገለፀው አራት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በሙሉና በከፊል በኤርትራ መንግስት ወታደሮች ቁጥጥር ስር ይገኛሉ።

በኤርትራ መንግስት ወታደሮች ቁጥጥር ስር የሚገኘው የአከባቢው ማህበረሰብ ለአራት ዓመታት በከፍተኛ የፀጥታ አደጋ ስጋትና ተስፋ መቁረጥ ስሜት እንደሚገኝ የገለፁት የወረዳዎች ነዋሪና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ገልጸዋል።

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተተግብሮ የኤርትራ ጦር ከያዘው አካባቢ እንዲወጣ ፣ የህዝብ ደህንነት እንዲጠበው፣ ተፈናቃዮች ወደ ቂያቸው እንዲመለሱ ተጠይቋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#መውሊድ : 1499ኛው የታላቁ ነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በነገው ዕለት #እሁድ እንደሚከበር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት አሳውቋል።

@tikvahethiopia
2024/09/30 16:20:54
Back to Top
HTML Embed Code: