Telegram Web Link
ግሎባል ባንክ እየሸለመ ነው !

መልዕክቱን ያጋሩ፣ ከ1ሺህ ብር ጀምሮ ተሸላሚ ይሁኑ !
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ 5ኛ ዙር ሽልማት

1. በመጀመሪያ ቀጣዩን የቦት ሊንክ ይጫኑ፡- https://www.tg-me.com/global_bank_referral_bot?start=476862805
2. START የሚለውን ይጫኑ፣
3. JOIN CHANNEL የሚለውን ይጫኑ፣
4. ወደ መጀመሪያው ቦት ይመለሱ፣
5. CONTINUE የሚለውን ሲጫኑ የመጋበዣ ሊንክዎን ያገኛሉ፣
6. መልዕክቱን ቢያንስ ለ30  እና ከዚያ በላይ ወዳጅ ዘመድዎ ሼር ሲያደርጉ ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በየሳምንቱ ከአንድ ሺ ብር ጀምሮ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን ያበረክታል፡፡
ሽልማቱ በመጪው ሰኞ ለተሸላሚዎች ይደርሳል፡፡
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚ ናቸው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በነፃ የጥሪ ማዕከል ቁጥራችን ☎️ 8118 ☎️ ይደውሉ፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!
#ደራ🚨

" የደራ ወረዳ ነዋሪዎች በሁለት ታጣቂዎች መካከል እየተሰቃዩ ናቸው " - ነዋሪዎች

በሰሜን ሸዋ ደራ ወረዳ የተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ በታጣቂዎች እየተፈጸመ ባለው ጥቃት አሁንም የዜጎች ህይወት እየጠፋ፣ ነዋሪውም ቄዬውን ለቆ ለመሸሽ እየተገደደ ይገኛል።

አንዴ በፋኖ ታጣቂዎች አንዴ ደግሞ በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ታጣቂዎች መከራቸውን እያዩ እንደሆነ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በወረዳው በተለይ በ13 ቀበሌዎች ከሁለት ሳምንት ወዲህ ተቀስቅሷል በተባለ የጸጥታ መደፍረስ የሰዎች ህይወት መጥፋቱ ተሰምቷል።

አንድ የጅሩዳዳ ነዋሪ ፥ አራት አርሶ አደሮች በእርሻ ስራቸው ላይ እያሉ መገደላቸውን ገልጸዋል።

ከወረዳው 44 ቀበሌዎች በ18ቱ የታጣቂዎች እንጂ የመንግሥት መዋቅር እንደሌለ ጠቁመዋል።

ሌላ ነዋሪ ፤ " የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ሲመጣ መኪና አስቁሞ የአማራ ተወላጆችን አግቶ ይወስዳል።  የፋኖ ኃይል ደግሞ የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እርምጃ ይወስዳል። የደራ ወረዳ ነዋሪዎች በሁለት ታጣቂዎች መካከል እየተሰቃዩ ናቸው። ነዋሪዎች ሰላም ፍለጋ ቄያቸውን እና ንብረታቸውን ጥለው በኤጄሬ በኩል እያቋረጡ ወደ ፍቼ እየሸሹ ነው። ጓደኛዬ የ15 ቀን አራስ ሚስቱን ይዞ ሸሽቷል። ህዝቡ ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ነው። መንግስት አፋጣኝ መፍትሄ መስጠት አለበት " ብለዋል።

ሌላኛው ነዋሪ ፤ " እየተሰቃየን ይኸው ሁለት ዓመት አሳልፈናል የመንግስት ዝምታ አልገባንም " ያሉ ሲሆን ከቀናት በፊት በቱቲ ቀበሌ በኩል የፋኖ ኃይል ተኩስ መክፈቱን ጠቁመዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪው አቶ ከፍያለው አዳሬ ፤ በደራ ወረዳ የጸጥታ ችግር መኖሩን አረጋግጠዋል።

" የደራ እና ሂዳቡ አቦቴ ነዋሪዎች ብዙ ጊዜ በፋኖ እና ሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት ይደርስባቸዋል። ታጣቂዎቹ የነዋሪዎችን ቤት ያቃጥላሉ፣ ሰዎችንም ያግታሉ። ሁለቱም ኃይሎች ህዝቡን በብሄር እና በሃይማኖት ለማጋጨት በተደጋጋሚ ይጥራሉ። ለምሳሌ ፦ ' ፋኖ ነኝ ' ባዩ አካል የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን ንብረት ያወድማል ፤ የሸኔ ታጣቂም እንደዛው የአማራ ብሄር ተወላጆችን ንብረት ያወድማል " ብለዋል።

" የመንግስት የጸጥታ ኃይል በሁለቱም ታጣቂ ኃይሎች ላይ እርምጃ እየወሰደ ነው " ሲሉ አክለዋል።

" ደራ ወረዳ አልፈረሰችም የመንግሥት ማዋቅርም አለ "  ያሉት አስተዳዳሪው " የመንግስት ኃይል በማይደርስባቸው ቦታዎች ሰላም ለማስፈን አስቸጋሪ ሆኗል " ብለዋል።

" ታጣቂው ኃይል በእነዛ ቀበሌዎች ነው ያለው ግን ሌላም ቦታ ገብቶ አያጠፋም ማለት አይቻልም ፤ ይህ ታጣቂ ኃይል ከሌላ አካባቢ የመጣ ሳይሆን ከዚሁ አፋና ኦሮሞ እና አማርኛ ተናጋሪ ህብረተሰብ ውስጥ የወጣ ነው ገሚሱ ተገዶ ሌሎቹ ፈቅደው ነው  የታጣቂውን ቡድን ተልዕኮ ተቀብለው ለሰላም ጠንቅ ሆነዋል " ሲሉ አክለዋል።

አቶ ከፍያለው የደራ ጸጥታ ጉዳይ ሰራዊት / የጸጥታ ኃይል በማስለፍ ብቻ መፍትሄ እንደማያገኝ ገልጸው ነዋሪዎች ለሰላም መስራት አለባቸው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዚህ መረጃ ባለቤት የቪኦኤ ሬድዮ አማርኛው ክፍል (ጸሐይ ዳምጠው) መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia🕊

ቅዱስነታቸው ሁሉም ለሰላም በአንድነት እንዲቆም ጥሪ አቀረቡ።

" የሃይማኖት ተቋሞቻችን ለዘላቂ ሰላማችን " በሚል ርእስ በአዲስ አበባ አንድ መድረክ ተካሂዷል።

በዚህም መድረክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወክጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው ፤ " ጥላቻ፣ ጦርነት፣ ጠብ፣ ክርክር፣ ሞኝ መሆኑን እያወቅን እዚያ ላይ እንንከባለላለን። የሰው ልጅ ህልውናውን ለመጠበቅ ሰላምን መምረጥ እና መከተል ይኖርበታል " ብለዋል።

" የሰላምን እጦት ያመጣነው ራሳችን ነን። ማንም አምጥቶ አልጫነብንም " ያሉ ሲሆን " ሰላም ከሌላ መንፈሳዊም ሆነ ዓለማዊ ተቋማት ምንም መሰራት እንደማይችሉ አውቀን ለሰላም በአንድነት መቆምና ሰላምን መከተል ይኖርብናል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ለዚህም ሁላችንም ከቀደመው እየተማርን መጪውን ሰላማዊ ለማድረግ መጣር ይኖርብናል " ብለዋል።

ቅዱስነታቸው ፥ " የሔድንበት መንገድ ጎድቶናል ስለሆነም ወደ ሰላም እንመለስ ብለን መወሰን አለብን። ለዚህም ሁላችንም ወደ አእምሮችን ተመልሰን ሰላምን እንከተላት " ሲሉ አባታዊ ጥሪ አቅርበዋል።

#EOTC
#Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ ምንም እንኳን ትላንትና የኬንያ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ በፋይናንስ ረቂቅ ሕጉ ላይ ፊርማቸውን እንደማያኖሩ እና ሙሉ በሙሉ ውድቅ እንደተደረገ ቢያሳውቁም ዛሬም ተቃዋሚዎች አደባባይ ወጥተው ነበር። ናይኖቢ ውስጥ የመንግስት ጸጥታ ኃይሎች አደባባይ በወጡ ተቃዋሚዎች ላይ አስለቃሽ ጪስ ተኩሰዋል። ወደ ፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት የሚወስደውን መንገድ ዘግተውታል። ዛሬም በከተማይቱ በርካታ የንግድ ተቋማት…
#Kenya

በኬንያ ሰሞነኛውን ተቃውሞ እና ሰልፍ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በርካቶች ዝርፊያ ላይ መሰማራታቸው ተሰምቷል።

የሀገሪቱ የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት ዝርፊያ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች " ዋጋቸውን ያገኛሉ " ብሏል።

በኬንያ ከፋይናንስ ሕጉ ጋር የተቀሰቀሰው ተቃውሞ አልቆመም።

ምንም እንኳን ፕሬዜዳንት ሩቶ " ትቼዋለሁ ፤ አልፈርምም፣ ተሰርዟል " ቢሉም ተቃዋሚዎቻቸው " ረፍዷል ስልጣን ይልቀቁ " በሚል ተቃውመ ቀጥለዋል።

ተቃውሞውን ተከትሎ ግን በርካታ ዘረፋዎች እየተፈጸሙ ነው።

እነዚህ የዝርፊያ ተግባራት በዜጎች የእጅ ስልክ እና በደህንነት ካሜራዎች ተቀርጸው እየተሰራጩ ነው።

የኬንያ የወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት ተቃውሞ እና ሰልፉን በመጠቀም የወሮበሎች ቡድን ንጹሃንን ሲዘርፉ መታየታቸውን እና እነዚህን ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ለማዋል እየተሰራ እንደሆነ አመልክቷል።

ዘራፊዎች የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ ዋጋቸውን ያገኛሉም ብሏል።

ሌሎችም ከሰልፉ ጋር በተያዘ ህገወጥ ተግባር ላይ ተሳትፈዋል ያላቸውን ተፈላጊ ተጠርጣሪ ሰዎችንም በፎቶ አሰራጭቷል።

@tikvahethiopia
አንጋፋው ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ከ ' አዲስ አድማስ ጋዜጣ ' መሥራች አንዱ እና በዋና አዘጋጅነትም ጋዜጣዋን ተወዳጅ ያደረጋት ገጣሚና ደራሲ ነቢይ መኮንን ባደረበት ህመም ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ዛሬ ረቡዕ ረፋድ ላይ ድንገት ህይወቱ አልፏል።

ነቢይ ተርጓሚ ፣ ገጣሚ ወግ አዋቂ የጥበብ ሰው ነበር።

Via @tikvahethmagazine
#Ethiopia

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ አቶ ካሳሁን ጎፌን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር አድርገው ሾሙ።

ወ/ሮ ሽዊት ሻንካን ደግሞ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር አድርገው ሾመዋቸዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር የነበሩት አቶ ቀጀላ መርዳሳ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወጣቶች እና ስፖርት አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ከዛሬ ሰኔ 26 /2016 ዓ/ም ጀምሮ እንደ ተሾሙ ታውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፓለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 “ መንግስት እንደ መንግስት ሥራውን እየሰራ አይደለም ” ሲል ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ተቸ። የፓርቲው ሊቀመንበር ፤ ዶክተር አብዱልቃድር አደም ስለወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች የፓርቲያቸውን ምልከታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርተዋል። ሊቀመንበሩ በነበራቸው ቆይታ  ፦ - የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል ጉዳይ - የኑሮ ውድነት - የሰላም እና ጸጥታ ጉዳይ - ከሰሞኑን…
" ሁለት ወራት ከ18 ቀናት ነው መተከል የቆየሁት አንድም ቀን መብራት አልበራም " - ዶክተር መብራቱ አለሙ

የኢትዮጵያ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሥራ አስፈፃሚ ፣ የቦሮ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ቦሮ) የውጪ እና ዓለም አቀፍ ዘርፍ ኃላፊ ፣ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር መብራቱ አለሙ የቦሮ ዲሞክራሲ ፓርቲን ወክለው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በዚህ ቆይታቸው ፦
- ስለ ሰሞነኛው ምርጫ
- ስለ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የደህንነትና ሰላም ሁኔታ
- ከምርጫ ሲመለሱ ስላጋጠማቸው ነገር
- ስለ መሰረተ ልማት ጉዳይ ... ሌሎችም ጉዳዮች ተነስተውበታል።

ዶ/ር መብራቱ አለሙ ከተናገሩት ፦

" በዚህ ምርጫ ላይ ህዝባችን በምን ሁኔታ ውስጥ እንዳለ ለማየት ሞክረናል።

2 ወራት ከ18 ቀናት ነው መተከል የቆየሁት አንድም ቀን መብራት አልበራም።

ኤሌክትሪክ ከተዘረጋ ወደ 10 ዓመታት ይሆነዋል ፤ ግን ከግጭቱ በኋላ መሠረተ ልማቶች ተመልሰው አልተገነቡም። ጨለማ ውስጥ ነው መተከል ያለው።

ገዢው ፓርቲ (ብልጽግና) ደግሞ የሚበራ አምፓል ነው ያቀረበው ለምርጫ እንኳ ምልክት አድርጎ።  ‘ የቆመ ፓል እንጂ ሚበራ አምፓል የለም ’ እያሉ መፈክር ያሰሙ ነበር የኛ የፓርቲ ደጋፊዎች።

የሚጠጣ ንጹህ ውሃ የለም፤ መንገድ የለም።

መተከል ዞን ማለት የህዳሴው ግድብ፣ ብዙ ብሔር ብሔረሰቦች ፣ ሰፋፊ መሬት ፣ ከሱዳንም ጋር ረጅም ድንበር ያሉበት ዞን ነው።

ይህ ዞን እንግዲህ የመልካም አስተዳደር ፣ የመንገድ እጦት አይገባውም። የተማረ የሰው ኃይል አለው። ይሄ ማለት በክልሉ የLeadership ክፍተት አለ። ይሄንን የገዢው ፓርቲም ቢሆን አይቶ እልባት እንዲሰጠው እንደ ፓርቲ ሰላማዊ ትግል እናደርጋለን።

የክልሉ መንግስት በተለይ በተለይ በመሠረተ ልማት ላይ ኮሚቴ አቋቁሞ በደንብ መስራት እንዳለበት ይሰማኛል።

በተረፈ ብዙ ችግሮች አሉ። በመልካም አስተዳደር ፣ በሙስና (በተለይም ማዕድን ያለበት አካባቢ ላይ)፣ የወርቅ ኮንትሮባንድ ንግድ በጣም ከፍተኛ ነው። ይሄ ሁሉ ችግር ተደማምሮ ህዝቡ ችግር ላይ ነው። "

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-03

#የፖለቲካፓርቲዎችምንይላሉ? #ቦሮፓርቲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sidama #Hawassa ° " በሀዋሳ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ነዳጅ በመቋረጡ ለከፋ ችግር ተጋልጠናል " - የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች ° " በእጃችን ምንም ነዳጅ ባለመኖሩ ተጠቃሚው ለተወሰነ ጊዜ ይታገሰን " - የሀዋሳ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016 በሀዋሳ ከተማ ያሉ ማደያዎች መዘጋታቸውን ተከትሎ በርካታ የህዝብ ትራንስፖርት አሽከርካሪዎች መቆማቸውን በመግለጽ ቅሬታቸዉን…
#Sidama

በሀዋሳ ከተማ 1 ሊትር ቤንዚን በድብቅ እስከ 180 ብር እየተሸጠ ነው።

በከተማይቱ ያሉ ሁሉም ማደያዎች ውስጥ ቤንዚን የለም ተብሏል።

ይህን ተከትሎ 1 ሊትር ቤንንዚን ከ150 ብር እስከ 180 ብር በድብቅ እየተሸጠ ይገኛል።

ቀድሞውም ቢሆን በከተማዋ በድብቅ ነዳጅ ይሸጥ ነበር። ዋጋውም 100 ብር የነበረ ሲሆን አሁን ላይ በመላ ከተማይቱ ነዳጅ መጥፋቱን ተከትሎ እስከ 180 ብር ደርሷል።

የከተማ ውስጥ ታክሲዎች በተለይ በከተሞች ዳርቻ ዋጋቸዉን እጥፍ ከማድረግ በዘለለ ኮንትራት ካልሆነ አንጭንም እያሉ መሆኑን ሰምተናል።

አንድ የሀዋሳ ከተማ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል  " ዛሬ በሀዋሳ 1 ሊትር ቤንዚል ከ170 ብር ጀምሮ እየተሸጠ ነው። በየትኛውም ነዳጅ ማደያ ዛሬ ቤንዚል የለም " ብሏል።

" አንዳንድ ታክሲዎች ዝም ብለን ከምንቀመጥ ብለው 2 ሊትር ከ320 ብር ጀምሮ እየገዙ ፤ የ5 ብር መንገዶችን በ10 ብር እየጫኑ ነው ፤ ከዛ ውጭ ሌሎች በተለይ ባጃጆች በየጥሻው ቆመው ነው ያሉት " ብለዋል።

የከተማው ትራንስፖርት ቢሮም ሆነ የነዳጅ ጉዳይ የሚመለከተዉ የሀዋሳ ከተማ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ትናንት ስብሰባ ላይ እንደነበሩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረዳት ችሏል።

ስብሰባውን ተከትሎ እስካሁን ምንም አዲስ ነገር አልተፈጠረም።

በትላንትናው ዕለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡት  የከተማዉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ችሎት " ጉዳዩ አገር አቀፍ ችግር ነው " ብለዋል።

በማደያዎች ነዳጅ አለመኖሩን እና መንገድ የጀመረ የነዳጅ ጫኝ ቦቴ እንደሌለ በመግለጽም ማህበረሰቡ እንዲታገስ ጥሪ አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#የጤናባለሞያዎች

" የ5 ወር የትርፍ ሰአት ክፍያ አልተከፈለንም !  አፋጣኝ ምላሽ እንፈልጋለን " - በዋቻሞ ዩኒቨርስቲ የንግስት እሌኒ መሐመድ ሆስፒታል ሰራተኞች

" በጀቱ ስለተለቀቀልን ክፍያዉን በሁለት ቀን ውስጥ እናጠናቅቃለን ተረጋጉ " - የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ


በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሀመድ ሆስፒታል ውስት የሚሰሩ ሰራተኞች 5 ወር ሙሉ የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ለወራት የትርፍ ሰአት ክፍያ ስንጠይቅ ነበር " ያሉት ሰራተኞቹ ከሰሞኑ ድምጻቸዉን ለማሰማት ሰልፍ ለመውጣት መገደዳቸውን አመልክተዋል።

" የዘገየዉ ገንዘባችን ይሰጠን  !! " ሲሉም ለሚመለከተዉ አካል መልእክታቸዉን አሰምተዋል።

" የኑሮ ዉድነት ምን ያክል ፈተና እንደሆነብን እየታወቀ የትርፍ ሰአት ክፍያችን በጠየቅን ቁጥር ቀጠሮ መስጠት የማይሰለቸዉ የሆስፒታሉ አስተዳደር ትእግስታችን ተፈታትኖታል " የሚሉት ሰራተኞቹ " ከዚህ በላይ መታገስ የምንችልበት ሁኔታ ላይ ባለመሆናችን ጥያቄያችን በቶሎ ይመለስ " ሲሉ አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞቹን ጥያቄ ይዞ የሆስፒታሉን ስራ አስኪያጅ ዶክተር አያኖ ሻንቆን አነጋግሯል።

" ምንም እንኳን ችግሩ የታወቀ ቢሆንም የ5 ወር መዘግየት ሰልፍ የሚያስወጣ አልነበረም " ብለዋል።

አሁን ላይ ክፍያዉን ለማጠናቀቅ ቢበዛ 2 ቀናት ብቻ እንደሚበቃቸዉ ገልጸዋል።

የገንዘብ እጥረቱ የተከሰተዉ የነበረውን የበጀት እጥረት ለማስተካከል ዩኒቨርሲቲው ቅድሚያ ለተማሪ በማለቱ እንደሆነ አስረድተዋል።

" አሁን ላይ በጀቱ ተለቋል " ብለዋል።

ለክፍያው የተፈቀደው ገንዘብ በጽሁፍ እንጅ በካሽ አለመለቀቁን ተከትሎ ክፍያዉ በቶሎ አለመጀመሩን የገለጹት ስራ አስኪያጁ ፥ " አሁን ገንዘቡ በመድረሱ በ2 ቀን ውስጥ ክፍያዉ ይጠናቀቃል " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
" እኔ ያያሁት 3 ሰዎች ሞተዋል እና የቆሰሉ ሰዎችም ነበሩ " - ነዋሪ

በአዳማ ከተማ ፤ በቦኩ ሸነን ክፍለ ከተማ ሀሮሬቲ ወረዳ እና ቶርበን ኦቦ ወረዳ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ የሰው ሕይወት ማለፉና የቆሰሉ ሰዎች መኖራቸውን ለመስማት ችለናል።

በነዋሪዎች ዘንድ ተቃውሞ እንዲቀሰቀሰ ምክንያት የሆነው የከተማ አስተዳደሩ በወረዳዎቹ የሚገኙ ቤቶችን ሕገ-ወጥ ናቸው በሚል የማፍረስ ሂደት ሊጀምር ሲል መሆኑን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

ከዚህ ቀደም ይፈርሳሉ ያሏቸውን ቤቶች በቀይ ቀለም " X " እያረጉ እንደነበር እና ዛሬ ለማፍረስ ሲመጡ ነዋሪዎች ተቃውሞ እንዳነሱ ይህን ተከትሎም የጸጥታ ኃይሎች ተኩስ መክፈታቸውን አንድ የዐይን እማኝ አስረድተዋል።

ቦታዎቹ ላለፉት ዓመታት ግብር ሲከፈልባቸው የነበሩ እንደሆኑም ጠቁመዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የአከባቢው ነዋሪ እንዳሉት " በተቀሰቀሰው ግጭት እኔ ያያሁት 3 ሰዎች ሞተዋል እና የቆሰሉ ሰዎችም ነበሩ። በዛ አከባቢ ከሰዓት በኋላ እንቅሰቃሴ አልነበረም። ሁሉም ሰው በቤቱ ውስጥ ተቀምጧል እና በአጠቃላይ ያለውን ነገር ማወቅ አልቻልንም " ሲሉ ገልጸዋል።

ከማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ያገኘናቸው ቪዲዮዎች እንደሚያሳዩት የኢትዮጵያ እና የኦሮሚያ ክልል ባንዲራ የያዙ በርካታ ሰዎች ተቃውሞቸውን ለማሰማት መንገድ በመዝጋት እና " ፈረሳው ይቁም !! " የሚሉ መፈክሮች እየሰሙ እንደነበር ነው።

በሌላ አንድ ቪዲዮ ላይ ነዋሪዎቹ በዱላ እንዲሁም በድንጋይ መንገድ ዘግተው እንደነበር ተመልክተናል።

ነዋሪው ተቃውሞውን ማሰማት በጀመረበት ወቅት ተኩስ መጀመሩና በሰልፍ ላይ የነበሩ ሰዎች ሲበታተኑም ተመልክተናል።

በዚህ ውስጥ የሰዎች ሕይወት ማለፉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዐይን እማኞች መስማት የቻለን ቢሆንም ምን ያህል ሰዎች ሕይወታቸው እንዳለፈ ማረጋገጥ አልተቻለም።

ከከተማው አመራርና የጸጥታ አካላት ጉዳዩን ለማጣራት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

#TikvahEthiopiaFamilyAdama

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል። ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው…
#Update

የሀገር መከላከያው ስለ ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ እንቅስቃሴ ምን አለ ?

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።

የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነትን መሰረት በማድረግ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሀገር መከላከያው ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ እንዲያስተባብር አቅጣጫ ተሰጥቶ እየሰራ እንዳለ አመልክተዋል።

የፀለምት እና አካባቢው ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ኃላፊነት የተሰጠው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መሆኑን ተናግረው " ስራው እጅግ በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው " ብለዋል።

ዛሬን ረቡዕ ጨምሮ ባለፉት ቀናት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቄያቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ሌ/ጄነራሉ ፥ ተፈናቃዮች እየተመለሱ ያሉት አስፈላጊና መሟላት አለባቸው የተባሉ ቅድመ ሁኔታዎች ከጎን እየተሰሩ ነው ብለዋል።

ስራው በፍጥነት እየሄደ ያለው አብዛኛዎቹ አርሶ አደር የክረምቱ ወቅት ሳያልፍ እርሻውን እንዲሰራና ህይወቱን እንዲመራ በማሰብ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በፀለምት ካሉ 25 ቀበሌዎች አብዛኛው ተፈናቃይ ከ22 ቀበሌዎች ነው አሁን ባለው ሁኔታ በአስራዎቹ ቀበሌዎች ተፈናቃይ ተመልሷል ፤ እስከዚህ ሳምንት መጨረሻ ቀሪ 11 ቀበሌዎች  አብዛኛው እንዲገባ ይደረጋል ሲሉ አሳውቀዋል።

የቀረውም ስራ በቀጣይ ይሄዳል ብለዋል።

ስለ ታጣቂዎች መውጣት ምን አሉ ?

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የትግራይ ታጣቂዎች በኃይል ገብተዋል " ስለሚባለው ጉዳይ ሌ/ጄነራሉ ፥" ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ በፀለምትም ይሁን በወልቃይት በኃይል የገባባቸው ቦታዎች የሉም " ሲሉ መልሰዋል።

ፀለምት ካሉት ቀበሌዎች 3 ቀበሌዎች ላይ የትግራይ ታጣቂዎች እንዳሉ እነዚህም ጦርነት ሲቆም ባሉበት የቆሙ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።

ባለው መግባባት ከሁለቱም ክልል ጋር የሁለቱም ክልል ታጣቂ መውጣት ስላለበት ተፈናቃዮችን በመመለስ ታጣቂዎቹን የማስወጣት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ፀለምት ያለው የትግራይ ታጣቂ እንዲወጣ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከተፈናቃይ ጋር ታጣቂ እንዳይመለስ ስለሚሰራ ስራ ምን አሉ ?

በአማራ በኩል " ከተፈናቃይ ጋር ታጣቂ ይገባል " የሚል ስጋት እንዳለ ያልሸሸጉት አዛዡ ፥ በትግራይ በኩልም " ታጣቂዎች (በአማራ በኩል ያሉ) እንደ አዲስ ተደራጅተዋል ስጋት ናቸው " የሚል ነገር እንዳለ ገልጸዋል።

" የሀገር መከላከያው ከሁለቱም በኩል ከተፈናቃዮች እና እዛው ከነበሩት ነዋሪዎች ( ካልተፈናቀሉት ) ሽማግሌዎች እንዲውጣጡ አድርጎ የተፈናቃዮችን ዝርዝር ለመከላከያ ተሰጥቶ ከዛም መከላከያው ከሽማግሌዎቹ ጋር አብሮ ሰዎቹ የዛ ቦታ ነዋሪ መሆናቸውን እየጠየቀና እያረጋገጠ ተፈናቃዮች ይመለሳሉ " ብለዋል።

' ይሄ ታጣቂ ነው ፣ ይሄ ሚሊሻ ነው ' የሚል ክርክር በሽማግሌ ደረጃ ከተነሳ ወደ ህዝብ ተወስዶ ህዝቡ እራሱ ይፈርዳል ሲሉ ተናግረዋል።

" እንግዳ ሰው ሲገባ ይታወቃል ይህ ጉዳይ አሳሳቢ አይደለም " ያሉት አዛዡ ፥ ገጠር ይሁን ከተማ መሬት ከሌላቸው / ሊገቡበት የሚችሉበት ቤት ከሌላቸው ተለይቶ ይታወቃል ብለዋል።

#Ethiopia
#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሀገር መከላከያው ስለ ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ እንቅስቃሴ ምን አለ ? የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገው ነበር። የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነትን መሰረት በማድረግ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል። ሀገር መከላከያው ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ እንዲያስተባብር አቅጣጫ…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ በጦርነት ከፀለምት እና አካባቢው ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉትን ወገኖች ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ እየተሰራ ይገኛል።

በርካታ የህዝብ ማመላለሻ መኪናዎች ተፈናቃዮችን እያደረሱ ነው።

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማስተባበር ኃላፊነት እየተወጣ ነው።

በፀለምት ውስጥ ካሉ 25 ቀበሌዎች በአብዛኛው ከ22ቱ ዜጎች ተፈናቅለዋል።

እነዚህን ዜጎችን ነው በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ የተገለጸው።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በቀጣይም የሌሎች አካባቢዎች ተፈናቃዮች እንደሚመለሱ አሳውቋል።

Video Credit - DW

@tikvahethiopia
የአሜሪካ ኤምባሲ ነገ ለምን ተዘግቶ ይውላል ?

በአዲስ አበባ የአሜሪካ አሜባሲ ነገ ሀሙስ ሙሉ ቀን ተዘግቶ ይውላል።

የሚከፈተውም በነጋታው አርብ ዕለት ነው።

ኤምባሲው ተዘግቶ የሚውለው የሀገሪቱን የነጻነት ቀን ለማክበር ነው።

አሜሪካ በየአመቱ እኤአ ሃምሌ 4 ላይ የነጻነት ቀኗን ታከብራለች።

ሀገሪቱ እኤአ በ1776 በኢትዮጵያ አቆጣጠር ደግሞ በ1769 ዓ.ም ነው ከብሪታንያ ቅኝ ግዛትነት ነጻነቷዋን ያወጀችው።

@tikvahethiopia
#CHAPA

የይለፍ ቁጥሮን ባለማጋራት ራስዎን ካጭበርባሪዎች ይጠብቁ!

🚫አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎች ሲኖሩ ወደ 📞8911 በመደወል ሪፖርት ያድርጉ

🌐 ለበለጠ መረጃ ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ፡ https://chapa.co/

#chapa #chapapayments #Fraudawareness #Digitalpayment
2024/09/30 08:28:36
Back to Top
HTML Embed Code: